Badr Ethiopia

Badr strives to foster transformative social change by implementing impactful, sustainable, and scalable solutions grounded in Islamic principles, empowering the Ethiopian Muslim community.

06/05/2026

♦️♦️♦️በአርሲ ወገኖቻችን ላይ የተፈፀመውን ጥቃትእናወግዛለን !!
ከበድር አለም አቀፍ የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ድርጅት የተሰጠ መግለጫ

06/05/2026
የሐዘን መግለጫ               ኢናሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን   በድር ኢትዮጵያ የቀድሞው የአዲሰ አበባ ከንቲባ የነበሩት አምባሣደር አሊ አብዶ ወደ አሄራ መሄድ የተሰማውን ጥልቅ ሐዘ...
06/05/2026

የሐዘን መግለጫ
ኢናሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን
በድር ኢትዮጵያ የቀድሞው የአዲሰ አበባ ከንቲባ የነበሩት አምባሣደር አሊ አብዶ ወደ አሄራ መሄድ የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን ይገልፃል።
የቀድሞ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ የነበሩት አምባሳደር ዓሊ አብዶ በሕየወት ዘመናቸው ለሀገራቸው እንደዜጋ ለእምነታቸው እንደ ሞዕሚን ለፈፀሟቸው አበርክቶዎች በድር ኢትዮጵያ እውቅና ይሰጣል።
አምባሳደር አሊ አብዶ በተለይም 27ኛው የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ በነበሩባቸው ከ1990 - 1995 አምስት አመታት ሙስሊም ጠል በሆኑ የቢሮክራሲው ቡድን አባላት በመሰጂዶች አካባቢ የሚፈፅመውን ደባ በመበጣጠስ ፍትሐዊ የአምልኮ ሥርዐት እንዲኖር ያበረከቱት አስተዋፅኦ የሚታወሱ ናቸው።
አምባሳደር ዓሊ አብዶ በአርሲ ዴራ ከተማ ከአባታቸው አቶ ዓሊ ሱለይማንና ከእናታቸው ወ/ሮ አፀደ ወልደማሪያም የተወለዱ ሲሆን ከትዳር አጋራቸውም ሶስት ሴቶች እና አንድ ወንድ ልጅ አፍርተዋል።
አምባሳደር ዓሊ አብዶ በስራ ዘመናቸው ሁሉ ሐገራቸውንና ሕዝባቸውን በቅንነት፣ በታማኝነትና በታታሪነት ሲያገለግሉ ነበር። በድር አለም አቀፍ የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ድርጅት አላህ ለአምባሳደር ዓሊ አብዶን ጀነተል ፊርደውስ፤ ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸውና ላገለገሉት ሕዝብ ደግሞ መፅናናትን እንዲሰጥ ይማፀናል።
በድር አለም አቀፍ የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ድርጅት

እንኳን 1447 ዓ.ሂ  የዒደ አል አድሐ (አረፋ) በዓል አደረሰን፣ አደረሳችሁ! 🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺ዒደ አል አድሐ (አረፋ) በዓል በእስልምና አስተምሮ ከፍ ያለ መንፈሳዊ ትርጉም ያለው የመስዋዕት...
05/27/2026

እንኳን 1447 ዓ.ሂ የዒደ አል አድሐ (አረፋ) በዓል አደረሰን፣ አደረሳችሁ!
🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺🌺
ዒደ አል አድሐ (አረፋ) በዓል በእስልምና አስተምሮ ከፍ ያለ መንፈሳዊ ትርጉም ያለው የመስዋዕትነት፣ የታዛዥነት እና የርህራሄ በዓል ነው።ነቢዩ ኢብራሂም (ዐ.ሰ) ለአላህ ያሳዩትን ፍጹም ታዛዥነትና ፅኑ እምነት ያስታውሰናል። ከዚህ ታላቅ በዓል የምንማረው ለእውነት፣ ለሰላም፣ ለፍትሕ እና ለሰውነት መቆም እንዳለብን ነው።ኢዳችን ስናከብር ከድሆች፣ ከችግረኞች እና ከተጎዱ ወገኖቻችን ጋር ያለንን በመካፈል በዓሉን በእውነተኛ መንፈስ እናከብራለን።አሏህ በልባችን ፍቅርን፣ በማህበረሰባችን አንድነትን፣ በሀገራችን ሰላምና መተባበርን ያጠናክርልን።

ኢድ ሙባረክ!

🌟🌙እንኳን ለ1447ኛው የኢድ አል–አድሀ (አረፋ) በዓል በሠላም አደረሳችሁ በማለት በድር ኢትዮጵያ መልካም ምኞቱን ይገልፃል!
05/26/2026

🌟🌙እንኳን ለ1447ኛው የኢድ አል–አድሀ (አረፋ) በዓል በሠላም አደረሳችሁ በማለት በድር ኢትዮጵያ መልካም ምኞቱን ይገልፃል!

05/21/2026
11/18/2025

ተማሪዎችን ከትምህርት ገበታቸው ላይ የማፈናቀል ሴራን በድር ኢትዮጵያ እንደሚያወግዝ አስታወቀ።
መጅሊስም ማብራሪያ እንዲሰጥ ጠይቋል።

ነጃሺ ቲቪ :- ህዳር 9 ቀን 2018

በትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ ኃላፊዎች ወቅት እየጠበቀ የሚካሄድ ሙስሊም ተማሪዎችን ከትምህርት ገበታቸው የማፈናቀል ድብቅ ሴራ መቆም እንዳለበት በድር አለም አቀፍ የኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች ድርጅት ያሳወቀው ትላት ባወጣው መግለጫ ነው ።

ባለፉ አመታት የፈተና ወቅትና የመስሊም በዓላትን እየጠበቁ ሙስሊም ተማሪዎችን ከትምህርታቸው መስተጓጎላቸውና አሁን ደግሞ ሆንተብሎ ከትምህርታቸው ለማፈናቀል እንቅስቃሴ መጀመሩን በመግለጫው ጠቁሟል ።

ህዳር 2 ቀን 2018 አዳማ ላይ የሁሉም ክልሎች የትምህርት ኃላፊዎችና ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት በሴኩላር ስም እስላማዊ አለባበሶች መከልከላቸውና ይህም መመሪያ እንዲተገበር ትዕዛዝ መተላለፉን አውግዟል።

በጉዳዩ ላይ መጅሊስም ማብራሪያ እንዲሰጥበት ጠይቋል።
የመግለጫውን ሙሉቃል አያይዘን አቅርበነዋል።

Address

5185 MacArthur Boulevard NW
Washington D.C., DC
20016

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Badr Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Badr Ethiopia:

Featured

Share