Sidama Media Network-SMN

Sidama Media Network-SMN Sidama Media Network

የ2019 ዓ.ም የሲዳማ ብሄር ዘመን መለወጫ ፍቼ-ጫምባላላ በዓል በዓለም አቀፍ ደረጃ በደማቁ ተከበረ።************//**********ማርች  30, 2026 SMN ዲሲ​የዘንድሮው የሲዳማ...
03/31/2026

የ2019 ዓ.ም የሲዳማ ብሄር ዘመን መለወጫ ፍቼ-ጫምባላላ በዓል በዓለም አቀፍ ደረጃ በደማቁ ተከበረ።
************//**********
ማርች 30, 2026
SMN ዲሲ

​የዘንድሮው የሲዳማ የዘመን መለወጫ በዓል—ፍቼ-ጫምባላላ—ከምንጊዜውም በላይ በላቀ ድምቀት፣ በህብረት እና በታላቅ መነቃቃት በመላው ዓለም በሚገኙ የሲዳማ ተወላጆችና ወዳጆች ዘንድ እንደተከበረ ታውቋል።

በአሜሪካን ሀገር በ​ዋሽንግተን ዲሲ፣ አትላንታ ጆርጅያ እና ሲያትል፤ በካናዳ ቶሮንቶ፤ በአውሮፓ ጀርመን በዓረብ ሀገራት በተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስ እንዲሁም በአዲስ አበባ ከተሞች የሲዳማ ማህበረሰብ አባላት ውብና ማራኪ በሆኑ ባህላዊ አልባሳት አጊጠው፣ የጥንቱንና ጥልቅ ትርጉም ያለውን ቅርሳቸውን በአንድነት አድምቀውታል።

​በየቦታው ታዳሚዎች በሲዳማ ህዝብ ዘንድ እጅግ ተወዳጅ የሆነውና በክብር የሚቀርበውን ባህላዊ ምግብ ቡርሳሜ በህብረት ተቋድሰዋል። በተጨማሪም የማህበረሰቡን አንድነትና በረከት በሚያበስረው የሻፈታ ስነ-ስርዓት በዓሉ ይበልጥ በባህላዊ እሴቶች ተሞልቷል።

ልዩ መስህብ የሆነው በስነ-ጥበብ የታጀበ፣ በሚገባ የተደራጀ ሚድያ ባልነበረበት ጊዜ ህዝቡ ወሳኝ መልእክቶችን በሚያዝናና መልኩ የሚያስተላልፍበት የቄጣላ ትዕይንትም አንዱ የበዓሉ ድምቀት አካል ነው።

በየቦታው ​ተሳታፊዎች የነገዋን ብሩህ ተስፋ በማለም የመልካም ምኞት መግለጫዎችን የተለዋወጡበት፣ የሲዳማን መንፈስና ጥንታዊ ስልጣኔ በዓለም ፊት በኩራት ያሳዩበት ታሪካዊ ዓመት መሆኑ ታምኗል።

የሲዳማ ብሄር አዲስ ዓመት – ፍቼ-ጫምባላላ በዋሽንግተን ዲሲ በድምቀት ተከበረ ።*****************//*****************ማርች 29, 2026SMN ዲሲየሲዳማ ህዝብ የዘመን መ...
03/30/2026

የሲዳማ ብሄር አዲስ ዓመት – ፍቼ-ጫምባላላ በዋሽንግተን ዲሲ በድምቀት ተከበረ ።
*****************//*****************
ማርች 29, 2026
SMN ዲሲ

የሲዳማ ህዝብ የዘመን መለወጫ በዓል ፍቼ-ጫምባላላ በዓል በዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ በታላቅ ድምቀት ተከብሯል።

በዝግጅቱ ላይ በዲኤምቪ (DMV) አካባቢ የሚኖሩ የሲዳማ ማህበረሰብ አባላት፣ ኢትዮጵያውያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች የተገኙ ሲሆን፤ በዓሉም የባህልና የአንድነት መንፈስ የታየበት ነበር።

የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የዲኤምቪ አካባቢ የሲዳማ ማህበር ፕሬዝዳንት ዶ/ር ጸጋዬ ጊምቦ፤ ለምክትል አምባሳደሩ፣ ለዲፕሎማቶችና ለታዳሚዎች ሞቅ ያለ አቀባበል ካደረጉ በኋላ፣ ስለ ባህላዊ እሴቶችና ስለ ማህበረሰቡ ጥንካሬ ገልጸዋል።

የኤምባሲው ምክትል አምባሳደር ባስተላለፉት መልዕክት፣ ባህልን ጠብቆ ማቆየትና ከሀገር ውጭ የሚኖረውን ማህበረሰብ ትስስር ማጠናከር ያለውን ፋይዳ አብራርተዋል።

የበዓሉ ልዩ ድምቀት የሆነውና የሲዳማን ማንነት የሚወክለው ባህላዊው ቀጣላ (Qexaala) የቀረበ ሲሆን፤ ታዳሚዎች ተወዳጁን የሲዳማ ባህላዊ ምግቦችን ሻፌታ እና ቡሪሳሜ ተጋርተዋል።

ከዕለቱ ዝግጅቶች መካከል ሁሉንም ያሳተፈው በምልክት ቋንቋ የመግለጽ ጫዎታና የጥያቄና መልስ መርሃ-ግብር ለታዳሚው ልዩ ደስታንና ፈገግታን የፈጠረ ነበር።

በመጨረሻም፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ መዝሙርና የሲዳማ ክልል መዝሙር ተዘምሮ በዓሉ በታላቅ የአገር ፍቅርና የማንነት ኩራት ተጠናቋል።

አይዴ ጫምባላላ።

AYIDDE CAMBALAALLA!**********//*************በዋሽንግተን ዲስ ለሚከበረው የሲዳማ ብሔር ዘመን መለወጫ ፍቼ ጫምባላላ በዓል በአክብሮት ተጋብዘዋል::Date: March ...
03/28/2026

AYIDDE CAMBALAALLA!
**********//*************
በዋሽንግተን ዲስ ለሚከበረው የሲዳማ ብሔር ዘመን መለወጫ ፍቼ ጫምባላላ በዓል በአክብሮት ተጋብዘዋል::

Date: March 29, 2026

Time: 1 - 5 PM EST

Address: 3506 International Dr NW,
Washington, DC 20008

በቶሮንቶ የሚኖሩ የሲዳማ ኮሚዩኒቲ አባላት የፊቼ ጫምባላላ በአልን አከበሩ።**************//**************ማርች 23, 2026SMN ዲሲበቶሮንቶ የሚገኙ የሲዳማ ኮሚዩኒቲ አባላ...
03/23/2026

በቶሮንቶ የሚኖሩ የሲዳማ ኮሚዩኒቲ አባላት የፊቼ ጫምባላላ በአልን አከበሩ።
**************//**************
ማርች 23, 2026
SMN ዲሲ

በቶሮንቶ የሚገኙ የሲዳማ ኮሚዩኒቲ አባላት የሲዳማ አዲሱን አመት የፊቼ ጫምባላላ በአል በተለያዩ ዝግጂቶች አክብረው መዋላቸውን ከስፍራው የደረሰን መረጃ ያመለክታል።

እ.ኤ.አ ማርቻ 21 , 2026 በተከበረው በዚሁ በአል የሲዳማን ህዝብ ባህል እና ታሪክ የተመለከተ ጽሁፍ በታዳጊዎች የቀረበ ሲሆን፣ በውጭ አገር ተወልደው በማደግ የሚገኙ እነዚሁ የማህበረሰቡ ልጆች ባህላቸውን በራሳቸው ተነሳሽነት በቀጣይነት እያከበሩ እንዲዘልቁም ምክክር ተደርጎል።

በእለቱ በስፍራው ለነበሩ ለሁሉም ታዳጊዎች እና ህፃናት ልዩ የፊቼ ጫምባላላ ስጦታ ከኮሚኒቲውም ተበርክቶላቸዋል።

በአሉን በየአመቱ በጋራ ሰብሰብ ብሎ ማክበር ለኮሚኒቲው ያለው ጠቀመታ የአንድ ቀን ጉዳይ ብቻ አለመሆኑና በተለይ የማህበሩን አንድነት ለማጠናከር ፋይዳው የጎላ መሆኑን ታዳሚዎች ገልፀዋል።

የግሎባል ሲዳማ ዳያስፖራ ማህበር (GSDA) ሥራአስፈጻሚ ኮሚቴ ምርጫ ውጤት ይፋ ሆነ።**************/***************SMN, ዲሲማርች 21 2026ላለፉት ወራት ሲካሄድ የቆየው...
03/22/2026

የግሎባል ሲዳማ ዳያስፖራ ማህበር (GSDA) ሥራአስፈጻሚ ኮሚቴ ምርጫ ውጤት ይፋ ሆነ።
**************/***************
SMN, ዲሲ
ማርች 21 2026

ላለፉት ወራት ሲካሄድ የቆየው የግሎባል ሲዳማ ዳያስፖራ ማህበር(GSDA) የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ምርጫ ውጤት ዛሬ ይፋ ሆልኗ።

ምርጫውን ሲያከናውን የቆየው፣ ሶስት አባላት ያለው አስመራጭ ኮሚቴ ዛሬ በተካሄደው የካውንስሉ ስብሰባ ላይ፣ ከቀረቡት ስምንት ዕጩዎች መካከል በየፖዚሺኑ አብላጫ ድምጽ ያገኙትን አምስት አሸናፍዎች ይፋ አድርጓል።

በዚህ መሰረት የተመረጡ ግለሰቦች
1ኛ. ዶ/ር ጸጋዬ ግንቦ:- ፕረዚዴንት
2ኛ አባ ሙሴ ዮሀንስ:-ም/ፕሬዚዴንት
3ኛ. አቶ ነጋ ጠይቀ:- ፋይናንስ ኦፍሴር
4ኛ. አቶ ከበደ ካቻራ:- የፕላንና ፕሮግራም ኦፍስር
5ኛ. አቶ ፋና አለማዬሁ:- የህዝብ ግንኙነት እና ኮሚዩንኬሺን ኦፍሴር
ናቸው።

ይህንንም ተከትሎ የካውንስሉ አባላት አስመራጭ ኮሚቴው ሳይንሳዊ ጥናት ተደርጎ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት፣ ላደረገው በቴክኖሎጂ የታገዘ፣ ግልጽ፣ ነጻና ገለልተኛ ምርጫ፣ የኮሚቴውን አባላት አመስግኖ ውጤቱን ሙሉ በሙሉ ተቀብሎ አጽድቋል። ለተመረጡትም የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፎአል።

የተመረጡ የስራአስፈጻሚ አባላትም ውጤቱን ተቀብለው ወደፊት ብዙ የሚሰሩ ስራዎች ስላሉ የሁሉም ትብብር ከጎናቸው እንዳይለያቸው ለአባላቱ ጥሪ አቅርበዋል።

በመጨረሻም የካውንስሉ ቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር ማርቆስ ዋሬ ለአስመራጭ ኮሚቴዎች የምስጋና ሰርቴፊኬት አበርክቶ ስብሰባውን አጠናቋል።

የGSDA ስራአስፈጻሚ ኮሚቴ ምርጫ ውጤት ዛሬ ይፋ እንደሚሆን ተጠቆመ።************/*************SMN, ዲሲማርች 21 2026ሲካሄድ የቆየው የግሎባል ሲዳማ ዳያስፖራ ማህበር G...
03/21/2026

የGSDA ስራአስፈጻሚ ኮሚቴ ምርጫ ውጤት ዛሬ ይፋ እንደሚሆን ተጠቆመ።
************/*************
SMN, ዲሲ
ማርች 21 2026

ሲካሄድ የቆየው የግሎባል ሲዳማ ዳያስፖራ ማህበር GSDA የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ምርጫ ውጤት ዛሬ ይፋ እንደሚያደርግ ከአስመራጭ ኮሚቴ ሚድያችን ለመስማት ችለናል።

ውጤቱ ይፋ ሲደረግ ተከታትለን የሚናቀርብ ይሆናል።

ፍቼ-ጫምባላላ በዓልን በሲያትል ዋሽንግተን  በጋራ እናክብር!**************//**************SMN, ዲሲማርች 2026.በዩኒስኮ በዓለም ቅርሰነት የተመዘገበውና የሲዳማ ህዝብ የ...
03/20/2026

ፍቼ-ጫምባላላ በዓልን በሲያትል ዋሽንግተን በጋራ እናክብር!
**************//**************
SMN, ዲሲ
ማርች 2026.

በዩኒስኮ በዓለም ቅርሰነት የተመዘገበውና የሲዳማ ህዝብ የዘመን መለወጫ የሆነው ፍቼ-ጫምባላላ በዓል በሰሜን አሜሪካ ደረጃ ዘንድሮ በሲያትል ዋሸንግተን እንዲከበር በተወሰነው መሰረት ቅዳሜ March 28 ይከበራል::

ሁላችንም የጋራችን የሆነውን ድንቅ ፍቼ-ጫምባላላ በዓልን በጋራ እንዲናከብር ዘንድ በመላው አሜሪካ፣ ካናዳ እንድሁም በሲያትል ዋሸንግተን አቅራቢያ የምትገኙ አትዮጵያውያን በክብር ተጋብዛችኋል::

ፍቼ-ጫምባላል ስናከብር ስለሀገራችን ሰላም ፈጣሪን እንማፀናለን፤ አንድ የሚያደርጉንን ሰብዓዊ እሴቶችን እናስታውሳለን።

ቀን:- ማርች 28፣ 2026
ሰዓት:- ከቀትር በኋላ 12፡00 PM (ማምሻ ሰዓት)
ቦታ:- 7201 E Green Lake Dr. N, Seattle, WA 98115

እርሶና እና ቤተሰቦ በታላቅ ክብር ተጋብዘዋል!

አዘጋጅ ኮሚቴ ከሲዳማ ዲያስፖራ አለም አቀፍ ኮሚቴ ጋር በመተባበር።

Ayidde Chambalaalla!! 🎉 !!

03/18/2026

የአውሮፓ ሲዳማ ኮሚዩኒቲ በጀርመን ለመጀመሪያ ጊዜ ለሚያከብረው ፍቼ-ጫምባላላ በዓል እንዲገኙለት የአውሮፓ ነዋሪ ለሆኑ ኢትዮጵያውያን ግብዣ አቀረበ።
****************//****************
ማርች 18, 2026
SMN, ዲሲ

"ፍቼ ጨንበላላ በዩኔስኮ የማይዳሰሱ የአለም ቅርሶች የተመዘገበ የሲዳማ ብሔር የሰላም፣ የፍቅርና የአብሮነት ተምሳሌት ነው" ያለው ማህበሩ ይህን ደማቅ እና ተወዳጅ በዓል ከዚህ ቀደመ ባልተለመደ መልኩ እና ለመጀመሪያ ጊዜ በአንድነት እና በደማቅ ሁኔታ ለማክበር በአውሮፓ ላሉ የሲዳማ ዳያስፖራ ኮሚኒቲ አባላት እና ኢትዮጵያውያን በጀርመን ፍራንክፈርት አፕርል 25/04/2026 ለማክበር ጥሪ አቅቧል።

ዝግጅቱን ከደቡብ ልማት ማህበር ጋር በመተባበር ማዘጋጀቱን ጠቅሶ "በአውሮፓ በተለያዩ አቅጣጫዎች ያላችሁ የሲዳማ ክልል ተወላጆች፤ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በሙሉ በዚህ ደማቅ እና ተናፋቂ በዓል ላይ እንዲትገኙ በአክብሮ ተጋብዛችኋል" ብሏል።

የዝግጁቱ አድራሻ Mannheimer Str. 15, 60329 Frankfurt am Main መሆኑንም ጠቁሟል።

ሲዳማ አዲስ እና ባለራዕይ መሪ ያስፈልጋታል ተባለ።************//************ማርች 17, 2026SMN, ዲሲሰሞኑን የፍቼ ጫንባላላ በዓል አከባበር ላይ ተገኝተው የክልሉ ፕሬዝዳ...
03/17/2026

ሲዳማ አዲስ እና ባለራዕይ መሪ ያስፈልጋታል ተባለ።
************//************
ማርች 17, 2026
SMN, ዲሲ

ሰሞኑን የፍቼ ጫንባላላ በዓል አከባበር ላይ ተገኝተው የክልሉ ፕሬዝዳንት አቶ ደስታ ሌዳሞ ያደረጉትን ንግግር ተከትሎ በርካቶች ሀሳባቸውን እየሰጡ ይገኛሉ። ሀሳባቸው ከሰጡት መሀከል በሰሜን አሜሪካ የሚኖሩ፣ ለሲዳማ ህዝብ ትግል ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከቱ የአስተውሎተ-ሰውሰራሽ ሳይንቲስት ዶክተር በኃይሉ ቤላሞ ይጠቀሳሉ።

ዶክተር በኃይሉ ቤላሞ የሲዳማ ክልል ርዕሰ-መስተዳድሩ በፍቼ ጫንባላላ በዓል አከባበር ላይ፣ በመድረክ ያደረጉትን ንግግር በተመለከተ የሚከተለውን ዘለግ ያለ ሀሳብ በግላቸው ፌስቡክ ገፅ አስፍረዋል።

«በዘንድሮው በዓል ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር በሕዝብ ፊት ቀርበው ብዙዎች ሲሰማቸው የነበረውን እውነት ተናግረዋል፤ ይኸውም አንድነቱ መላላቱን ነው።

ይህ ድፍረትን ይጠይቃል። ንግግሩ ከልብ የመነጨ ከሆነ፣ እንዲሁም ስህተትን አምኖ በተሻለ መንገድ ለመሥራት እውነተኛ ቁርጠኝነት የታየበት ከሆነ፣ የሚደነቅ ብቻ ሳይሆን ፊቼ ጫንባባላላ የሚጠይቀውም ይሄኑ ነው።

ነገር ግን፣ ፊቼ ጫንባላላ የሚያስተምረን ፈውስ እውነተኛነትን እንደሚሻ ነው። ያለ እውነተኛ ለውጥ የሚደረግ እርቅ ባዶ ነው።

ሲዳማ በለም መሬት፣ በባህል፣ እንዲሁም በሕዝቡ ብሩህ አእምሮና ጉልበት የታደለች እጅግ ሰፊ አቅም ያላት ክልል ናት። የሲዳማ ሕዝብ ታግሎ ያገኘው የክልልነት ጥያቄ ችግሩ አልነበረም። የክልልነት መብት ትክክለኛ መሠረት ነበረ፣ አሁንም ነው። የሚያመው እውነት ግን ትርጉም ያለው ኢኮኖሚያዊ ልማት ጨርሶ አለመኖሩ ነው፤ ይህ ደግሞ የሲዳማ ሕዝብ ወይም የክልልነት ጥያቄው ውድቀት አይደለም። ይልቁንም የአመራር ውድቀት ነው። በቃ፣ ግልጽና ቀላል እውነት ይሄው ነው።

ያለፈውን ስህተት ማመን ዋጋ የሚኖረው ለቀጣዩ እርምጃ መሰረት ሲሆን ብቻ ነው። የሚቀጥለው እርምጃ ደግሞ ግልጽ ነው፡ ሲዳማ አዲስና ባለራዕይ አመራር ያስፈልገዋል። ደፋር፣ ብቁና ሥራን ለመሥራት የሚተጋ አዲስ ትውልድ! በትላንትናው ታማኝነትና ዕዳ ያልተተበተበ አመራር! በየቀኑ ሲነቃ ስለ መንገድ፣ ስለ ሥራ ዕድል፣ ስለ ትምህርት ቤት፣ ስለ ኢንቨስትመንትና ስለ ተራው የሲዳማ ቤተሰብ ዕድል የሚያስብ—ያንን ለማሳካትም ተነሳሽነትና ራዕይ ያለው መሪ ያስፈልጋል። በአሮጌ መንገድ ላይ አዲስ ስም መለጠፍ ሳይሆን፣ እውነተኛና መሠረታዊ ለውጥ የሚያመጣ አዲስነት!

የሲዳማ ሕዝብ ብዙ የፊቼ በዓላትን አክብሯል፣ ብዙ ቃላትን ሰምቷል፣ እንዲሁም ረጅም ጊዜ ጠብቋል። ሕዝቡ በእውነተኛ ለውጥና በስም ብቻ በሚደረግ ለውጥ መካከል ያለውን ልዩነት ያውቃል። ይህ አዲስ ዓመት ይዞት በሚመጣው ተስፋና ግልጽነት፣ እውነተኛ ለውጥ ሲመጣ የማየት አለባቸው።

ፊቼ አንድ ሕዝብ በድፍረት መታደስን ሲመርጥ ምን ሊሳካ እንደሚችል የሚታይበት በዓል ነው። ይህ አዲስ ዓመት ለሲዳማ ሕዝብ ሁሌም የሚገባውን አዲስ፣ ደፋርና ባለራዕይ አመራር ይዞ ይምጣ—ሥራውን ዳር የሚያደርሱ መሪዎችን!»

03/14/2026

GSDA Boorde Murrichi Dr. Maarkoosi Buddusihu Ficheete Ayyaannira Sayisino Sokka
***********//***********
SMN, DC
May 14, 2026

ኣይዴ ጫምባላላ!*******//******በዋሽንግተን ዲሲ፣ ቬርጅኒያ እና ሜሪላንድ አካባቢ የሚንኖር የሲዳማ ኬሙይኒቲ የ2026 ዓ ም የፍቼ-ጫምባላላ በዓልን በማርች 29, 2026 ከታች በተጠ...
03/14/2026

ኣይዴ ጫምባላላ!
*******//******

በዋሽንግተን ዲሲ፣ ቬርጅኒያ እና ሜሪላንድ አካባቢ የሚንኖር የሲዳማ ኬሙይኒቲ የ2026 ዓ ም የፍቼ-ጫምባላላ በዓልን በማርች 29, 2026 ከታች በተጠቀሰው ቦታና ሰዓት ስለምናከብር በዚህ ዓለማቀፋዊና ደማቅ ሀገር በቀል በዓል ከቤተሰብ፣ ወዳጅ እና ጓደኛ ጋር እንድትገኙልን እያልን ለአካባቢው ኢትዮጵያውያንን እና ወዳጆቻችን ጥሪ እናደርጋለን።

ቦታ:- 3506 International Dr. NW, Washington DC 20008

ቀን:- March 29, 2026

ሰዓት:- 1PM EST

አስፈላጊ ዝግጅቶችን ለማድረግ ያመቸን ዘንድ መገኘቶን በስልክ ቁጥር 202-556-0899 ቀድመው እዲያሳውቁን በአክብሮት እንጠይቃለን።

ከፕሮግራሙ አስተባባሪዎች

AYIDDE CAMBALAALLA!**********//*************The Sidama Diaspora Community in the Washington DC, Maryland and Virginia wa...
03/14/2026

AYIDDE CAMBALAALLA!
**********//*************

The Sidama Diaspora Community in the Washington DC, Maryland and Virginia warmly invites all Ethiopia diaspora living in the area to join us in celebrating Fichee–Chambalaalla, the Sidama New Year. This cherished cultural tradition symbolizes renewal, unity, and the continuation of Sidama heritage across generations.

Please Join us for this joyful event as we celebrate the Sidama culture, strengthen community bonds, and welcome the New Year together.

📅 Date: March 29, 2026

⏰ Time: 1:00 PM EST

Venue: 3506 International Dr NW, Washington, DC 20008

Please share this invitation and send us your participation confirmation via (202)556-0899.

Address

DMV
Silver Spring, MD
20902

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Sidama Media Network-SMN posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Sidama Media Network-SMN:

Featured

Share