05/18/2024
ስለአማራ ህዝብ የህልውና ትግልና አንድነት ተብሎ በታላቁ እስክንድር ነጋ እየተከፈለ ያለ ያልተነገረ ታላቅ መስዋእትነት ‼️
በወዳጅና በጠላት 7/24 ሰዓት ስሙ እየተብጠለጠለ በዝምታ ድባብ የማስተናገዱ ምስጢር ምንድነው??
*** ወንድወሰን ተክሉ***
💥💥💥 እየተሰደቡ ዝም ለማለት፤ እየተብጠለጠሉ ዝም ለማለት ታላቁ እስክንድርን መሆን ሳይጠይቅ አይቀርም
ሁላችንም ብንሆን ስማችን ሲነሳ Re-act እናደርጋለን፡ ብዙዎች ስማቸው አንዴ ተነስቶ መቶ ግዜ ስማቸውን ለማጥራት መልሰው መላልሰው ሲናገሩ ይደመጣሉ፡፡ አንዳንዲች ደግሞ በዝምታ ልጔም እራሳቸውን ለጉመውና ሸብበው ግን ስማቸው በክፉ ሲነሳ ብቅ ብለው ከመቅጽፈት ምላሽ ሲሰጡ ይሰማል፡፡ በወዳጅም ሆነ በጠላት ስሙ almost 7/24hr እየተጠራ ቅንጣት ምላሽ ሳይሰጥ በዝ፤ታው ድባብ በስራው ላይ ብቻ አትኩሮ የሚሰራ ሰው ቢኖር ያለአንዳች ማጋነን ታላቁ እስክንድር ነጋ ብቻ እና ብቻ ነው፡፡
የታላቁን ስም ሁሉም ያነሳዋል፡፡ ከትናንሾቹ እስከ ትላልቆቹ ስሙን ያነሱታል፡፡ ትናንሾቹ ስል በእድሜ ያልበሰሉ እንቦቆቅላ ታዳጊዎቻችንን ማለቴ ሳይሆን የህይወታቸውን አብዛኛውን እድሜ ቅርጥፍ አድርገው የበሉ ከሀምሳና ከስድሳ በላይ ሆነው ግን በአሳስብ አድጎ ህጻን የሆኑትን ማለቴ ነው፡፡
ታላቁ እስክንድር ነጋ በወርሃ ሀምሌ አጋማሽ በ2022 ላይ ከአሜሪካን በመጣ ማግስት ደብዛውን አጥፍቶ ለትጥቅ ትግሉ ወደ ጫካ ከገባበት ግዜ ጀምሮ ስሙ ከጠላት ጎራ በኩል ብቻ ሳይሆን የትግል አጋርህ ነን ከሚሉት የቅርብ ሰዎችም ጭምር ስሙ ነጋ ጠባ Almost 7/24hrs በሚያስብል ደረጃ እየተነሳ ሲተች፤ሲብጠለጠልና ብሎም ሲደገፍ እነሆ ወደ ሁለተኛ አመቱ በተቃረበበት ሁኔታ ታላቁ ሰው ቅንጣት ታክል ምላሽ ሳይሰጥና አካሄዱን፤ አቌሙን ሳይቀይር የተነሳበትን ዓላማን ከግብ ለማድረስ ድምጹን አጥፍቶ ታግሎ በማታገል ላይ ያለ ልዪ ሰው ነው፡፡
የታላቁ እስክንድር ነጋ ስም ከትግል አጋሮቹ አርበኛ ዘመነ ካሴ፤አስረስ ማረ ዳምጤ፤አበበ ፈንታውን ጨምሮ በበርካታ አጋሮቹ በበጎና በትችት ነቀፌታ ስሙ እየተጠራ ሲገለጽ የሰማና ያወቀ ቢሆንም ታላቁ ሰው ግን ብቅ ብሎ በአንዳቸውም ላይ ምላሽ ያልሰጠ ሰው በመሆን ይታወቃል፡፡
ይህ አይነቱ ስብእና ከብዙዎቻችን ዘንድ ፈጽሞ የሌለ ግን ለአንድ ህዝብ የህልውና ትግል አደረጃጀት እጅግ ወሳኝ በሆነ ሁኔታ የሚያስፈልግና የሚጠቅም ልዩ ተሰጥኦ መሆኑን መገንዘብና መረዳት ያስፈልጋል፡፡ ታላቁ ሰው የአማራን ህዝብ የህልውናን ትግል በትጥቅ ለመክፈት አምኖበት ወደ ጫካ ከገባበት ወርሃ ሀምሌ 2022 ጀምሮ እስከዛሬዋ እለት ድረስ የአንዱንም ታጋይ ወንድሙን ስም ጠርቶ ምላሽ ባለመስጠት ዝምታው ሪኮርድ የሰበረ ሰው መሆኑን ስንቶቻችን እናውቃለን? ስሙ ነጋ ጠባ እየተጠራ ለድፍን ሁለት ዓመት ያህል በዝምታ ስራው ላይ ማተኮር የቻለ ከታላቁ ሰው በስተቀር ማን አለ?? ያጋነንኩ ከሆነ ስም ጥቀሱልኝ፤ ለመቀበል ልቤና ዓይኔ ክፍት ነውና እቀበላለሁ፡፡
በሪኮርድ ደረጃ በዚህ ሁለት ዓመት ሊሞላው እየተቃረበ በመጣው የታላቁ ሰው ወደ ጫካ መግባት ሂደት ውስጥ ታላቁ ሰው አንድ ግዜ ብቻ የማንንም ስም ሳይጠቅስ ለመጀመሪያ ግዜ የደም ነጋዴዎች በማለት በህልውና ትግሉ ላይ ታላቅ ተግዳሮት የፈጸሙትን ሀይሎች የገለጸበትን አገላለጽ ከመስማታችን በስተቀር ታላቁ ሰው ስለጠላት እንጂ ስለአጋር ወንድሙ ቅንጣት ያህል የክፋት ቃል የማይወጣው ሰው መሆኑን በተግባር ያረጋገጠልን ልዩ ሰው ነው ፡፡
በተለይ በተለይ እራሱን ዓለም አቀፍ የፋኖ ድጋፍ አስተባባሪ IFCC ብሎ በሚጠራው ቡድን በሶስት ሚዲያዎች (አሻራ ሚዲያ፤ ማገር ሚዲያና የ IFCC channel ) በኩል በተክሌ ይሻው፤ አቻምየለህ ታምሩ፤ሀብታሙ ተገኝ፤ጋሻው ካሴና መሰል ቡድን ከወርሀ ታህሳስ 2023 እስከ ጥር 2024 ድረስ ሰባት ተከታታይ ፕሮግራም በማዘጋጀት ታላቁ ሰው ያልዋለበትን እንደዋለ አድርገው በማስተጋባት ያለስሙ ስም ሲሰጡት የሰጠው ምላሽ በዝምታ ስራውን መስራትን ብቻ ነበር የመረጠው፡፡ ይህ ፍጹማዊ ዝምታው ግን ከአክብሮት ይልቅ ለሀሰበ ድኩማን እንጭጮችና ሰርጎ ገብ የአማራ ህዝብ ጠላቶች የልብ ልብ ሰጠና እንደ ዋን ወያኔ (ዋን አማራ) ከአማራው በላይ አማራ ነኝ ለማለት የቃጣቸው እንጭጭ ሰርጎ ገቦች (ግርማ ካሳ፤ ዘመድኩን ነቀለ) አይነት አይናቸውን በጨው ያጠቡ ደናቁርቶች ታላቁን ሰው ስሙን እያነሱ ነጋ ጠባ እንዲያብጠለጥሉት እድል የሰጠ ሆነ፡፡
ከሁሉም በላይ መቼም ሆነ መች ፈጽሞ የማንረሳው ጥቃት የተሰነዘረው በኤሊያስ ክፍሌ አዛዥነት መረጃ ቲቪ ስር በተሰበሰቡ ኮልኮሌ None AMHARA አወቅን ባይ ጥልቅ ብዬ ሰርጎ ገቦች (ዘመድኩን ነቀለ፤ ግርማ ካሳ) በኩል የተከፈተበትን ተከታታይ የስም ማጠልሻ ዘመቻን ነው፡፡ እስቲ ይታያችሁ የበረከት ስምኦን ታዛዥ የመለስ ዜናዊ አድናቂና አምላኬ የሆነው ዘመድኩን ነቀለ የሚባል እብድ ከህወሃት ኢህአዴግ እስከ ኦህዴድ ብልጽግና የተፈራረቁትን ገዢዎችን («መለስ ዜናዊ፤ ኃይለማሪያም ደሳለኝና አቢይ አህመድን) በመታገል ጽናቱ ልዪ ሪኮርድ ካለው ታላቁ ሰው ይበልጥ ለአማራ ህዝብ አዋቂና ተቆርቌሪ መስሎ ታላቁን እስክንድር ነጋን ከትግሉ ውጣና ገዳም ግባ ብሎ መዳፈርን መፈጸም የመሰል ሰቅጣጭ ድድብና ይፈጸማል ብለን ፈጽሞ ባንገምትም - ዘመድኩን ነቀለ ግርማ ካሳ ኤሊያስ ክፍሌ በታላቅ ድፍረትና ድንቁርና ጸረ እስክንድር ዘመቻ ሲከፍቱ ያየንበትን ክስተት መቼም የማንረሳው ጥቃት መሆኑን የምንገልጸው ሀቅ ነው፡፡
💥💥💥 እዚህጋ ለእውነተኛውና Conscious ለሆነው ነገደ አማራ ተወላጅ የምጠይቀው ጥያቄ ለመሆኑ ዘመድኩን ነቀለ የሚባል ዘላን እብድ ብድግ ብሎ ታላቁን ሰው ከትግል ውጣና ገዳም ግባ ብሎ ሲለፋደድ፦
📌 1ኛ - እንዴት አንድ በጀርመን ያለ None AMHARA በሀገር ውስጥ ህይወቱን ለመስዋእትነት ሰጥቶ የሚታገልን ታጋይ ከትግሉ ወጥተህ ከፈለግክ ገዳም ካልሆነም ወደ ዲሲ ተጔዝ ልትል የቻልከው ብላችሁ ያላፋጠጣችሁት ???
📌 2ኛ - በምን ስሌትና ሎጂክ ነው አንድ ምትክ የለሽ ብርቅዬ ህይወቱ እንደሚሰዋ እያወቀ ግን ከነገደ አማራ ህልውና አይበልጥም ብሎ ታግሎ በማታገል ሂደት ውስጥ ሊከሰት የሚችልን የህይወት መስዋእትነትን ለመቀበል ወስኖ ጫካ የገባን ብርቅዬን የአማራን ልጅ አንድ ጀርመን የተጎለተ እብድ ኦሮሞ (ዘመድኩን ነቀለ ) እና አሜሪካን የተጎለተ ማንነት የለሹ ባዶ እራስ (ግርማ ካሳ) ጫካ ውስጥ ሆኖ ከሚታገለው አማራ ወገንህ (ታላቁ እስክንድር) በልጦብህ ዘመዴ ያለው እውነት ነው፡ እስክንድር ወጥቶ መልስ ይስጥበት እያልክ ልታስተጋባ የቻልከው ???
ወንድ ሆንክ ሴት፤ ወጣት ሆንክ አዛውንት፤ ምሁር ሆንክ መሀይም ለአንተ/ቺ ነገዳዊ ህልውና እና ነጻነት ብሎ ታግሎ ለማታገል ጫካ የገባን ታላቁን እስክንድር ይልቅ ይህ ወፍ ዘራሽ የሆነው ዘመድኩን፤ግርማና ኤሊያስ ክፍሌ በልጠውብህ ያወናበዱህ ሁሉ Shame on You ልንልህ እንወዳለን፡፡ አንተ አማራ ነኝ እያልክ ከመሪህ ታላቁ ሰው ይልቅ ሊመራህ የማይችለውንና ሊመራህ የማይገባውን ኦሮሞውን ዘመዴን እና ግርማ ተብዬውን የቅናት ሴራን ወሬ ተከትለህ የምትወዛገብ ካለህ Shame on You አንተ ተወልጃለሁ ብትልም ያልተፈጠርክ መናፍስት መሆንህን ልንገልጽልህ እንወዳለን፡፡ በሀገር ውስጥ ሆኖ ዋጋ እየከፈለ ያለውን እውነተኛን አማራ፤ ጀርመንና አሜሪካን ከተጎለተ ኢሮሞ ተወላጅ (ዘመድኩንና ግርማ) አሳንሰህ ለኦሮሞዎቹ ጩህት ልብና ጆሮህን በመስጠት ዘመዴ ለአማራ አስቦ ነው፤ ግርማ ለአማራ አስቦ ነው የምትል ሰው ነኝ ባይ አማራ ካለህ ቁርጥህን እወቅ አንተ/ቺ ሰው መሳይ መናፍስት የእንግዴ ልጅ ናችሁ፡፡
በዚህ ሰአት የነገደ አማራ ተወላጅ ሆኖ የኦሮሞው ዘመድኩን በቀለ ግርማ ካሳ ኤሊያስ ክፍሌና መረጃ ቲቪ ደጋፊና ተከታይ የሆነ ሰው ካለ እውነት እውነት እላለሁ አማራ መባሉ ይቅርና Councsiou የሆነ የሰው ልጅ ነው የማይባል - ወዳጅና ጠላቱን የማያውቅ ( ልክ እንደ በግ፤ፍየል፤ዶሮና ላም) ከጠላቱ ጋር የሚኖርና ጠላቱን የሚያገለግል እንሥሳ መሆኑን ይወቅ፡፡
አንድ Councsiou ነኝ የሚል አማራ ነኝ ባይ በምንም ዓይነት ተአምርና ሎጂክ ለነገደ አማራ ህዝብ ሁለንተናዊ ነጻነትና ሁለንተናዊ ህልውና ብሎ ጫካ ውስጥ እየታገለ ያለን እውነተኛን አማራ (ታላቁ እስክንድር ነጋን) በአንድ ለአማራው ከአማራው በላይ አውቅልሀለሁ ባይ ብልጣብልጥ ኦሮሞ ጩህትና ልፈፋ ተደነባብሮ ዘመዴ ያለው እውነት ይሆን ብሎ ፈጽሞ አይወዛገብም፡፡ ለእኔ ለአማራው የሚቀርበው ማን ነው ??
ለእኔ ብሎ ጫካ ውስጥ እየታገለ ያለው እውነተኛው አማራ (ታላቁ እስክንድር ) ነው ወይንስ አማራ ሳይሆን ከአማራ በላይ አማራ ነኝ በማለት ጀርመንና አሜሪካን ቁጭ ብሎ በአማራ ስም የሚነግደውን ዘመዴ፤ኤሊያስ፤ግርማ እና በዲያስፖራ የብ ዓዴን ክንፍ የሚባለው ቡድን ነው ?
ወርቅን ያየ ሁሉ ወርቅነቱን አያውቅም፡፡ ወርቅን ከብረት ወይም ከነሀስ ለይቶ የሚያውቀው ወርቅን ያወቀ ብቻ ነው፡፡
እኛ ወርቆቻችንን እና ብርቆቻችን ወርቅነት ለማወቅ መጀመሪያ እኛ ወርቅን ከብረት ለይተን የምናውቅ መሆን ይገባናል፡፡ ወርቅና ቆርቆሮ እኩል ለሚመስለው ደንቆሮ በታላቁ እስክንድር እና በሀሳበ ድኩማኖቹ ኦሮሞዎች (ዘመድኩንና መሰሎቹ) መካከል ልዩነት መኖሩን ማወቅ ባለመቻል ከእስክንድር ይልቅ ኦሮሞው ዘመድኩን ለአማራው አስቦ ነው በሚል ድንቁርናዊ አመክኒዮ አማራ ሆኖ ለዘመዴ ዘላናዊ ጩህት ልብና ጆሮውን የሚሰጥ ሆኖ እናገኛለን፡፡
ለመሆኑ ታላቁ ሰው ለምንድነው ይህንን ያህል መስዋእትነት ለአማራው እየከፈለ እራሱን በዝምታ የሸበበውን?? አማራ ነኝ የሚለውስ ለምንድነው ይህንን የታላቁን ሰው ታላቅ መስዋእትነትን ማወቅና መረዳት ያልቻለው??
ለመሆኑ የአማራን ህዝብ አንድነት ለመጠበቅ ታላቁ ሰው የፈጸማቸው ወሳኝ ተግባራት ምንድናቸው ?? ለምሳሌ የአማራ ፋኖ ህዝባዊ ሰራዊት ምስረታን በተመለከተ የታላቁ ሰው አቌም ድርሻና ሚና ምን ነበር??
ቆማጣን ቆማጣ ነህ ካላሉት ልፈትፍት ይላል፡፡
የታላቁ ሰው ዝምታ ለወፍ ዘራሾቹ የልብ ልብ በመስጠት እንደፈለጉ እንዲጨማለቁ አድርጔል፡፡ እናም ጋሻ ሚዲያ በተለየ ሁኔታ ለአማራ ህዝብ አንድነት ተብሎ በታላቁ ሰው የተፈጸመንና እየተፈጸመም ያለን ታላቅ ስራን የማቅረቡን ጉዳይ ክፍል አንድን እነሆ ዛሬ ማቅረቡን እየገለጸ በቀጣይ የዛሬውን ጥያቄ መልስን ጨምሮ እስከዛሬ ያልተገለጹ ተጋድሎዎችን በተከታታይ የምናቀርብ መሆኑን በመግለጽ የዛሬውን መጣጥፍ ስንደመድም - በጫካ እየታገለ ካለው እውነተኛው አማራ ይልቅ በጀርመንና አሜሪካ ያለው ኦሮሞ ለአማራው ያውቃል፤ ይቆረቆራል የሚል ካል እሱ/ሧ በቁም ያሉ የበከቱ ምውታን መሆናቸውን እንዲያውቁ በመግለጽ ነውና በቀጣይ እስከምንገናኝ ቸር እንሰንብት፤ አበቃሁ ፡፡
++++++++++++++***+++
👉 Join Us
💥 Gasha Media Discussion Forum
📌https://chat.whatsapp.com/CWRh7ScRFcs3mAhpSMwQFN
📌 https://t.me/GMMediad