Ethiopian Community Jeddah. በጅዳ የኢትዮጵያውያን ኮሚኒቲ

Ethiopian Community Jeddah. በጅዳ የኢትዮጵያውያን ኮሚኒቲ Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Ethiopian Community Jeddah. በጅዳ የኢትዮጵያውያን ኮሚኒቲ, Community Center, Jeddah, Saudi Arabiya, Jeddah.

26/06/2026

መልካም ዜና ለኢትዮጵያዊያን በሙሉ ወ/ሪት ለይላ ኑርሰቦ ረዲ ከእስር ተፈትተው ወደ አገራቸው እንዲመለሱ ተወሰነ፣
=========================
(ሪያድ ፣ ሰኔ 19 ቀን 2018 ዓ.ም) ወ/ሪት ለይላ ኑርሶቦ ረዲ የተባሉ ዜጋችን ከዛሬ 13 ዓመት በፊት ወደ ሳዑዲ አረቢያ ለስራ የመጡ ሲሆን የሰው ህይወት በማጥፋት ወንጀል ተከሰው በክስ ቻርጅ ቁጥር 13456902511 በሳኡዲ አረቢያ የሪያድ ከፍተኛ ፍ/ቤት ጥፋተኛ ናቸው በሚል በሞት እንዲቀጡ የፍርድ ውሳኔ አስተላልፎ እንደነበር ይታወሳል።

በወቅቱ ዜጋችን ለስራ ከአገር ወጥተው በሰራተኝነት እያገለገሉ በነበሩበት ሁኔታ ከላይ የተጠቀሰው አደጋ ማጋጠሙ የመላ ኢትዮጵያዊያንን ልብ የሰበረ ነበር። ከዚህ በመነሳት ኤምባሲያችን ለጉዳዩ ትኩረት በመስጠት በእርቅ እንዲፈታ ከቤተሰባቸውና ከማህበረሰቡ የተውጣጣ ኮሚቴዎችን እንዲቋቋሙ በማድረግ፣ ጉዳዩን በማስተባበር ከፍተኛ የዲፕሎማሲ ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል።

በዚሁ መሠረት የተደረገው ሰፊ የዲፕሎማሲ ጥረት ፊሬ አፍርቶ ለተጎጂ ቤተሰብ የገንዘብ ካሣ በመክፈል ምህረት እንዲያገኙና ተወሰኖባቸው የነበረው የሞት ፍርድ ተነስቶላቸው ለአገራቸው እንዲበቁ በመወሰኑ እንኳን ደስ አላችሁ፣ እንኳን ደስ አለን።

በዚህ አጋጣሚ ይህ ውጤት እንዲገኝ የተጎጂ ቤተሰቦችን በመካስ የዜጋችን ህይወት ለማትረፍ የተረባረባችሁ ኢትዮጵያዊያን በተለይም በሪያድ የምትገኙ የኮሚቴ አባላት፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ የኃይማኖት አባቶች፣ የዜጋችንን ጉዳይ እንደራሳችሁ ጉዳይ ወስዳችሁ ቀን እና ሌሊት የደከማችሁ ወገኖቻችን፣ ለወገናችን ድምፅ በመሆንና ገንዘብ በማሰባሰብ እገዛ ያደረጋችሁ የሚዲያ ባለቤቶች፣ አገር ቤት ከህዝብ የተሰበሰበውን ገንዘብ በውጭ ምንዛሪ ተቀይሮ ለካሳ ክፍያው እንዲውል ለረዱን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አመራሮችና ሠራተኞች፣ እንዲሁም ይህ ውጤት እንዲገኝ ድጋፍ ላደረጉልን የሳዑዲ መንግስት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የስራ ሃላፊዎችና የፍትህ አካላት እንዲሁም በተለያየ መንገድ አስተዋፅኦ ለባረከታችሁ በሙሉ ኤምባሲው ከፍተኛ ምስጋና ያቀርባል።

በተመሳሳይ መልኩ በተለያዩ ወንጀሎች ክስ ተመስርቶባቸው በእስር ላይ የነበሩ 1665 ዜጎቻችንን ሚሲዮናችንና የጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤታችን ባደረጉት ሰፊ ዲፕሎማሲያዊ ጥረት የክስ ሂደታቸዉ ተቋርጦ ወደ አገራቸዉ እንዲመለሱ መደረጉ ይታወሳል። ይህ የሁለቱ አገሮች ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነትና ትብብር እየተጠናከረ ለመምጣቱ አንድ ማሳያ ነው።

በዚህ አጋጣሚም ዜጎቻችን ወደ ሳዑዲ አረቢያ ለስራ መምጣት ፍላጎት ካላችሁ በሁለቱ ሀገራት እየተተገበረ የሚገኘውን ህጋዊን የስራ ሰምሪት ተከትላችሁ እንዲትመጡ፣ በተሰማራችሁበት ቦታ ሁሉ የአገሩን ህግ አክብራችሁ እንድትሰሩ፣ አስቸጋሪ ሁኔታ ካጋጠማችሁ እንኳን መብታችሁን በህጋዊ መንገድ ብቻ በማስከበር ከእንዲህ ዓይነቱ አስቸጋሪ ሁኔታዎች ራሳችሁን እንድትጠብቁ ኤምባሲው ይመክራል።

ምንጭ:- የኢትዮጵያ ኢምባሲ ሪያድ

26/06/2026

በጅዛን የኢትዮጵያ ኮሙኒቲ ማህበር የማጠናከር ሥራ ተከናወነ

(ሰኔ 18 ቀን 2018 ዓ.ም) በጄዳ የኢፌዲሪ ቆንስል ጄነራል ክቡር አምባሳደር ጣፋ ቱሉ የተመራ ቡድን በጅዛን የኢትዮጵያ ኮሙኒቲ ማህበርን የማጠናከር ሥራ አከናውኗል፡፡ በፕሮግራሙ ላይ ክቡር አምባሳደር ጣፋ ቱሉ ባደረጉት ንግግር በጅዛን አካባቢ በርካታ ኢትዮጵያዊያን ዳያስፖራዎች ከመኖራቸውም በላይ ቦታው በአብዛኛው ዜጎቻችን ወደ ሳዑዲ አረቢያ የሚገቡበት እና ለተለያዩ ችግሮች የሚጋለጡበት ቦታ በመሆኑ ልዩ ትኩረት የሚሻ ስትራቴጂያዊ የሳኡዲ አረቢያ ግዛት እንደሆነ አስገንዝበዋል፡፡ አምባሳደሩ አክለውም ነባሩ የጅዛን ኮሚዩኒቲ አማራሮች ለነበራቸው ከፍተኛ የማህበረሰብ አገልግሎት በማመስገን በአሁኑ ወቅት መጠነኛ የሥራ ኃላፊነት ሽግሽግ በማድረግ የበለጠ ማጠናከር ማስፈለጉን አስረድተዋል፡።
ክቡር አምባሳደር ጣፋ ቱሉ አያይዘውም ለጅዛን ኮሙኒቲ ለቀጣይ የሥራ ዘመን በአዲስ መልክ በተዘጋጀው የመተዳደሪያ ደንብ መሠረት የሥራ ክፍፍል ማድረግ እንደሚያስፈልግ አብራርተዋል፡፡
የኮሚዩኒቲ አመራሮቹም የተካሄደው ማህበሩን የማጠናከር ሥራ በአዎንታ እንደሚቀበሉት በመግለጽ ማህበረሰቡን በተሻለ አቅም ለማገልገል ዝግጁነታቸውን ገልጸዋል፡፡
በመጨረሻም ክቡር አምባሳደር ጣፋ ቱሉ በአዲስ መልክ የተዋቀረው የሥራ አስፈጻሚ አንድነቱን እና ጥንካሬውን እንደያዘ እንዲቀጥል በማሳሰብ ለማህበረሰብ አመራሮቹ የስራ መመሪያ በመስጠት በአዲስ መልክ በሚያዘጋጁት የኮሙኒቲ መተዳደሪያ ደንብ መሠረት ወደ ሥራ እንዲገቡ አሳስበዋል፡፡

በሳዑዲ አረቢያ በአንጋፋው በጅዳ ኢትዮጵያዊያን ኮሚኒቲ ማህበር የተመሠረተው ለበርካታ አመታት በኮሚኒቲ አሥተዳደር ሥር ሲመራ የቆየውና የኮሚኒቲው ማህበረሰብ የአመታት ጥረት እና ዘመን ተሻጋሪ...
25/06/2026

በሳዑዲ አረቢያ በአንጋፋው በጅዳ ኢትዮጵያዊያን ኮሚኒቲ ማህበር የተመሠረተው ለበርካታ አመታት በኮሚኒቲ አሥተዳደር ሥር ሲመራ የቆየውና የኮሚኒቲው ማህበረሰብ የአመታት ጥረት እና ዘመን ተሻጋሪ ቅርስ ተደርጎ የሚታመነው ከቅርብ አመታት ወዲህ የአስተዳደር አወቃቀሩን በመቀየር በቦርድ እንዲመራ የተደረገዉ የኢትዮጵያ አለም አቀፍ ት/ቤት ሰኔ 17 ቀን 2018(Jun 24 2026) ለ16ኛ ግዜ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የማጠናቀቂያ ፕሮግራም በደመቀ ሥነ-ሥርዓት ተከበረ።
በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ በጅዳ የኢፌዲሪ ቆንሲል ጀኔራል ጽ/ቤት አስተዳደር እና ዲፕሎማቶች የት/ቤቱ አስተዳደርና መምህራን የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ አመራሮች የት/ቤቱ ቦርድ አመራር የተመራቂ ተማሪዎች ወላጅና ጥሪ የደረገላቸው እንግዶች በመገኘት የተማሪዎቹን ስኬት አክብሯል።
በዕለቱ የክብር እንግዳ በጅዳ ቆንሲል ጀኔራል ጽ/ቤት ም/ቆንሲል ጀኔራል የሆኑት ክቡር አቶ ለዓለም ጥላሁን ባደረጉት ንግግር የዛሬ ተመራቂ ተማሪዎች ለዚህ ደረጃ ለመድረስ ያሳዩት ፅናት፣ ትጋት፣ቁርጠኝነትን በማድነቅ ዛሬ የደረሱበት የመጨረሻ ሳይሆን ወደ ፊት በከፍተኛ ትምህርታቸው እና በሙያ ህይዎታቸው የበለጠ ስኬት እነዲያስመዘግቡ ምኞታቸውን ገልፀው የጅዳ ኢትዮጵያ አለም አቀፍ ት/ቤት ከሪያድ እና ጅቡቲ ት/ቤት ልምድ በመቅሰም የራሱ የሆነ ት/ቤት እንዲኖረው ለማስቻል እንቅስቃሴ መጀመሩን አብስሯል።
በመጨረሻም ለተመራቂ ተማሪዎች የምስክር ወረቀት ተሰጥቶ የማስታወሻ ፎቶ ግራፍ በመነሳት የዕለቱ መርሃ ግብርማብቂያ ሆኗል።

10/06/2026

“ኢትዮጵያ መርጣለች፤ ኢትዮጵያ ተመርጣለች፤ ኢትዮጵያ አሸንፋለች”

(ግንቦት 30 ቀን 2018 ዓ.ም፤ ጄዳ) 7ኛው አገራዊ ምርጫ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁን በማስመልከት በጄዳ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ቆንስላ ጀኔራል ጽሕፈት ቤት የምስጋና ምሽት ተካሄደ። በፕሮግራሙ ላይ በጄዳና አካባቢው የሚኖሩ የዲያስፖራ ማህበረሰብ አባላት፣ የኮሙኒቲ መሪዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታድመዋል።
በፕሮግራሙ መክፈቻ ላይ በጄዳ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ቆንስል ጀኔራል ክቡር አምባሳደር ጣፋ ቱሉ ባደረጉት ንግግር “ኢትዮጵያ መርጣለች፤ ኢትዮጵያ ተመርጣለች፤ ኢትዮጵያ አሸንፋለች” በማለት 7ኛው አገራዊ ምርጫ በሰላማዊና በዴሞክራሲያዊ ሁኔታ መጠናቀቁ የመላው ኢትዮጵያ ሕዝብ ድል መሆኑን ገልጸዋል። ምርጫው ከመካሄዱ በፊትም ሆነ በሂደቱ ወቅት የተፈጠሩ ውስጣዊና ውጫዊ ፈተናዎችን በሰላማዊ መንገድ በማለፍ የኢትዮጵያ ሕዝብ ለአንድነት፣ ለሰላም እና ለዴሞክራሲያዊ ሂደት ያለውን ጽኑ ቁርጠኝነት በተግባር ማረጋገጡን አስታውቀዋል። በተጨማሪም በውጭ የሚኖረው የዲያስፖራ ማህበረሰብ በምርጫው ሂደት ውስጥ እያበረከተ ያለውን አስተዋጽኦ በማድነቅ፣ የተገኘው ስኬት ለሀገራችን ሰላም፣ ልማት እና ብልጽግና የበለጠ በጋራ ለመስራት አዲስ እድል የፈጠረ መሆኑን ገልጸዋል።

በማስከተልም በ7ኛው አጠቃላይ ሀገራዊ ምርጫ በስኬት መጠናቀቁን አስመልክቶ በጅዳ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ቆንስላ ጀኔራል ጽ/ቤት የዳያስፖራ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ክፍል ኃላፊ አቶ ለዓለም ጥላሁን ባቀረቡት ገለፃ ላይ ተመስርቶ ውይይት ተደርጓል። በገለጻው ላይ ከቅድመ-ምርጫ ዝግጅት ጀምሮ ምርጫው ነፃ፣ ፍትሃዊ፣ ዴሞክራሲያዊ፣ አካታች እና ተአማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ በመንግስት በኩል ያላሰለሰ ጥረት መደረጉን አብራርተዋል። የድህረ-ምርጫ ምልከታን በተመለከተ ከሀገር ውስጥ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ምርጫው "ሰላማዊ፣ ዲሞክራሲያዊ እና የሰብዓዊ መብት ጥሰት ያልተፈጸመበት መሆኑን" ማረጋገጡን እንዲሁም "ዓለም አቀፍ መስፈርቶችን ያሟላ፣ አሳታፊና አካታች መሆኑን" መግለጹን አብራርተዋል። በተመሳሳይ የአፍሪካ ህብረት ታዛቢ ቡድን መሪ ምርጫው "ዲሞክራሲያዊ አስተዳደርን በሰፊው በሚደግፍ ሕጋዊና ተቋማዊ ማዕቀፍ ውስጥ የተካሄደ” በሚል ማድነቁን እንዲሁም የኢጋድ ታዛቢ ቡድን መሪ በበኩላቸው ምርጫው "አካታች እንደነበረ ማረጋገጣቸውን" አስረድተዋል። በገለፃው ማጠቃለያ ላይ ምርጫው በስኬት መካሄዱን ተከትሎ ሰላማዊ ትግሉን ከዳር በማድረስ የሀገራችንን ብልጽግና ለማረጋገጥ እየተደረገ ባለው ጥረት በጅዳና አካባቢው የሚገኘው የዳያስፖራ ማህበረሰብ የበኩሉን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል። በገለጻው ላይ ተመስርቶ በተደረገው ውይይት ሰላማዊ ትግሉን ወደፊት ለማስኬድ ዳያስፖራው የሚጠበቅበትን ለመወጣት ዝግጁ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፣ ምርጫው በስኬት መጠናቀቁን በማስመልከት ፕሮግራሙ በመዘጋጀቱ ምስጋና አቅርበዋል።

08/06/2026

‎በሳዑዲ ዓረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ያሉ 1 ሺህ 722 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመለሱ።
‎*************
‎(አዲስ አበባ፣ ግንቦት30 / 2018 ዓ.ም) በሳዑዲ ዓረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 1 ሺህ 722 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል፡፡

‎በሳምንቱ ውስጥ በተደረገ 10 ዙር በረራ የተመለሱት 1ሺህ 666 ወንዶች እና 48 ሴቶች እንዲሁም 8 ህፃናት ሲሆኑ ከነዚህ ውስጥ 27 ተመላሾች ደግሞ እድሜያቸው ከአስራ ስምንት አመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች ይገኙበታል።

‎መስከረም 5/ 2018 በተጀመረው ዜጎችን ወደ ሀገር ቤት የመመለስ ስራ እስካሁን ከ77 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያንን ወደ ሀገር መመለስ ተችሏል።

‎ሚኒስቴሩ ለተመላሽ ዜጎች በአየር ማረፊያና በማቆያ ማዕከላት ተገቢውን ድጋፍ እና እንክብካቤ የማድረግ እና ከቤተሰብ ጋር የማቀላቀል ስራ ከሚመለከታቸው ባለድርሻና አጋር አካላት ጋር በመተባበር በትኩረት እየሰራ ይገኛል።

‎በተጨማሪም መደበኛ ባልሆነ ፍልሰት ወደ ተለያዩ ሀገራት ሄደው የሚመለሱ የፍልሰት ተጎጂዎችን ለመደገፍና መልሶ ለማቋቋም የሚያስችሉ ተግባራትን በትብብር እያከናወነ መሆኑ ይታወቃል።

‎ወደፊትም በህገወጥ የሰዎች ዝውውር አስከፊነት ዙሪያ ህብረተሰቡን ለማስገንዘብ፣ መደበኛ ያልሆነ ፍልሰትን ለመከላከልና ደህንነቱ የተጠበቀ ፍልሰትን ለማበረታታት ሚኒስቴሩ የጀመራቸውን ስራዎች አጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል።

23/05/2026

ማስታወቂያ
ለመላዉ የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለኢድ አል- አድሀ (አረፋ)በዓል አደረሳችሁ እያልን በዓሉን ምክንያት በማድረግ ከግንቦት 14ቀን 2018(may 22,2026)እስከ ግንቦት 24ቀን 2018(june 01,2026) በጅዳ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ጽ/ቤታችን ዝግ ሆኖ የምቆይ መሆኑን እየገለፅን ማክሰኞ ግንቦት 25 ቀን 2018(june 2,2026)በተለመደው የሥራ ሰዓት አገልግሎት የምንሰጥ መሆኑን በአክብሮት እንገልፃለን።
ከኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ጽ/ቤት
ጅዳ

Beeksisa
Hordoftoota amanttaa muslimootaa hundaaf baga ayyaana id al- adaha(arafattin) isin gahe jechaa ayyaanicha sababeeffachun caamsaa guyyaa 14,2018(may 22,2026)irraa Eegalee hanga wiixata caamsaa Guyyaa24,2018(june 01,2026) tti waajjri cominitii itoophiyaa keenya cufaa ta'uu isaa isiniif ibsaa kiibxata caamsaa gaafa guyyaa 25,2018(june 02,2026)irra jalqabee sa'aatii hojii keengatti tajaajila idilee kan jalqabnu ta'uu kabajaan isin beeksifna
Waajjira kominitii itoophiyaa jiddah

ግንቦት 13/2018 ዓ/ምበጅዳ የኢትዮጵያ ቆንስላ ፅ/ቤት በተደረገ የህፃናት ሊሴፓሴ አገልግሎት የጅዳ ማህበረሰብ ኮሚኒቲ 10ኛ ምክር ቤት ስራ አስፈፃሚ እና የኮሚኒቲ ሠራተኞች እንዲሁም የቆ...
21/05/2026

ግንቦት 13/2018 ዓ/ም
በጅዳ የኢትዮጵያ ቆንስላ ፅ/ቤት በተደረገ የህፃናት ሊሴፓሴ አገልግሎት የጅዳ ማህበረሰብ ኮሚኒቲ 10ኛ ምክር ቤት ስራ አስፈፃሚ እና የኮሚኒቲ ሠራተኞች እንዲሁም የቆንሲላ ድፕሎማቶች ለ 355 የአገልግሎት ፈላጊዎች የተፋጠነ አገልግሎት በመስጠት ላይ ውሏል።
በዚህም ዜጎቻችን ፈጣን አገልግሎት ማግኘት ችሏል።
ለቀጣይ ዜጎቻችን በሚሰጠው ተመሳሳይ አገልግሎት ለመስተናገድ ሲመጡ በግልፅ የሚነበብ መታወቅያና የአባት የጉዞ ማስረጃ( ሰነድ) ይዘው እንዲቀርቡ ለማሳሰብ እንወዳለን።
የጅዳ ማህበረሰብ ኮሚኒቲ
ፅ/ቤት

10/05/2026

Address

Jeddah, Saudi Arabiya
Jeddah

Opening Hours

Monday 8am - 3pm
Tuesday 8am - 3pm
Wednesday 8am - 3pm
Thursday 8am - 3pm
Sunday 8am - 3pm

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Community Jeddah. በጅዳ የኢትዮጵያውያን ኮሚኒቲ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share