Ethiopian Children in Lebanon

Ethiopian Children in Lebanon ይህ በቤሩት ሊባኖስ ያሉ ልጆች ከዘር ከፖሎቲቃ እና ከእምነ�

30/04/2026

ክብርት ከንቲባ፣

ቅጠል ተራን ወደ ዘመናዊ የመኖርያ ቦታነት ለመቀየር መታሰቡ መልካም ነው፣ እነዚህ በቦታው ይኖሩ የነበሩ በኩራዝ እና ሻማ ይጠቀሙ የነበሩ እጅግ የከፋ ድህነት ውስጥ የነበሩ ዜጎች መሄጃቸውስ የት ነው?

ቅጠል ሸጠው የሚኖሩ ዜጎች መቼም ቅንጡ ቤቱ እንደማይደርሳቸው ግልፅ ነው፣ ዛሬ የተጋራው መረጃ ላይ ስለ ነባር ነዋሪዎቹ መዳረሻ የተባለ የለም። እጣ ፈንታቸው እንደሌሎቹ ትራንስፖርት እንኳን የሌለበት ከከተማ ርቆ ወጥቶ የባሰ ድህነት ውስጥ መግባት ወይስ ሌላ የታሰበ ነገር አለ?

12/04/2026
ኽያውን ከሙታን መካከል ስለምን ትፈልጋላችሁ?" እንደ ተናገረ ተነሥቶአልና በዚህ የለም "              ማቴ.28:6)    እንኳን 2018 ለብርሃነ ትንሳኤው በሰላም አደረሳችሁEthio...
12/04/2026

ኽያውን ከሙታን መካከል ስለምን ትፈልጋላችሁ?

" እንደ ተናገረ ተነሥቶአልና በዚህ የለም " ማቴ.28:6)
እንኳን 2018 ለብርሃነ ትንሳኤው በሰላም አደረሳችሁ
Ethiopian Children in Lebanon

ክርስቶስ በታላቅ ሃይሉና ሥልጣኑ ከሙታን መካከል ተለይቶ ተነሳ፤
ሰይጣንን አሰረው፤ አዳምን ነፃ አወጣው፤
ከእንግዲህ ወዲህ ፍሰሃ፣ ሰላም፣ ደስታ ሆነ።

እንኳን ለጌታችንና መድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ ትንሣኤ በሰላምና በጤና አደረሰን: አደረሳችሁ።

የሰላም የፍቅርና የበረከት በዓል ያድርግልን : አሜን!!!

130ኛው የአድዋ ድል በዓል በቤይሩት በድምቀት ተከበረ፤ Ethiopian Children in Lebanon Haregeweyn Dady Mulugeta ============================1...
02/03/2026

130ኛው የአድዋ ድል በዓል በቤይሩት በድምቀት ተከበረ፤ Ethiopian Children in Lebanon Haregeweyn Dady Mulugeta
============================
130ኛው የአድዋ ድል በዓል በቤይሩት የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ቆንስላ ጄኔራል ጽ/ቤት በድምቀት ተከበረ፡፡ “ #ከአኩሪታሪክወደብሩህአድማስ” በሚል መሪ ቃል በተከበረው በዓል ላይ በቤይሩት የኢፌዴሪ ቆንሱል ጀነራል ክቡር አምባሳደር አቶ ጌታቸው ረዳ ኡቶ ጨምሮ የሀይማኖት አባቶች፣ በሊባኖስ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ማህበር አመራሮችና የምክር ቤት አባላት፣ የተለያዩ የዲያስፖራ ማህበራት ፣ የቆንስላ ጄኔራል እና የኮሚዩኒቲ ማኅበር ሰራተኞች፣ ኢትዮጵያውያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች በተለያየ ባህላዊ ልብስ አሸብርቀው በተገኙበት በድምቀት ተከብሯል፡፡
በእለቱ የተለያዩ አድዋን የሚዘክሩ ፎቶዎች፣ ባህላዊ ሙዚቃዎች፣ ትዕይንቶች እና ግጥሞች @የኢትዮጽያን ልጆች በሊባኖስ ቤሩት ተማሪዎች በዳያስፓራ አባላት የቀረቡ ሲሆን በዚሁ በዓሉ ድምቀቱን እንደጠበቀ ተጠናቋል፡፡

10/02/2026

ልዩ የበረዶ ጉዞ የፊታችን እሁድ በኢትዮጵያ ልጆች አዘጋጅነት
15/2/2026 ደርሶ መልስ 10$ ብቻ
ባታ ለመያዝ 76 152 264

07/12/2025

20ኛው የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል በቤይሩት የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ቆንስላ ጄነራል ጽ/ቤት በድምቀት ተከበረ፤
= = = = = = = = = = = = = = = = = = = = = = =
(ህዳር 28 ቀን 2018 ዓ.ም- ቤይሩት) 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል በቤይሩት የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ቆንስላ ጄነራል ጽ/ቤት በድምቀት ተከበረ፡፡ “ዲሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ-ብሄራዊ አንድነት” በሚል መሪ ቃል በተከበረው በዓል የሀይማኖት አባቶች፣ ኮሚኒቲ ማህበራት፣ የዳያስፖራ አደረጃጀቶች፣ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን እንዲሁም የኢትዮጵያ ወዳጆች በተለያየ ባህል ልብስ አሸብርቀው በተገኙበት ተከብሯል፡:

በዓሉ በአባቶች ምርቃት ከተከፈተ በኋላ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የቆንስላ ጄነራል ፅ/ቤት ጉዳይ ፈፃሚና የዳያስፓራ ዘርፍ ሀላፊ አቶ ጌታቸው ኡታ በመልዕክታቸው ኢትዮጵያ የተለያዩ ብሔሮች እና ብሔረሰቦች፣ ቋንቋዎች፣ ባህሎች፣ እምነቶች…ወዘተ ያሉባት የብዝኃነት ቤት እንደሆነች ጠቅሰው የአገራችንን ብዝኃነት ለማስተዳደር፣ ኅብረ-ብሔራዊ አንድነትን ለማጠናከርና የሀገረ-መንግስት ግንባታን ስኬታማ ለማድረግ ከተሠሩ ሥራዎች ዋናው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች መብቶች መከበር ዋስትና የሰጠው የኢፌዴሪ ሕገ-መንግስት ህዳር 29 ቀን 1987 ዓ.ም መጽደቁ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ በማያያዝም ሕገ-መንግስቱ የፀደቀበት ቀን “የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን” ሆኖ ከ1999 ዓ.ም ጀምሮ ላለፉት 19 ዓመታት መከበሩ በአገራችን ሕዝቦች መካከል የበለጠ መቀራረብ፣ መተዋወቅና አንዱ ከአንዱ የሚማማርበት እድል በማስፋት፣ የብዝሃነት አያያዝና የዲሞክራሲ ባህል በማዳበርና ሀገራዊ አንድነትን በማጠናከር ረገድ ከፍተኛ ሚና እንደተጫወተ አስገንዝበዋል፡፡

20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን “ዲሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ-ብሄራዊ አንድነት” በሚል መሪ እየተከበረ እንደሆነ ጠቅሰው መሪ ቃሉ ከብዝኃነታችን አንጻር በውሳኔ አሰጣጥ ሰፊ ተሳትፎን፣ የህዳጣን/አናሳ ውክልናን፣ አካታችነትን፣ አቃፊነትን፣ ድርድርና የጋራ ስምምነት በማስፋት ዜጎች በአገራዊ ጉዳዮች የጋራ ኃላፊነት እንዲሰማቸው በማድረግ ለሕብረ-ብሔራዊ አንድነትና ለአገረ-መንግስት ግንባታ አስተዋጽኦ የሚያበረክተውን የመግባባት ዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዳበርን የሚጠይቅ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡ በሊባኖስ የሚኖረውን የኢትዮጵያ ማህበረሰብ ለአገር ልማት፣ ለወገን ድጋፍና ለቤተሰብ ሕይወት መሻሻል ለጋሽ በመሆን የአብሮነት፣ የአንድነት፣ የመተሳሰብና የመደጋገፍ ተምሳሌት እንደሆነ በመግለጽ ይኸው ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል፡፡ በመጨረሻም ጳጉሜ 2 የኅብር ቀን በሚል የተካሄደው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ምርቃት ዝግጅት እንዲሳካ አስተዋፅኦ ላደረጉ አካላት የምስጋና የምስክር ወረቀት አበርክተዋል፡፡

በዕለቱ የሕጻናት መዝሙርና ግጥም፣ በአዋቂዎች በቀረቡ ግጥሞች፣ የሀገራችንን ብዝኃነትና የልማት ስራዎች የሚያሳይ ቪዲዮ፣ የኢትዮጵያ ቡና አፈላል ስነ- ስርዓት፣ የተለያዩ የብሔር፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች የሚወክሉ ሙዚቃዎችና ውዝዋዜ በመሳሰሉ ኩነቶች በዓሉ በድምቀት ተከብሮ ተጠናቋል፡፡

07/12/2025
20ኛው የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል በቤይሩት የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ቆንስላ ጄነራል ጽ/ቤት በድምቀት ተከበረ፤= = = = = = = = = = = = = = = = = = = = = = =...
07/12/2025

20ኛው የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል በቤይሩት የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ቆንስላ ጄነራል ጽ/ቤት በድምቀት ተከበረ፤
= = = = = = = = = = = = = = = = = = = = = = =
(ህዳር 28 ቀን 2018 ዓ.ም- ቤይሩት) 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል በቤይሩት የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ቆንስላ ጄነራል ጽ/ቤት በድምቀት ተከበረ፡፡ “ዲሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ-ብሄራዊ አንድነት” በሚል መሪ ቃል በተከበረው በዓል የሀይማኖት አባቶች፣ ኮሚኒቲ ማህበራት፣ የዳያስፖራ አደረጃጀቶች፣ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን እንዲሁም የኢትዮጵያ ወዳጆች በተለያየ ባህል ልብስ አሸብርቀው በተገኙበት ተከብሯል፡:

በዓሉ በአባቶች ምርቃት ከተከፈተ በኋላ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የቆንስላ ጄነራል ፅ/ቤት ጉዳይ ፈፃሚና የዳያስፓራ ዘርፍ ሀላፊ አቶ ጌታቸው ኡታ በመልዕክታቸው ኢትዮጵያ የተለያዩ ብሔሮች እና ብሔረሰቦች፣ ቋንቋዎች፣ ባህሎች፣ እምነቶች…ወዘተ ያሉባት የብዝኃነት ቤት እንደሆነች ጠቅሰው የአገራችንን ብዝኃነት ለማስተዳደር፣ ኅብረ-ብሔራዊ አንድነትን ለማጠናከርና የሀገረ-መንግስት ግንባታን ስኬታማ ለማድረግ ከተሠሩ ሥራዎች ዋናው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች መብቶች መከበር ዋስትና የሰጠው የኢፌዴሪ ሕገ-መንግስት ህዳር 29 ቀን 1987 ዓ.ም መጽደቁ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ በማያያዝም ሕገ-መንግስቱ የፀደቀበት ቀን “የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን” ሆኖ ከ1999 ዓ.ም ጀምሮ ላለፉት 19 ዓመታት መከበሩ በአገራችን ሕዝቦች መካከል የበለጠ መቀራረብ፣ መተዋወቅና አንዱ ከአንዱ የሚማማርበት እድል በማስፋት፣ የብዝሃነት አያያዝና የዲሞክራሲ ባህል በማዳበርና ሀገራዊ አንድነትን በማጠናከር ረገድ ከፍተኛ ሚና እንደተጫወተ አስገንዝበዋል፡፡

20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን “ዲሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ-ብሄራዊ አንድነት” በሚል መሪ እየተከበረ እንደሆነ ጠቅሰው መሪ ቃሉ ከብዝኃነታችን አንጻር በውሳኔ አሰጣጥ ሰፊ ተሳትፎን፣ የህዳጣን/አናሳ ውክልናን፣ አካታችነትን፣ አቃፊነትን፣ ድርድርና የጋራ ስምምነት በማስፋት ዜጎች በአገራዊ ጉዳዮች የጋራ ኃላፊነት እንዲሰማቸው በማድረግ ለሕብረ-ብሔራዊ አንድነትና ለአገረ-መንግስት ግንባታ አስተዋጽኦ የሚያበረክተውን የመግባባት ዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዳበርን የሚጠይቅ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡ በሊባኖስ የሚኖረውን የኢትዮጵያ ማህበረሰብ ለአገር ልማት፣ ለወገን ድጋፍና ለቤተሰብ ሕይወት መሻሻል ለጋሽ በመሆን የአብሮነት፣ የአንድነት፣ የመተሳሰብና የመደጋገፍ ተምሳሌት እንደሆነ በመግለጽ ይኸው ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል፡፡ በመጨረሻም ጳጉሜ 2 የኅብር ቀን በሚል የተካሄደው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ምርቃት ዝግጅት እንዲሳካ አስተዋፅኦ ላደረጉ አካላት የምስጋና የምስክር ወረቀት አበርክተዋል፡፡

በዕለቱ የሕጻናት መዝሙርና ግጥም፣ በአዋቂዎች በቀረቡ ግጥሞች፣ የሀገራችንን ብዝኃነትና የልማት ስራዎች የሚያሳይ ቪዲዮ፣ የኢትዮጵያ ቡና አፈላል ስነ- ስርዓት፣ የተለያዩ የብሔር፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች የሚወክሉ ሙዚቃዎችና ውዝዋዜ በመሳሰሉ ኩነቶች በዓሉ በድምቀት ተከብሮ ተጠናቋል፡፡

ባድላይ
07/12/2025

ባድላይ

Address

Beirut

Telephone

+96176152264

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Children in Lebanon posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Ethiopian Children in Lebanon:

Share