Berhet woreda communication

Berhet woreda communication to build up berhet woreda communication service to comunity

" ከምርጫ በኋላ የተሳካ አመራር የሚለካው በድምፅ ብዛት ሳይሆን የህዝብን ተጠቃሚነት በማረጋገጥ መሆን አለበት "አቶ መካሻ አለማየሁየሰሜን ሸዋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የሰሜን ሸዋ ዞን ብልፅግና...
12/06/2026

" ከምርጫ በኋላ የተሳካ አመራር የሚለካው በድምፅ ብዛት ሳይሆን የህዝብን ተጠቃሚነት በማረጋገጥ መሆን አለበት "

አቶ መካሻ አለማየሁ
የሰሜን ሸዋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ

የሰሜን ሸዋ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት "ከምርጫ ድል ማግስት፤ ጠንካራ መንግስት!" በሚል መሪ ሃሳብ የሰባተኛውን ሀገራዊ ጠቅላላ የምርጫ ሂደትና የፓርቲውን የምርጫ ዕቅድ አፈጻጸም ገመገመ።

በመድረኩ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ መካሻ አለማየሁ እና ፓርቲ ሃላፊው አቶ ኤልያስ አበበ እንዲሁም የዞኑ ከፍተኛ አመራሮችና ሁሉም የወረዳና ከተሞች አመራሮች ተሳትፈዋል።

በመድረኩ የሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ የፓርቲ እቅድ አፈጻጸም በዝርዝር ቀርቦ ተገምግሟል ጠንካራና ደካማ አፈጻጸሞች ተለይተው ውይይት ተካሂዶበታል።

በድህረ ምርጫ ወቅትም ትኩረት በሚሰጣቸው ጉዳዮች ላይ ዝርዝር አቅጣጫ ተቀምጧል። ጥቅል ተግባሮች ተገምግመዋል።

የዞኑ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ኤልያስ አበበ እንዳሉት ሰሜን ሸዋ ከአመራሩ እስከ መላ ህዝቡ ድረስ ሃገርን ለማፅናት ትልቅ መስዋዕትነት እየከፈለ ያለ መሆኑን ይህ ታላቅ ሃገራዊ ምርጫ በግልፅ ያሳየ መሆኑን ተናግረዋል። ምስጋናቸውንም አቅርበዋል።

ይህን የተሳካ ቅንጅታዊ አሰራር በማስቀጠል በቀጣይ እንደዞን መላውን ህዝባችንን የልማቱና የሰላሙ ባለቤት በማድረግ ሃላፊነታችንን ልንወጣ ይገባል ሲሉ ኃላፊው አሳስበዋል።

የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ መካሻ አለማየሁ እንዳሉትም በዞኑ በርካታ አካባቢዎች ምርጫው በተገቢው ሁኔታ ማሳካት እንደተቻለ ገልፀው በዞኑ ከላይ እስከታች የነበረው መናበብና እና መቀናጀት ሊመሰገን የሚገባው መሆኑን ተናግረዋል።

በቀጣይም በምርጫው ሂደት የነበረው የተቀናጀ እና ውጤታማነት ስራ ተጠናክሮ መቃጠል እንዳለበት ገልፀዋል፤ ስለሆነም በቀጣይ በልማት ሰላሙና መልካም አስተዳደር ዘርፍ እምርታ ለማምጣት መስራት እንደሚገባ በአፅንኦት ተናግረዋል።

ሁሉም በየመስኩ ሃገር እንዲፀና ሃገር እንዲመሰረት የተከፈለውን ዋጋ በማሰብ የጋራ ራዕይ መፍጠር እና ጠንክሮ መጓዝ እንደሚገባ ተናግረዋል፤

ከምርጫ በኋላ የተሳካ አመራር የሚለካው በድምፅ ብዛት ሳይሆን የህዝብን ተጠቃሚነት በማረጋገጥ መሆኑን ሁሉም አመራር ተገንዝቦ በላቀ ስሜት ወደ ልማት ስራ መግባት እንደሚገባ በአፅንኦት ገልፀዋል።

የተማሪ ወላጆች እና የትምህርት ቤቱ ማህበረሰብ እንኳን ደስ አላችሁ!! በአንጋፋው የመጥተህ ብላ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዛሬ አበቦች የነገ ፍሬዎች በድምቀት ተመርቀዋል። መጥተህ ብላ፡ ...
11/06/2026

የተማሪ ወላጆች እና የትምህርት ቤቱ ማህበረሰብ እንኳን ደስ አላችሁ!!

በአንጋፋው የመጥተህ ብላ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የዛሬ አበቦች የነገ ፍሬዎች በድምቀት ተመርቀዋል።

መጥተህ ብላ፡ ሰኔ 04/2018 ዓ.ም (በወመኮ)

አንጋፋው የመጥተህ ብላ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ዕድሜያቸው 6 ዓመት የሆናቸውን 1 መቶ 70 የቅድመ አንደኛ ደረጃ ተማሪዎችን በአማረና በደመቀ ሁኔታ አስመረቀ።

የሚገርመው ደግሞ ከተመራቂ ተማሪዎች ውስጥ 10 ህጻናት በልደታቸው እለት መመረቃቸው ደስታቸውን እጥፍ ድርብ አድርጎታል።

በእለቱ ተመራቂ ህጻናት በተኮላተፈ አንደበታቸው ሲያዜሙ ወላጆች ላይ ፍጹም ሀሴት ይነበባል።

"ዱባ ዛፍ ላይ ላይበቅል፤
ውሀ ሽቅብ ላይወጣ፤
ልጅነቴ ናፈቀኝ ተመልሶ ላይመጣ"
የሚለው ግጥም ከወላጆች አዕምሮ እንደተሰነቀረ ከፊታቸው መረዳት አያዳግትም።

በዘንድሮው የትምህርት ዘመን 1 መቶ 70 ተማሪዎች መመረቃቸውን ያበሰሩት የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር አቶ ውብሸት አበባየሁ፡ ትምህርት ቤቱ ለህጻናት በቂ መዝናኛና የመማሪያ ክፍሎች ስለሌሉት ወላጆችና የወረዳው ትምህርት ጽህፈት ቤት ሁሉን አቀፍ ድጋፍ እንዲያደርጉላቸው ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

የበረኸት ወረዳ ትምህርት ጽህፈት ቤት ምክትል ሀላፊ ወ/ሮ ሸዋንግዥው ጎሽሜ ደግሞ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት በማስተላለፍ፡ ለእነዚህ ታዳጊ ህጻናት በሁሉ ነገር ቅድሚያ በመስጠትና በመንከባከብ ለዛሬዋ ቀን ላደረሳችሁ ሁሉ ምስጋናየ ከልብ ነው ብለዋል።

እነዚህን የዛሬ አበቦች ማስተማር የነገዋን ኢትዮጵያ በጽኑ መሰረት ላይ መገንባት መሆኑንም ምክትል ሀላፊዋ በአጽንኦት ተናግረዋል።

የአንድ ትውልድ መሠረቱ የቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ሲሆን ይህም ለትምህርት ጥራት እና የተማሪዎችን ብቃት ለማሳደግ የላቀ ጠቀሜታ እንዳለው ለሁሉም ግልጽ ነው።

በተለይም እድሜያቸው ለመደበኛ ትምህርት ያልደረሱ ህጻናት የትምህርት ቤት አካባቢን እንዲላመዱ በማድረግ ለመደበኛው ትምህርት ዝግጁ ማድረግ ይገባል።

ስለሆነም ሁሉም ወላጆች ህጻናትን ቅድመ መደበኛ ትምህርት በማስገባት ማህበራዊ ሀላፊነታችሁን እንድትወጡ ስንል መልዕክታችንን እናስተላልፋለን።

ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 22 የፀደቁ ውጤቶችን ይፋ ማድረጉ ተገለጸ፤የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ በኦሮሚያ፣ በአማራ፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ እና በሶማሌ ክልል በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለክልሎችና ለሕዝብ ተ...
11/06/2026

ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 22 የፀደቁ ውጤቶችን ይፋ ማድረጉ ተገለጸ፤

የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ በኦሮሚያ፣ በአማራ፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ እና በሶማሌ ክልል በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለክልሎችና ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተወዳደሩ የእጩዎች ውጤቶችን ይፋ አድርጓል።

ቦርዱ በዛሬው ዕለት ይፋ ያደረጋቸው 22 የፀደቁ ውጤቶችን ነው።

በአማራ ክልል ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 1፣ በኦሮሚያ ክልል ለክልል ዕጩ 9 ለተወካዮች ምክር ቤት 7 ውጤቶችን ነው ይፋ ያደረገው።

በተመሳሳይ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ 3 የፀደቁ ውጤቶችን ይፋ አድርጓል ሲል የዘገበው ኤፍ ኤም ሲ ነው።

የህፃናት የማይንቀሳቀስ ንብረት ለመሸጥ የፍርድ ቤት ፍቃድ የሚያስፈልግ ስለመሆኑየህፃናት ንብረት ያለፍርድ ቤት ፈቃድ መሸጥ አይቻልም። በቅርቡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት አ...
10/06/2026

የህፃናት የማይንቀሳቀስ ንብረት ለመሸጥ የፍርድ ቤት ፍቃድ የሚያስፈልግ ስለመሆኑ
የህፃናት ንብረት ያለፍርድ ቤት ፈቃድ መሸጥ አይቻልም። በቅርቡ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት አንድን ትልቅ የቤት ሽያጭ ውል "ህፃኑ ሳይፈቅድ እና የፍርድ ቤት ፈቃድ ሳይኖር የተደረገ ነው" በማለት ውድቅ አድርጎታል።ጉዳዩ ምን ነበር? አመልካች (ፍቅሩ መገርሳ)፦ በህፃንነቱ (ከ14-16 ዓመቱ) አባቱ የሞቱበት እና በውርስ ያገኘው ቤት ነበረው። ተጠሪዎች (ሚሊዮን ተክላይ እና አለምነሽ አቸቴ)፦ የህፃኑ እናት (2ኛ ተጠሪ) ለ1ኛ ተጠሪ በውክልና ቤቱን ሸጠውለታል።
ክርክሩ፦ አመልካች "ቤቱ ሲሸጥ ለአቅመ አዳም አልደረስኩም ነበር፤ ሽያጩም የእኔን ጥቅም አላስጠበቀም" በማለት ክስ መሰረተ። ገዢው በበኩሉ "ቤቱን የገዛሁት በህጋዊ ውክልና ነው፤ ብዙ ወጪ አውጥቼም አድሻለሁ" ብሎ ተከራክሯል። የሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔ እና ትርጉም፦የፍርድ ቤት ፈቃድ ግዴታ ነው፦ የህፃናትን የማይንቀሳቀስ ንብረት ለመሸጥ የአሳዳጊ ውክልና ብቻ በቂ አይደለም። የግድ የፍርድ ቤት ፈቃድ መኖር አለበት።
የውክልና ስልጣን ገደብ፦ አንድ ህፃን ለአቅመ አዳም ሳይደርስ የሰጠው ውክልናም ሆነ በእሱ ስም ያለፍርድ ቤት ፈቃድ የሚደረግ የቤት ሽያጭ በህግ ፊት ፀንቶ አይቆምም።
ውሉ ፈርሷል፦ ችሎቱ በሰበታ ከተማ የሚገኘው ቤት ሽያጭ ውል እንዲፈርስ እና ቤቱ ለአመልካች እንዲመለስ ወስኗል።
የገዢው መብት፦ ገዢው ቤቱ ላይ ላወጣው ተጨማሪ ወጪአመልካቹን ለብቻው የመጠየቅ መብት አለው ተብሏል።
ከዚህ ምን እንማራለን?
ለገዢዎች፦ ከህፃናት ወይም ከአሳዳጊዎቻቸው ቤት ሲገዙ የፍርድ ቤት የሽያጭ ፈቃድ መኖሩን ማረጋገጥ ግዴታ ነው። አለበለዚያ ከዓመታት በኋላ ንብረቱ ሊወሰድብዎት ይችላል።
ለወላጆች አሳዳጊዎች፦ የልጆችን ንብረት ለልጆቹ ጥቅም ሲባል እንኳን ቢሆን ለመሸጥ የፍርድ ቤት ፈቃድ ማግኘት ህጋዊ ግዴታ መሆኑን ይገንዘቡ። የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔ፣ ቅፅ 25 መዝገብ ቁጥር 194876

የ2019 ረቂቅ በጀት ከ2.3 ትሪሊዮን ብር በላይ ሆኖ እንዲቀርብ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ወሰነ  ***************** የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 56ኛ መደበኛ ስ...
09/06/2026

የ2019 ረቂቅ በጀት ከ2.3 ትሪሊዮን ብር በላይ ሆኖ እንዲቀርብ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ወሰነ
*****************

የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 56ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል።

ምክር ቤቱ የ2019 በጀት ዓመት የፌዴራል መንግሥት የበጀት ረቂቅ አዋጅ ላይ ተወያይቷል።

የ2019 የፌዴራል መንግሥት በጀት የዐሥር ዓመቱ መሪ የልማት ዕቅድ አካል የሆነው የ2019-2021 የልማት እና ኢንቨስትመንት ዕቅድ ላይ የተቀመጡ ግቦችን እና የመካከለኛ ዘመን (2019-2023) የማክሮ ኢኮኖሚ እና የፊሲካል ማዕቀፍን መሠረት በማድረግ፣ የ2018 በጀት ዓመት የፕሮግራም በጀት አፈጻጸም መነሻ በማድረግ፣ በቀጣይ ሊኖር የሚችለውን የማኅበራዊ እና የኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን አቅጣጫዎች እና ዓላማዎች እንዲሁም በመንግሥት የተቀመጡ ግቦችን ለማሳካት የመንግሥትን የፋይናንስ አቅም እና አስፈጻሚ መሥሪያ ቤቶች ከተሰጣቸው ተልዕኮ እና ኃላፊነት አንጻር የሚያስፈልገውን ወጪ በመገምገም ተዘጋጅቶ ቀርቧል።

በዚሁ መሠረትም ለመደበኛ ወጪዎች፣ ለካፒታል ወጪዎች፣ ለክልል መንግሥታት ድጋፍ፣ ለዘላቂ የልማት ግቦች ማስፈጸሚያ ድጋፍ የሚውል 2 ትሪሊዮን 339 ቢሊዮን 268 ሚሊዮን 126 ሺህ 738 (ሁለት ትሪሊዮን፣ ሦስት መቶ ሠላሳ ዘጠኝ ቢሊዮን፣ ሁለት መቶ ስድሳ ስምንት ሚሊዮን፣ አንድ መቶ ሀያ ስድስት ሺህ፣ ሰባት መቶ ሰላሳ ስምንት) ብር በጀት ለምክር ቤቱ ቀርቧል።

ምክር ቤቱም በቀረበው የፌዴራል መንግሥት የ2019 ረቂቅ በጀት አዋጅ ላይ በሰፊው ከተወያየበት በኋላ ግብአቶችን በማከል ወደ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምፅ መወሰኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት አስታውቋል።

ስለ ቼክ ማወቅ ያለባችሁ ወሳኝ የህግ ነጥቦችበቼክ ገንዘብ ሊሰጣችሁ ወይም ቼክ ልትፈርሙ ስለምትችሉ ቀጣዮቹን ቼክን የሚመለከቱ ወሳኝ ነጥቦች እናንሳ። ቼክ ማለት ገንዘብን ተክቶ የሚያገለግል ...
08/06/2026

ስለ ቼክ ማወቅ ያለባችሁ ወሳኝ የህግ ነጥቦች

በቼክ ገንዘብ ሊሰጣችሁ ወይም ቼክ ልትፈርሙ ስለምትችሉ ቀጣዮቹን ቼክን የሚመለከቱ ወሳኝ ነጥቦች እናንሳ።
ቼክ ማለት ገንዘብን ተክቶ የሚያገለግል ተላላፊ የገንዘብ ሰነድ ነው፡፡ ቼክ ሊፈርም የሚችለው በአንድ ባንክ ውስጥ ተንቀሳቃሽ ሂሳብ ያለው ሰው ነው፡፡ድርጅት ከሆነ ደግሞ ፈራሚው በድርጅቱ ቼክ ላይ የመፈረም ስልጣን የተሰጠው መሆን አለበት፡፡
-ቼክ ከመቀበላችሁ በፊት በቼኩ ላይ የሚከፈለው የገንዘብ መጠን በአሀዝና በፊደል መፃፉን የሚከፈለው ሰው ስም እና የባንኩ ቅርንጫፍ መፃፉን፣ ቼኩን የሰጠው ሰው ፊርማ መኖሩን ፣ቼኩ የተፃፈበት ቀን እና ቦታ መኖሩ ማረጋገጥ የግድ አስፈላጊ መሆኑን የንግድ ህግ አንቀፅ 827 ይደነግጋል።
-ቼኩ ለማን እንደሚከፈል ስም ካልተጠቀሰበት ማንኛውም ቼኩን ይዞ የቀረበ ሰው ይከፈለዋል። ቼኩ በስሙ የተፃፈለት ሰው ወይም በትዕዛዝ የሚል ካለበት ደግሞ በቀላሉ ከጀርባው በመፈረም ለሌላ ሰው ሊያስተላልፈው ይችላል ። ያም ሰው በጀርባው ፈርሞ ለሌላ ሰው ማስተላለፍ ይችላል፡፡
-የገንዘብ መጠኑ ያልተጠቀሰበትን ቼክ ፈርሞ መስጠት አደገኛ ነው ፡፡ ቼኩ የተፃፈለት ወይም የተላለፈለት ሰው የፈለገውን ገንዘብ ሊሞላበት ይችላል፡፡
-ቼኩ የሚከፈለው ለባንኩ ለክፍያ በቀረበ ቀን ነው። - ሆኖም ቼኩ በን/ሕ/ቁ 857 መሠረት የወጣበት ቀን ከግምት ሳይስገባ ቼኩ ላይ ከተፃፈው ቀን ጀምሮ በ6 ወር ውስጥ ለባንኩ ለክፍያ መቅረብ አለበት፡፡ ቼኩን የሚፈርመው ሰው የክፍያውን ቀን ቼኩን ከፃፈበት ወይም ቼኩን ካወጣበት ቀን ወደፊት ወይም ወደ ኋላ ሊያደርገው ይችላል። ለምሳሌ ዛሬ ቼኩን ሲፅፍ የተፃፈበት ቀን ወደኃላ 7 ወር አድርጎ ቀኑን ቢፅፈው ለክፍያ መቅረብ ያለበት 6 ወር ጊዜ ስላለፈ ባንኩ መክፈልም ሆነ ያልከፈለበትን ምክንያት ለመግለፅ ሳይገደድ ቼኩ ለክፍያ መቅረብ ባለበት ጊዜ ባለመቅረቡ ብቻ ይመልሰዋል፡፡ ዛሬ የሚሰጥህን ቼክ ወደፊት የዛሬ 4 ወር አድርጎ ቀኑ ከተፃፈበት ለክፍያ መቅረብ የሚችለው ከአራት ወራት በኃላ ካለው ቀን ጀምሮ ባለው 6 ወራት ውስጥ ነው፡፡ ስለዚህ ቼክ ተቀባዬች የሚሰጣቸውን ቼክ ገንዘቡን መቀበል ከሚችሉበት ቀን አንፃር በጥንቃቄ የተፃፈበት ቀን ማየት አለባቸው ።
-ቼክ የሰጠው ሰው ቼኩ ለባንኩ ለክፍያ ከመቅረቡ በፊት ባንኩን እንዳትከፍል ብሎ መከልከል ይችላል። ባንኩም የክፍያ መከልከያ ትእዛዝ ከደረሰው መክፈል የለበትም።
-የተረጋገጠ ቼክ (cpo) የተጠቀሰው ገንዘብ መኖሩ በባንኩ ተረጋግጦ የተቀመጠ በመሆኑ ከተራ ቼክ የበለጠ አስተማማኝ ነው።
-ቼኩን ለባንክ አቅርበን በቼኩ ላይ የተጠቀሰውን ያህል በቂ ገንዘብ ከሌለ በሂሳቡ ውስጥ ያለውን ያህል መቀበል ይቻላል። ለቀረው ገንዘብ ደግሞ ባንኩ ‘‘በቂ ስንቅ ለውም’’ የሚል የፅሁፍ ማስረጃ ቼኩን ይዞ ለቀረበው ሰው ይሰጠዋል።
-በተለምዶ ‘‘ደረቅ ቼክ’’ የሚባለው ለክፍያ ሲቀርብ በሂሳቡ ውስጥ በቂ ገንዘብ ከሌለው ሲሆን ባንኩ በሚሰጠው ማስረጃ መሰረት ቼክ ሰጪውን ወይም አውጭውን በወንጀል ያስጠይቃል። ሆን ተብሎ ከተፈፀመ ቼክ አውጪው በወንጀል ህግ አቀፅ 693 መሰረት በቀላል እስራት ወይም ነገሩ ከባድ ከሆነ ደግሞ ከአስር አመት በማይበልጥ ፅኑ እስርና በመቀጮ ይቀጣል።
-ደረቅ ቼኩ የተሰጠው በቸልተኝነት ከሆነ ደግሞ ሰጭው በመቀጮ ወይም ከአንድ አመት በማይበልጥ ቀላል እስር ይቀጣል ፡፡ ሳይከፈል የቀረውን የቼኩን ገንዘብ ና ወጭውን ቼኩ የተፃፈለት ወይም ተፈርሞ የተላለፈለት ሰው በፍትሀ ብሔር ከሶ ገንዘቡን ማስመለስ ይችላል፡፡
-በብሔራዊ ባንክ መመሪያ መሰረት ደረቅ ቼክ የሚሰጡ ሰዎች በጥፋታቸው በጥቁር መዝገብ ውስጥ የሚገቡ ሲሆን ከገንዘብ መቀጮ አንስቶ በቼክ ሂሳብ የማንቀሳቀስ መብታቸውን እስከማሳጣት ቅጣት ይጣልባቸዋል፡፡ እነዚህ ከላይ ያነሳናቸው ህጎች ቼክን የገንዘብ ያህል አስተማማኝ ለማድረግ የተደነገጉ ናቸው። ለግብይት ቅልጥፍና እንዲሁም ለገንዘብ እንቅስቃሴ አመቺነት በቼክ መጠቀሙ ከጥሬ ገንዘብ የተሻለ ዘመናዊ አሰራር በመሆኑ ቼክ አስፈላጊና ልንጠቀምበት የሚገባ የገንዘብ ሰነድ ነው። ለማንኛውም ቼክ ስንሰጥም ሆነ ስንቀበል ከላይ የተነሱትን ነጥቦች ልብ እንበል፡፡

"የሙቀት አማቂ ጋዞችን ለመቀነስ ስርዓተ ምህዳሩን ወደነበረበት መመለስ ይገባል።" አቶ ደምሰው ጌታቸው የበረኸት ወረዳ አካባቢ ጥበቃ ተጠሪ ፅህፈት ቤት "የአለም አካባቢ ቀንን"  በፓናል ውይ...
08/06/2026

"የሙቀት አማቂ ጋዞችን ለመቀነስ ስርዓተ ምህዳሩን ወደነበረበት መመለስ ይገባል።"

አቶ ደምሰው ጌታቸው

የበረኸት ወረዳ አካባቢ ጥበቃ ተጠሪ ፅህፈት ቤት "የአለም አካባቢ ቀንን" በፓናል ውይይት አከበረ።

መጥተህ ብላ፡ ሰኔ 01/2018 ዓ.ም (በወመኮ)

በመድረኩ የወረዳው አመራሮች፣ የመንግስት ተቋማት ቡድን መሪዎች እንዲሁም ተጋባዥ እንግዶች የታደሙ ሲሆን የበረኸት ወረዳ አካባቢ ጥበቃ ተጠሪ ጽህፈት ቤት ባለሙያ አቶ ወንዶሰን አራጋው በአየር ንብረት ለውጥ ምንነት፣ መንስኤዎችና የመፍትሄ አማራጮች ዙሪያ ሰነድ አቅርበዋል።

በአለም አቀፍ ደረጃ ለ53ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ለ33ኛ እንዲሁም በአማራ ክልል ለ29ኛ ጊዜ የተከበረው ይህ ወሳኝ ቀን እለቱ በፓናል ውይይት የተከበረበት መሰረታዊ ዓላማ ህብረተሰቡ በአየር ንብረት ለውጥና ተዛማጅ የአካባቢ ጉዳዮች የሚኖራቸውን ግንዛቤ ለማሳደግ እና አወንታዊ ሚና የሚወጣ ዜጋ በማፍራት ፅዱ እና ምቹ አካባቢ ለመፍጠር መሆኑ ተገልጿል ።

በእለቱ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የበረኸት ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ደምሰው ጌታቸው እንደገለጹት የአለም አካባቢ ቀን ማክበር ከተጀመረ ረጅም አመታትን ቢያስቆጥርም እምርታዊ ለውጥ ከማምጣት አንጻር ስር የሰደደ ችግር መኖሩን አብራርተዋል።

በአሉን ከማክበር በዘለለ ለአካባቢያችን እና ለህዝባችን ምቹና ጽዱ አካባቢ መፍጠር እንደሚገባ የጠቆሙት አስተዳዳሪው፡ የሙቀት አማቂ ጋዞችን ለመቀነስ ስርዓተ ምህዳሩን ወደነበረበት መመለስ እንደሚገባ በአጽንኦት ተናግረዋል።

የመጥተህ ብላ መሪ ማዘጋጃ ቤት ስራ አስኪያጅ አቶ በለጠ አማረ በበኩላቸው፡ ንፁህ ከባቢ አየር ለመፍጠርና ራሳችንን ከሰው ሰራሽ በሽታዎች ለመከላከል የቆሻሻ አወጋገድ ስርዓትን መተግበርና ህጋዊ ተጠያቂነትን በማስፈን በርብርብ መስራት አለብን ሲሉ ተናግረዋል።

በተለይ "የበረሀዋ ገነት" መጥተህ ብላ ለኑሮ ተስማሚና ለዜጎቿ የተመቸች ከተማ እንድትሆን ሁሉም ማህበረሰብ የድርሻቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ስራ አስኪያጁ አሳስበዋል።

በሌላ በኩል በቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ዙሪያ የወጣን አዋጅ በግልጽ ያብራሩት የበረኸት ወረዳ ፍትህ ጽህፈት ቤት የወንጀል አቃቢ ህግ ብናልፈው ምንዋጋው፡ ማንኛውም ሰው ከመኖሪያ ቤቱ አንስቶ እስከ 20 ሜትር ባለው ርቀት ውስጥ ደረቅ ቆሻሻን የማጽዳት ሀላፊነት እንዳለበት በአጽንኦት ተናግረዋል።

አክለውም ለአንድ ጊዜ ብቻ የሚያገለግሉ የፕላስቲክ ውጤቶች ወደሀገር ውስጥ ማስገባት፣ ማምረት፣ መሸጥ፣ ማከማቸት ወይም መጠቀም ተጠያቂነት የሚያስከትል መሆኑን አሳስበዋል።

የአካባቢያችንን ጽዳት ለመጠበቅ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት የድርሻቸውን መወጣት እንዳለባቸው የጠቆሙት የወረዳው ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ታደሰ ቤኩማ፡ ከተማዋን ከቆሻሻ ብክለት ነጻ በማድረግ ለኑሮ ተስማሚ አካባቢ መፍጠር እንደሚገባ ምክረ ሀሳባቸውን ለግሰዋል።

"የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን በጋራ እንግታ!!"

የተሰበሰቡ አጀንዳዎች ተደራጅተው ለመጨረሻው የአጀንዳ ቀረፃ እየተዘጋጁ ነው፦ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን  *****************የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሀገራችን ኢት...
08/06/2026

የተሰበሰቡ አጀንዳዎች ተደራጅተው ለመጨረሻው የአጀንዳ ቀረፃ እየተዘጋጁ ነው፦ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን
*****************

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሀገራችን ኢትዮጵያ ከሚገኙ እና በውጭ ሀገራት ከሚገኙ ኢትዮጵያዊያን የአጀንዳ ሃሳቦችን ማሰባሰቡ የሚታወቅ ነው። በዚህ የምክክር ሂደት በክልል/ ከተማ አስተዳደር ደረጃ፣ በፌዴራል ደረጃ እንዲሁም በዲያስፖራው ማህበረሰብ ዘንድ የተሰበሰቡ አጀንዳዎች በኮሚሽኑ ተደራጅተው ለመጨረሻው የአጀንዳ ቀረፃ እየተዘጋጁ ነው።

በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው ላይ ተሳትፎን የሚያደርጉ አካላት ኮሚሽኑ አጀንዳ ካሰባሰበባቸው ባለድርሻ አካላት የተመረጡ/ የተወከሉ ሲሆን ይህም በባለድርሻ አካላቱ እውቅና ሲከናወን ቆይቷል፡፡ በዚህ መሰረት በክልሎች/ ከተማ አስተዳደሮች፣ እና በዲያስፖራው ማህበረሰብ ዘንድ የሚገኙ ባለድርሻ አካላት በአጀንዳ ማሰባሰብ ወቅት በሀገራዊ ምክክር ጉባዔው ላይ እነሱን ወክለው የሚመካከሩ ወኪሎቻቸውን እንዲመርጡ ተደርጓል።

በሌላ በኩል በኩሚሽኑ አሰራር ስርዓት መሰረት በክልሎች/ከተማ አስተዳደሮች እና በፌዴራል ተቋማት በሚገኙና ወኪሎቻቸውን በአጀንዳ ማሰባሰብ ወቅት እንዲመርጡ ያልተደረጉ ባለድርሻ አካላት ወኪሎቻቸውን በደብዳቤ ወክለው ለኮሚሽኑ እንዲያሳውቁ ኮሚሽኑ ለባለድርሻ አካላቱ ጥሪ በማስተላለፍ ላይ ይገኛል።

በዚህ መሰረት በአጠቃላይ 4,000 የሚጠጉ ተሳታፊዎች የሚሳተፉበት የሀገራዊ ምክክር ሂደት
👉የየወረዳው የሕብረተሰብ ክፍል ወኪሎችን
👉የክልል/ከተማ አስተዳደር ባለድርሻ አካላት ወኪሎችን
👉የፌዴራል ባለድርሻ አካላት ወኪሎችን እና
👉የዲያስፖራ ማህበረሰብ ወኪሎችን ያሳትፋል፡፡

Ethiopian Broadcasting Corporation #ምክክር #ሀገራዊምክክር #ኢትዮጵያ

"29 የምርጫ ክልሎች ውጤታቸውን አጠናቀው ወደ ዋናው ማዕከል ልከዋል" ምርጫ ቦርድ በአዲስ አበባ፣ ኦሮሚያ፣ አማራና ማዕከላዊ ኢትዮጵያ የሚገኙ 29 የምርጫ ክልሎች ውጤታቸውን አጠናቀው ወደ ...
07/06/2026

"29 የምርጫ ክልሎች ውጤታቸውን አጠናቀው ወደ ዋናው ማዕከል ልከዋል" ምርጫ ቦርድ

በአዲስ አበባ፣ ኦሮሚያ፣ አማራና ማዕከላዊ ኢትዮጵያ የሚገኙ 29 የምርጫ ክልሎች ውጤታቸውን አጠናቀው ወደ ዋናው ማረጋገጫ ማዕከል መላካቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በሰጡት መግለጫ፤ በምርጫው ከተካተቱት 1 ሺህ 138 የምርጫ ክልሎች 825ቱን በማዳመር ሥራቸውን አጠናቀው ውጤታቸውን በየክልላቸው ይፋ አድርገዋል።

ከእነዚህም 29 የምርጫ ክልሎች መረጃዎቻቸውን አረጋግጠው ወደ ዋናው የማረጋገጫ ማዕከል መላካቸውን ተናግረዋል።

እንደ ሰብሳቢዋ ገለፃ፤ በምርጫው ወቅት በፀጥታ ችግር ምክንያት የድምፅ አሰጣጥ ሂደት ለተወሰነ ጊዜ ተቋርጦ የነበረ ቢሆንም፤ ሁኔታዎች ሲመቻቹ በአብዛኛዎቹ ጣቢያዎች ላይ ድምፅ እንዲሰጥ ተደርጓል።

ቦርዱ በሂደቱ የሚያጋጥሙ ቅሬታዎችን በልዩ ልዩ የቅሬታ መቀበያ ዴስኮች፣ በ7555 የስልክ መስመር በኩል በመቀበል ፈጣን እርምጃዎችን እየወሰደ መሆኑን ተናግረዋል ሲል የዘገበው ኢቢሲ ነው።

06/06/2026

Adresse

Berhet
09

Téléphone

0224720090/87

Site Web

Notifications

Soyez le premier à savoir et laissez-nous vous envoyer un courriel lorsque Berhet woreda communication publie des nouvelles et des promotions. Votre adresse e-mail ne sera pas utilisée à d'autres fins, et vous pouvez vous désabonner à tout moment.

Contacter L’organisation

Envoyer un message à Berhet woreda communication:

Partager