12/06/2026
" ከምርጫ በኋላ የተሳካ አመራር የሚለካው በድምፅ ብዛት ሳይሆን የህዝብን ተጠቃሚነት በማረጋገጥ መሆን አለበት "
አቶ መካሻ አለማየሁ
የሰሜን ሸዋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ
የሰሜን ሸዋ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት "ከምርጫ ድል ማግስት፤ ጠንካራ መንግስት!" በሚል መሪ ሃሳብ የሰባተኛውን ሀገራዊ ጠቅላላ የምርጫ ሂደትና የፓርቲውን የምርጫ ዕቅድ አፈጻጸም ገመገመ።
በመድረኩ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ መካሻ አለማየሁ እና ፓርቲ ሃላፊው አቶ ኤልያስ አበበ እንዲሁም የዞኑ ከፍተኛ አመራሮችና ሁሉም የወረዳና ከተሞች አመራሮች ተሳትፈዋል።
በመድረኩ የሰባተኛውን ጠቅላላ ምርጫ የፓርቲ እቅድ አፈጻጸም በዝርዝር ቀርቦ ተገምግሟል ጠንካራና ደካማ አፈጻጸሞች ተለይተው ውይይት ተካሂዶበታል።
በድህረ ምርጫ ወቅትም ትኩረት በሚሰጣቸው ጉዳዮች ላይ ዝርዝር አቅጣጫ ተቀምጧል። ጥቅል ተግባሮች ተገምግመዋል።
የዞኑ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ኤልያስ አበበ እንዳሉት ሰሜን ሸዋ ከአመራሩ እስከ መላ ህዝቡ ድረስ ሃገርን ለማፅናት ትልቅ መስዋዕትነት እየከፈለ ያለ መሆኑን ይህ ታላቅ ሃገራዊ ምርጫ በግልፅ ያሳየ መሆኑን ተናግረዋል። ምስጋናቸውንም አቅርበዋል።
ይህን የተሳካ ቅንጅታዊ አሰራር በማስቀጠል በቀጣይ እንደዞን መላውን ህዝባችንን የልማቱና የሰላሙ ባለቤት በማድረግ ሃላፊነታችንን ልንወጣ ይገባል ሲሉ ኃላፊው አሳስበዋል።
የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ መካሻ አለማየሁ እንዳሉትም በዞኑ በርካታ አካባቢዎች ምርጫው በተገቢው ሁኔታ ማሳካት እንደተቻለ ገልፀው በዞኑ ከላይ እስከታች የነበረው መናበብና እና መቀናጀት ሊመሰገን የሚገባው መሆኑን ተናግረዋል።
በቀጣይም በምርጫው ሂደት የነበረው የተቀናጀ እና ውጤታማነት ስራ ተጠናክሮ መቃጠል እንዳለበት ገልፀዋል፤ ስለሆነም በቀጣይ በልማት ሰላሙና መልካም አስተዳደር ዘርፍ እምርታ ለማምጣት መስራት እንደሚገባ በአፅንኦት ተናግረዋል።
ሁሉም በየመስኩ ሃገር እንዲፀና ሃገር እንዲመሰረት የተከፈለውን ዋጋ በማሰብ የጋራ ራዕይ መፍጠር እና ጠንክሮ መጓዝ እንደሚገባ ተናግረዋል፤
ከምርጫ በኋላ የተሳካ አመራር የሚለካው በድምፅ ብዛት ሳይሆን የህዝብን ተጠቃሚነት በማረጋገጥ መሆኑን ሁሉም አመራር ተገንዝቦ በላቀ ስሜት ወደ ልማት ስራ መግባት እንደሚገባ በአፅንኦት ገልፀዋል።