Berhet woreda communication

Berhet woreda communication to build up berhet woreda communication service to comunity

ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ በጎንደር ከተማ የተሠሩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ።በጉብኝቱ ከርእሰ መሥተዳድሩ በተጨማሪ የክልል እና የፌዴራል ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች ተሳትፈዋል። ከፍተኛ የሥራ ኀ...
05/09/2026

ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ በጎንደር ከተማ የተሠሩ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ።

በጉብኝቱ ከርእሰ መሥተዳድሩ በተጨማሪ የክልል እና የፌዴራል ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች ተሳትፈዋል። ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎቹ ታሪክን ከዘመናዊት ጋር አስተባብሮ የተገነባውን የዞብል ፓርክ እና ሌሎች የልማት ሥራዎችን ነው በምሽት ያላቸውን ገጽታ ተዘዋውረው የተመለከቱት።

የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ በጎንደር ከተማ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ተዘዋውረው መመልከታቸውን ተናግረዋል። የጎንደር ከተማ ልዩ ምልክት በኾነው በታሪካዊው የቅዱስ ፋሲለደስ ባሕረ ጥምቀት ዙሪያ ገባ የተሠራው ፓርክ በአማረ ሁኔታ መልማቱን ተናግረዋል።

ልማቱ ከተሞችን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ እየተደረገ ያለው ጥረት አንዱ አካል መኾኑን ገልጸዋል። ጎንደር ደግሞ የቱሪዝም ከተማ በመኾኗ ለጎብኝዎች ምቹ የማድረግ ሂደት መኾኑን ነው ያነሱት።

ፓርኩ ለቱሪዝም መዳረሻነት ኾኖ የሚያገለግል፣ ለመዝናኛም የሚኾን ነው ያሉት ርእሰ መሥተዳድሩ በጎንደር የኮሪደር ልማት ከፒያሳ ቀጥሎ ትልቁ የመዝናኛ ማዕከል እንደኾነ ነው ያነሱት። አካባቢው ከአሁን በፊት ለጎብኝዎችም ኾነ ለነዋሪዎቹ የተመቸ አልነበረም፤ አሁን ግን ከባሕረ ጥምቀቱ በተጨማሪ ራሱን ችሎ ለጎብኝዎች መዳረሻ ኾኖ እንዲያገለግል ባማረ ሁኔታ ተገንብቷል ብለዋል።

በጎንደር የልማት እንቅስቃሴ የበለጠ እየሰፋ መሄዱን ገልጸዋል። ጎንደር በ2018 በጀት ዓመት ሥራ አፈጻጸም በክልሉ ከተሞች አንደኛ መውጣቷን ያስታወሱት ርእሰ መሥተዳድሩ በ2019 በጀት ዓመትም የበለጠ መሥራት እንዲቻል ያለመ ጉብኝት እንዳደረጉ አንስተዋል። በተመለከቱት የልማት ሥራ ከፍተኛ ደስታ እንደተሰማቸውም ገልጸዋል።

ከአማራ ኮሙኒኬሽን

‎የበረኸት ወረዳ ሰላምና ደህንነት ፅህፈት ቤት ከፅንፈኛ ቤተሰብ ጋር ውይይት አደረገ።‎‎መጥተህብላ ነሀሴ 30/2018ዓ/ም(በወመኮ)‎‎በሰሜን ዞን በረኸት ወረዳ ሰላምና ደህንነት ፅህፈት ቤት...
05/09/2026

‎የበረኸት ወረዳ ሰላምና ደህንነት ፅህፈት ቤት ከፅንፈኛ ቤተሰብ ጋር ውይይት አደረገ።

‎መጥተህብላ ነሀሴ 30/2018ዓ/ም(በወመኮ)

‎በሰሜን ዞን በረኸት ወረዳ ሰላምና ደህንነት ፅህፈት ቤት
‎ከፅንፈኛ ቤተሰቦች የጋራ ውይይት መድረክ አካሄደ።
‎መድረኩን የወረዳው ምክትል አስተዳዳሪና ሰላምና ደህንነት ፅ/ቤት ሃላፊ ዋ/ሳጅን አወቀ ወ/ኪዳን እና የሚሊሻ ፅህፈት ቤት ሃላፊ ዋ/ሳጅን አለማየሁ ከበደ በጋራ የመሩት ሲሆን በውይይቱም በሁለቱም የመድረክ መሪዎች ሰፋ ያለ ማብራሪያ በተለይም ወረዳው ከገጠመው የሰላም እጦት ምክንያት ዘርፈ ብዙ ቀውስ ውስጥ እንደገባን በመረዳት ሁሉም አካል የታጠቁ ሀይሎችን በማስገባት እና ወደነበረበት ሰላም እዲመለሱ፣ ህዝቡ በሰላም ገብቶ በሰላም የሚወጣበትን፣ልማትን የሚያረጋግጥበት ምቹ ሁኔታ መፍጠር ታላቅ ሃላፊነት እንዳለባቸው በአፅንኦት ተናግረዋል።
‎ምክትል አስተዳዳሪ አክለውም ላለፉት ሶስት አመታት የወረዳችን ህብረተሰብ ማልማት ያለበትን እንዳያለማ ተዳርጓል፣በኢኮኖሚ ተዳክሟል፣በስነ ልቦና ተጎድቷል፣መተኪያ የሌለው የሰው ህይወት አልፏል፣ሀብት ንብረት ወድሟል ስለዚህ የዚህ ሁሉ መውጫ መንገዳችን ሰለም ነው ለሰላም መከፈል ያለበት መሰዋትነት ተከፍሎ ዘላቂ ሰላም መፍጠር እንደሚያስፈልግ በመገንዘብ የታጠቁ ሀይሎች መንግስት ያቀረበውን የሰላም አማራጭ በመቀበል እንዲገቡ ጥሪ አስተላልፈዋል።

‎ተጨማሪ መረጃዎችን ከበረኸት ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ለማግኘት ቀጣዮቹን ሊንኮች ይጫኑ።
‎Facebook: https://www.facebook.com/Berhetwerdacommu
‎Telegram ፡ https://t.me/+Ygpdxi4KijkwNGU0
‎Twitter: https://twitter.com/BerhetC
‎You Tube: www.youtube.com/
‎Ticktock: www.tiktok.com/.woreda.com

"ውጫዊ የወረራ ስጋትና ውስጣዊ የፅንፈኝነት አደጋን በመቀልበስ ዘላቂ ሰላምና ልማትን እናረጋግጣለን"በሚል መሪ ቃል በ01 ቀሌ በሁሉም ብሎኮች ካሉ ነዋሪዎች ጋር በወቅታዊ የሰላምና የልማት ጉ...
04/09/2026

"ውጫዊ የወረራ ስጋትና ውስጣዊ የፅንፈኝነት አደጋን በመቀልበስ ዘላቂ ሰላምና ልማትን እናረጋግጣለን"
በሚል መሪ ቃል በ01 ቀሌ በሁሉም ብሎኮች ካሉ ነዋሪዎች ጋር በወቅታዊ የሰላምና የልማት ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደረገ።

በሰሜን ሸዋ ዞን በረኸት ወረዳ በ01 ቀበሌ በሁሉም በብሎክና በቀጠና በወቅታዊ የሰላምና የልማት ጉዳዮች ዙሪያ "ውጫዊ የወረራ ስጋትና ውስጣዊ የፅንፈኝነት አደጋን በመቀልበስ ዘላቂ ሰላምና ልማትን እናረጋግጣለን"በሚል መሪ ቃል ውይይት ተደርጓል።

በውይይቱም ነዋሪዎቹ በሰፈራቸው ሰላማቸውን ከፀጥታ መዋቅር ጋር እየጠበቁ እንደሆነ ገልፀው በልማት ዙሪያም በአካባቢው በቀጣይ መሰራት ያለባቸውን የልማት ተግባራት አንስተዋል።

የውይይት መድረኮቹን የወረዳ ምድብተኛ አመራሮች መርተዋል።

‎ተጨማሪ መረጃዎችን ከበረኸት ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ለማግኘት ቀጣዮቹን ሊንኮች ይጫኑ።
‎Facebook: https://www.facebook.com/Berhetwerdacommu
‎Telegram ፡ https://t.me/+Ygpdxi4KijkwNGU0
‎Twitter: https://twitter.com/BerhetC
‎You Tube: www.youtube.com/
‎Ticktock: www.tiktok.com/.woreda.com

‎የዩኒቨርስቲ መግብያ ውጤት ላመጡ ተማሪዎች ማበረታቻ ሽልማት ተሰጠ። ‎በሰሜን ሸዋ ዞን የበረኸት ወረዳ አስተዳደር ምክር ቤት ለ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈትነው የዩኒቭርስቲ መግቢያ ውጤት...
03/09/2026

‎የዩኒቨርስቲ መግብያ ውጤት ላመጡ ተማሪዎች ማበረታቻ ሽልማት ተሰጠ።
‎በሰሜን ሸዋ ዞን የበረኸት ወረዳ አስተዳደር ምክር ቤት ለ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈትነው የዩኒቭርስቲ መግቢያ ውጤት ላመጡ ለ17 ተማሪዎች የእንኳን ድስ አላችሁ ፕሮግራም አዘጋጀ፡፡

‎(መጥተህ ብላ ነሀሴ 28/2018ዓ/ም በወመኮ)

‎ በእለቱ የበረኸት ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪና የሰላምና ደህንነት ፅ/ቤት ሃላፊ ዋ/ሳጅን አወቀ ወ/ኪዳን፣ የአስተዳደር ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ወረቁ አበበ፣ የትምህርት ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጎሳ ገ/ኪዳን፣ የግብርና ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ደምሰው ሻውል፣ የሴቶች ህፃናት ምህበራዊ ጉዳዮች ፅህፈት ቤት ኃላፊ ወ/ሮ እቴነሽ ጋረደውና ተማሪዎች ተገኝተዋል፡፡
‎የበረኸት ወረዳ አስተዳደር ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ወረቁ አበበ ያለፉትን ተማሪዎችን እንኳን ደስ አላችሁ በማለት ይህንን የማበረታቻ የሽልማት ፕሮግራም ስናዘጋጅ በሚጠበቀው ልክ እናንተን ይጠቅማል ብለን ሳይሆን ምክር ለመስጠት ነው ብለዋል፡፡
‎በወረዳችን የማለፊያ ውጤት ያመጡ አብዛኛዎቹ ሴት ተማሪዎች መሆናቸውን በመግለፅ ወላጆቻችሁንና የወረዳችሁን ህዝብ አኩርታችኋል ሲሉም አክለዋል፡፡
‎የትምህርት ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጎሳ ገ/ኪዳም በበኩላቸው በዚህ በችግር ውስጥ ሆናችሁ ይህንን ውጤት ሰላስመዘገባችሁ የወረዳችን ማህበረሰብና ወላጆቻችሁ ኮርተውባችኋል በማለት በተመደባችሁበት ዩኒቭርስቲ ጠንክራችሁ በማንበብና በማጥናት ከዚህ የበለጠ ውጤት በማስመዝገብ ወረዳችሁን ብሎም ሀገራችሁን ማስጠራት ይገባችኃል ሲሉም ምክራቸውን ለግሰዋል፡፡
‎ የወረዳው ምክትል አስተዳዳሪ ዋ/ሳጅን አወቀ ወ/ኪዳን በበኩላቸው እናንተ ለበረኸት ወረዳ ህዝብ አምባሳደሮች ናችሁ ወረዳችንን አኩርታችኋል በማልት ይህ ውጤት የመጨረሻ ምእራፍ አይደለም በተመደባችሁበት ዩኒቨርስቲ ጠንክራችሁ በማንበብ ከዚህ የበለጠ ውጤት እንድታመጡ በወረዳው ህዝብ ስም አደራቸውን አስረክበዋል፡፡
‎በመጨረሻም ሽልማቱን ከወረዳ ምክትል አስተዳደሪ ከአወቀ ወ/ኪዳንና ከግብርና ፅ/ቤት ኃላፊ ከአቶ ደምሰው ሻውል ተረክበዋል፡፡
ተጨማሪ መረጃዎችን ከበረኸት ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ለማግኘት ቀጣዮቹን ሊንኮች ይጫኑ።
Facebook : https://www.facebook.com/Berhetwerdacommu
Telegram ፡ https://t.me/+Ygpdxi4KijkwNGU0
Twitter : https://twitter.com/BerhetC
You Tube : www.youtube.com/
Ticktock : www.tiktok.com/.woreda.com

የዞኑ ኮሙንኬሽን መምሪያ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት አፈፃፀም 3ኛ በመውጣት ተሸላሚ ሆነደብረ ብርሃን፤ ነሃሴ 27 ቀን 2018 ዓ.ም (ሰሸዞመኮ) የሰሜን ሸዋ ዞን የመንግስት ኮሙንኬሽን መምሪያ...
02/09/2026

የዞኑ ኮሙንኬሽን መምሪያ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት አፈፃፀም 3ኛ በመውጣት ተሸላሚ ሆነ

ደብረ ብርሃን፤ ነሃሴ 27 ቀን 2018 ዓ.ም (ሰሸዞመኮ) የሰሜን ሸዋ ዞን የመንግስት ኮሙንኬሽን መምሪያ በ2018 በጀት ዓመት አፈፃፀሙ ከዞንች ተወዳድሮ 3ኛ በመውጣት ዕውቅናና ሽልማት ተቀበለ።

ሽልማቱን የተቀበሉት የዞኑ መምሪያ ኃላፊ አቶ ተማለደ በላይሁን ለተገኘው የላቀ ውጤት በየደረጃው ያለው አመራርና ባለሙያ እንዲሁም አጋር አካላተ የላቀ በመሆኑ እንኳን ደስ ያላችሁ ብለዋል።

‎በረኸት ወረዳ ጠቅላላ አመራር በ15 ቀን የተሰሩ ስራዎችን በመገምገም የቀጣይ ሳምንት የስራ አቅጣጫ ተቀመጠ!! ‎‎መጥተህ ብላ ነሐሴ 27/2018ዓ/ም‎‎በሰሜን ሸዋ ዞን በረኸት ወረዳ  በ1...
02/09/2026

‎በረኸት ወረዳ ጠቅላላ አመራር በ15 ቀን የተሰሩ ስራዎችን በመገምገም የቀጣይ ሳምንት የስራ አቅጣጫ ተቀመጠ!!

‎መጥተህ ብላ ነሐሴ 27/2018ዓ/ም

‎በሰሜን ሸዋ ዞን በረኸት ወረዳ በ15 ቀን የተከናወኑ ተግባራትን በመገምገም የቀጣይ ሳምንት የስራ አቅጣጫ ተቀምጧል።
‎በስራ ግምገማው የወረዳ ጠቅላላ አመራሩ የተሳተፉ ሲሆን በዋነኝነት የፖለቲካ፣የሰላም፣ልማትና የመልካም አስተዳደር ጥቅል ስራዎች ተገምግመዋል።
‎በዚህ የግምገማ መድረክ የመድረክ አፈፃፀም የህዝብ ግንኙነት ስራዎች ፤ የተማሪ ምዝገባ አፈጻጸም ፣ የፋይዳ መታወቂያን ማስጠቀም ፣ የገቢ አሰባሰብ ፣ የስራ ፈላጊ ምዝገባ፣ የክረምት በጎ ፍቃድ ፣የኑሮ ዉድነት ፥ የሃይል ማሰባሰብ ስራና ሌሎችም ተግባራት አሁናዊ አፈፃፀማቸው ተገምግሟል።
‎መድረኩን የበረኸት ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪና ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አወቀ ወ/ኪዳን የመሩት ሲሆን ለተነሡ ሃሳቦች ተገቢውን ማብራሪያና ምላሽ በመስጠት ፤የቀጣይ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ መድረኩ ተጠቃሏል ።
ተጨማሪ መረጃዎችን ከበረኸት ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ለማግኘት ቀጣዮቹን ሊንኮች ይጫኑ።
Facebook: https://www.facebook.com/Berhetwerdacommu
Telegram ፡ https://t.me/+Ygpdxi4KijkwNGU0
Twitter: https://twitter.com/BerhetC
You Tube: www.youtube.com/
Ticktock: www.tiktok.com/.woreda.com

"የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ በክልሉ ሰላምና ልማት እንዲረጋገጥ የድርሻውን እየተወጣ ነው" -አቶ አባይ መንግሥቴ​የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት አጠቃላ...
02/09/2026

"የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ በክልሉ ሰላምና ልማት እንዲረጋገጥ የድርሻውን እየተወጣ ነው" -አቶ አባይ መንግሥቴ

​የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት አጠቃላይ የሥራ አፈጻጸም፣ የተመዘገቡ ስኬቶችና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን የሚገመግም መድረክ እያካሄደ ነው።

​በመድረኩ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግርና የሥራ መመሪያ ያስተላለፉት የቢሮው ሃላፊ አቶ አባይ መንግሥቴ፤ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መረጃ ለሕዝብ ከማድረስ ባሻገር በክልሉ ሰላም፣ መረጋጋትና ልማት እንዲሰፍን ታሪካዊ ሚና እየተወጣ እንደሚገኝ ገልጸዋል። አክለውም በክልሉ ለተገኘው የሰላም አየርና ለሕዝቡ አብሮነት መጎልበት ዘርፉ ከፍተኛ ድርሻ ማበርከቱን አብራርተዋል።

​በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ተግባራት የዘርፉን ኃያልነት በተግባር ያረጋገጡ እንደነበሩ የጠቆሙት ሃላፊው፤ እነዚህ ሥራዎች የሕዝቡን የልማት እንቅስቃሴ የሚያፋጥኑ፣ እውነትን የሚያጎሉና የክልሉን መልካም ገጽታ በመገንባት ረገድ ትልቅ አስተዋጽኦ ማበርከታቸውን ገልጸዋል።

​በተጨማሪም በበጀት ዓመቱ የተካሄደው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ዲሞክራሲያዊ፣ ፍትሐዊና ተዓማኒ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ የተወጣው ሚና በታሪክ የሚዘከር መሆኑን ጠቅሰዋል።

​ዘርፉ የማህበረሰቡን ሁለንተናዊ የልማት ፍላጎት በማንጸባረቅ ረገድ የተጫወተው ሚና ለልማት ሥራዎች መፋጠን ትልቅ አቅም መሆኑንም አቶ አባይ አብራርተዋል።

​በመድረኩ ያለፉትን ስኬቶችና ያጋጠሙ ማነቆዎችን በመፈተሽ፤ በቀጣይ የበጀት ዓመት የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ዘርፉ ለክልሉ ዘላቂ ሰላም፣ ወንድማማችነትና ሁለንተናዊ እድገት በላቀ ኃላፊነት እንዲሠራ መንገድ የሚጠርግ መሆኑ ተመላክቷል።

AmharaCommunications

‎" ውጫዊ የወረራ ስጋት እና ውስጣዊ የፅንፈኝነት አደጋን በመቀልበስ ዘላቂ ሰላምና ልማት እናረጋግጣለን" በሚል መሪ ሃሳብ ከሴቶችና ከወጣቶች ጋር የውይይት መድረክ ተካሄደ ።‎‎በሰሜን ሸዋ ...
01/09/2026

‎" ውጫዊ የወረራ ስጋት እና ውስጣዊ የፅንፈኝነት አደጋን በመቀልበስ ዘላቂ ሰላምና ልማት እናረጋግጣለን" በሚል መሪ ሃሳብ ከሴቶችና ከወጣቶች ጋር የውይይት መድረክ ተካሄደ ።

‎በሰሜን ሸዋ ዞን በረኸት ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅርጫፍ ጽ/ቤት አስተባባሪነት " ውጫዊ የወረራ ስጋት እና ውስጣዊ የፅንፈኝነት አደጋን በመቀልበስ ዘላቂ ሰላምና ልማት እናረጋግጣለን" በሚል መሪ ቃል ከሴቶችና ከወጣቶች ጋር የምክክር መድረክ ተካሂዷል።
‎ በመድረኩ ሴቶችና ወጣቶች የሰላም ተምሳሌቶች በመሆን ተወናብደው ወደ ፅንፈኛው አካል ገብተው ጦርነት ውስጥ ያሉና የህውሀት ለፖለቲካ መነገጃ የሆኑ ልጆቻቸውን እንዲሁም ቤተሰቦቻቸውን ወደ ሰላም እንዲመለሱ በማድረግ እንደ ሀገር የገጠሙንን ፈተናዎች ለመውጣት በጋራ ጥረትና በተባበረ ክንድ በመመከት የክልላችን ብሎም የሀገራችንን ሰላምና ደህንነት በማረጋገጥ የተጀመረውን የብልጽግና ጉዞ እንዲያረጋግጡ ጥሪ ቀርቧል ።
‎ ትህነግ ከውልደቱ ጀምሮ ከፋፍሎ በመግዛትና በዋናነት የአማራ ክልል ህዝብ እረፍት እንዲያጣ አልሞ የሚሰራ ድርጅት መሆኑን ህዝባችን በተለይም ወጣቶችና ሴቶች እውነታውን በመረዳት ለሰላም ፋና ወጊ በመሆን ለሀገር ህልውናና ደህንነት የድርሻቸውን መወጣት እንደሚያስፈልጋቸው ተገልጿል።
ተጨማሪ መረጃዎችን ከበረኸት ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ለማግኘት ቀጣዮቹን ሊንኮች ይጫኑ።
Facebook: https://www.facebook.com/Berhetwerdacommu
Telegram ፡ https://t.me/+Ygpdxi4KijkwNGU0
Twitter: https://twitter.com/BerhetC
You Tube: www.youtube.com/
Ticktock: www.tiktok.com/.woreda.com

በ2018 በጀት ዓመት የላቀ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ዞኖችና ከተማ አስተዳደሮች እውቅና እና ሽልማት ተበረከተላቸውየአማራ ክልል ከፍተኛ እና መካከለኛ መሪዎች ለተከታታይ ቀናት ሲካሄድ የነበረው የ...
01/09/2026

በ2018 በጀት ዓመት የላቀ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ዞኖችና ከተማ አስተዳደሮች እውቅና እና ሽልማት ተበረከተላቸው

የአማራ ክልል ከፍተኛ እና መካከለኛ መሪዎች ለተከታታይ ቀናት ሲካሄድ የነበረው የ2018 በጀት ዓመት የፓርቲ እና የመንግሥት ሥራዎች አፈጻጸም ግምገማ እና የ2019 በጀት ዓመት የዕቅድ ትውውቅ መድረክ በዛሬው ዕለት ተጠናቋል።

በመድረኩ ማጠቃለያ በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት በሠላም፣ በልማት በመልካም አስተዳደር እና በፓርቲ ተግባራት የላቀ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ዞኖች እና ከተማ አስተዳድሮች እውቅና እና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

በዚህም የሰሜን ሸዋ ዞን አስተዳደር ከጥቅል የክልሉ ዞኖች 2ኛ ደረጃ በመያዝ የእውቅናና ሽልማት ተበርክቶለታል።

እንኳን ደስ አለን !!

#ሰሜን ሸዋ ዞን ኮሙኒኬሽን ነው

‎"በወረዳው የሚከናወኑ ተግባራትን ከፋይዳ ዲጅታል መታወቂያ ጋር ማስተሳሰር ይገባል፡፡"‎‎አቶ ወርቁ አበበ፡ የበረኸት ወረዳ አስተዳደር ጽህፈት ቤት ሀላፊ‎‎በሰሜን ሸዋ ዞን በረኸት ወረዳ ተ...
01/09/2026

‎"በወረዳው የሚከናወኑ ተግባራትን ከፋይዳ ዲጅታል መታወቂያ ጋር ማስተሳሰር ይገባል፡፡"

‎አቶ ወርቁ አበበ፡ የበረኸት ወረዳ አስተዳደር ጽህፈት ቤት ሀላፊ

‎በሰሜን ሸዋ ዞን በረኸት ወረዳ ተግባራዊ እየተደረጉ ካሉ ኢንሼቲቮች አንዱ የሆነው የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባና ከተግባራት ጋር ማስተሳሰርን በተመለከተ የግምገማ መድረክ ተካሄደ።

‎መጥተህ ብላ፡ ነሀሴ 26/2018 ዓ.ም (በወመኮ)

‎በመድረኩ የሚመለከታቸው ሴክተር መስሪያ ቤት አመራሮችና ተወካዮች፣ የቴሌ ኮሙዩኒኬሽን፣ የዳሸን እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መጥተህ ብላ ቅርንጫፍ ስራ አሰኪያጆች እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።

‎በወረዳችን የሚከናወኑ ሁሉም ተግባራት ከፋይዳ ዲጅታል መታወቂያ ጋር መተሳሰር እንዳለበት ያሳሰቡት የወረዳው አስተዳደር ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ወርቁ አበበ፡ ተግባራዊ ከሚደረጉት ኢንሼቲቮች አንዱ የሆነው የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ በወረዳው ትኩረት ተሰጥቶ መሰራት እንዳለበት በአጽንኦት ተናግረዋል።

‎የበረኸት ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ሀላፊ ወ/ሮ እንጎቻ በየነ በበኩላቸው፡ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ (National ID) ለሁሉም ማህበረሰብ ተደራሽ እንዲሆን በተጠናከረ እና በተደራጀ ሁኔታ ማህበረሰቡ እንዲመዘገብ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ርብርብ ማድረግ አለባቸው ብለዋል።

‎የፋይዳ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ የህዝብና የመንግስት አገልግሎቶችን የሚያሳልጥ በመሆኑ ሁሉም ማህበረሰብ ዲጅታል መታወቂያ ማሰራትና መያዝ እንዳለበት የጠቆሙት ሀላፊዋ፡ ተቋማት የሚሰጡትን አገልግሎት ከፉይዳ ዲጅታል መታወቂያ ጋር ማስተሳሰር እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል።

‎የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ዘርፈ ብዙ ጥቅሞች ያሉትና ሁሉም ማህበረሰብ በመላው ሀገሪቱ ተንቀሳቅሰው ልዩ ልዩ አገልግሎት ማግኘት የሚችሉበት በመሆኑ በዲጅታል መታወቂያ ላይ የሚታዩ ጉድለቶችን የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ፈጥነው በማስተካከል ዘመኑን የዋጁ ተግባራትን ማከናወን እንደሚገባ ተገልጿል።

‎ይህ በዚህ እንዳለ የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን ለመፍታት የዲጅታል መታወቂያ ምዝገባ የሚያካሂዱ አካላት ከእናት መስሪያ ቤታቸው ጋር የቅርብ ግንኙነት መፍጠር እንደሚገባም ተሳታፊዎች ገልጸዋል።

‎የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥና የዲጅታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ከሚያግዙ ነገሮች አንዱ የፋይዳ ብሄራዊ ዲጅታል መታወቂያ ድርሻው የላቀ መሆኑን በመረዳት ህብረተሰቡ በወቅቱ በመመዝገብ መታወቂያውን እንዲይዝ ሰፊ የግንዛቤ ፈጠራ ስራ መስራት እንደሚገባ ከመድረኩ ተመላክቷል።

‎በመጨረሻም ተሳታፊዎች በርካታ አስተማሪና ከችግር የሚያወጣ ሀሳብ አስተያየት የሰነዘሩ ሲሆን ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በቂ ማብራሪያ በመስጠትና የቀጣይ አቅጣጫ በማስቀመጥ መድረኩ ተጠናቋል።
ተጨማሪ መረጃዎችን ከበረኸት ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ለማግኘት ቀጣዮቹን ሊንኮች ይጫኑ።
Facebook: https://www.facebook.com/Berhetwerdacommu
Telegram ፡ https://t.me/+Ygpdxi4KijkwNGU0
Twitter: https://twitter.com/BerhetC
You Tube: www.youtube.com/
Ticktock: www.tiktok.com/.woreda.com

Adresse

Berhet
09

Téléphone

0224720090/87

Site Web

Notifications

Soyez le premier à savoir et laissez-nous vous envoyer un courriel lorsque Berhet woreda communication publie des nouvelles et des promotions. Votre adresse e-mail ne sera pas utilisée à d'autres fins, et vous pouvez vous désabonner à tout moment.

Contacter L’organisation

Envoyer un message à Berhet woreda communication:

Raccourcis

Partager