Boditti Times 360

Boditti Times 360 Mind set; to spread Positive vibe for humanbeing and to let them logical for decision
(1)

በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በስፋት እየተዘዋወረ የሚገኝ አንድ አጭር ቪዲዮ የብዙዎችን ልብ የነካና ታላቅ መነጋገሪያ ሆኗል። ክስተቱ አንድ የገጠር ታዳጊ የሚወዳት ዶሮው በድንገት ስትታመምበት፣ የሰ...
10/06/2026

በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በስፋት እየተዘዋወረ የሚገኝ አንድ አጭር ቪዲዮ የብዙዎችን ልብ የነካና ታላቅ መነጋገሪያ ሆኗል። ክስተቱ አንድ የገጠር ታዳጊ የሚወዳት ዶሮው በድንገት ስትታመምበት፣ የሰዎች ህክምና መስጫ ወደሆነ ሆስፒታል ይዞ በመምጣት ሊያሳክማት የሞከረበት እውነተኛና የየዋህነት ታሪክ ነው።

ታዳጊው ዶሮዋን በአረንጓዴ ነጠላ በጥንቃቄ ጠቅልሎና በክንዱ አቅፎ ወደ ሆስፒታሉ ግቢ ይዞ የገባ ሲሆን፣ በወቅቱ ያነጋገረው ግለሰብ ስለ ዶሮዋ ሁኔታ ሲጠይቀው በጥልቅ ጭንቀት ውስጥ ሆኖ ምላሽ ይሰጣል። ዶሮዋ ከፍተኛ የሰውነት ሙቀት ወይም ትኩሳት እንዳላት፣ ክንፎቿን እንደጣለችና ሆዷንም እያመማት እንደሆነ በንፁህ ህሊና ያስረዳል።

በቦታው የነበረውና ቪዲዮውን የቀረጸው ግለሰብ ታዳጊውን በማረጋጋት ይህ ሆስፒታል ለሰዎች ብቻ የሚሰጥ የህክምና ተቋም መሆኑን ያስረዳዋል። የቤት እንስሳትና ከብቶች የሚታከሙበት የተለየ የክሊኒክ ቦታ እንዳለና እዛ መውሰድ እንዳለበት ሲነግረው፣ ታዳጊው እውነታውን ተረድቶ ዶሮውን እንደታቀፈ ወደ መጣበት ለመመለስ ከሆስፒታሉ በር ወጥቶ ጉዞውን በሰላም ይጀምራል።

ይህ ክስተት በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ለብዙዎች ፈገግታንና መደነቅን ቢፈጥርም፣ በጀርባው ግን ትልቅ ሰብአዊ መልዕክትን ያዘለ ነው። የታዳጊው ንጹህ ህሊና እና ለእንስሳቱ ያለው ጥልቅ ፍቅርና የመንከባከብ ኃላፊነት እጅግ የሚደነቅ ነው። በተመሳሳይ መልኩ ክስተቱ በገጠሪቱ የሀገራችን ክፍሎች ያለውን የእንስሳት ህክምና ተደራሽነት ክፍተት እና መሰረታዊ የሆኑ የግንዛቤ ስራዎችን ለህብረተሰቡ ማድረስ ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ ትልቅ ማሳያ ሆኖ አልፏል።

ደሞዙ ከ 20 ሺ እንደማይበልጥ የሚነገርለት አቶ ሽመልስ አብዲሳ  የ 20 ሚልየን ብር ሰዓት አድርጎ መታየቱ አነጋጋሪ ሆኗል...🤔🤔🤔
10/06/2026

ደሞዙ ከ 20 ሺ እንደማይበልጥ የሚነገርለት አቶ ሽመልስ አብዲሳ የ 20 ሚልየን ብር ሰዓት አድርጎ መታየቱ አነጋጋሪ ሆኗል...🤔🤔🤔

06/06/2026

ከአርሰናል አርሲ ይቀርበናል።
ስታዲየም ገብታችሁ ለመጨፈር ያሰባችሁ ባለ ማኅተቦች ሆይ ወደ ራሳችሁ ተመለሱ።

‎🌍 የዓለም ዋንጫ ሰኔ 04 ሐሙስ ይጀመራል !‎=============================‎የ2026ቱ የዓለም እግርኳስ ዋንጫ በአሜሪካ፣ በሜክሲኮና ካናዳ ጣምራ አዘጋጅነት ከሰኔ 04 እስ...
05/06/2026

‎🌍 የዓለም ዋንጫ ሰኔ 04 ሐሙስ ይጀመራል !
‎=============================
‎የ2026ቱ የዓለም እግርኳስ ዋንጫ በአሜሪካ፣ በሜክሲኮና ካናዳ ጣምራ አዘጋጅነት ከሰኔ 04 እስከ ሐምሌ 12/20/18 ዓም ድረስ በ48 ሀገራት መካከል ለመጀመሪያ ግዜ ይካሄዳል ።

‎በአጠቃላይ ከሰባት አህጉራት የተውጣጡ 48 ሀገራት በ12 ምድብ ተደልድለዋል ። ከአውሮፓ 16፣ ከአፍሪካ 10፣ ከኤጂያ 9፣ ከሴሜንና መካከለኛ አሜሪካ 6፣ ከደቡብ አሜሪካ 6፣ ከኦሺኒያ 1 ተሳታፊ ይሆናሉ ።

‎የመክፈቻ ጨዋታ በሜክሲኮ እና በደቡብ አፍሪካ መካከል ሰኔ 04 በስታዲዮ አዚተካ ሜክሲኮ ከተማ ይደረጋል።

‎ኡዝበኪስታን፣ ጆርዳን፣ ኩራካዎና ኬፕ ቬርድ በታሪካቸው ለመጀመሪያ ግዜ በአለም ዋንጫ ይሳተፋሉ ። የሰሜን አሜሪካዋ ኩራካዎ 150 ሺ ህዝብ ብቻ ያላት ትንሿ ተሳታፊ ሀገር ናት ።

‎ብራዚል አምስት ግዜ ሻምፒዮን በመሆን ቀዳሚ ስትሆን ጀርመንና ጣሊያን አራት አራት ግዜ አርጀንቲና ደግሞ ለሶስተኛ ግዜ የዓለም ሻምፒዮን የሆኑ ሀገራት ናቸው ። ዘንድሮስ?

‎በአጠቃላይ በ39 ቀናት ቆይታው 104 ጨዋታዎች ተደርጎ ሐምሌ 12 በአሜሪካ ኒውዮርክ ኒውጄርሲ ስታዲየም ፍፃሜውን ያገኛል።

‎የጨዋታ ፕሮግራሞችና ውጤቶችን እየተከታተልን በየትኩሱ ወደ እናንተ እናደርሳለን። በፕሮግራሞቻችን ላይ ማስታወቂያ ማሰራት የምትፈልጉ በውስጥ መስመር አነጋግሩን።

በምሥራቅ አርሲ የተፈጸመው ጥቃት፡ 13 ንጹሐን ተገደሉ፣ ታሪካዊት ቤተክርስቲያን ተቃጠለችአርሲ፡ በአርሲ ሀገረ ስብከት በሚገኙ የተለያዩ ወረዳዎች በግንቦት ወር መጨረሻ በተፈጸመ ጥቃት የ13 ...
02/06/2026

በምሥራቅ አርሲ የተፈጸመው ጥቃት፡ 13 ንጹሐን ተገደሉ፣ ታሪካዊት ቤተክርስቲያን ተቃጠለች

አርሲ፡ በአርሲ ሀገረ ስብከት በሚገኙ የተለያዩ ወረዳዎች በግንቦት ወር መጨረሻ በተፈጸመ ጥቃት የ13 ዜጎች ሕይወት ማለፉን የአርሲና የሶማሌ ክልል ጅግጅጋ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ አስታወቁ።

እንደ ሀገረ ስብከቱ መረጃ ከሆነ፣ ጥቃቱ የተፈጸመው ከአሰኮ፣ ሺርካ እና ሆንቆሎ ዋቤ ወረዳዎች ሲሆን፣ በደረሰው ጥቃት ከ280 በላይ ምዕመናን ከቀያቸው መፈናቀላቸው ታውቋል።

በተፈጸመው ግፍ የአካባቢው ነዋሪዎች መኖሪያ ቤቶች በእሳት መውደማቸውና ንብረቶቻቸው መዘረፉ ተገልጿል።

የ101 ዓመት ዕድሜ ያስቆጠረው የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ሙሉ በሙሉ በእሳት ጋይቷል::

የካራ ኩፍተና መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን በዘረፋ የተጎዳ ሲሆን፣ ምዕመናን የቤተክርስቲያኒቱን ጽላት ይዘው ለመሰደድ መገደዳቸው ታውቋል።

ከጥቃቱ የተረፉት ወገኖች ምንም አይነት ንብረት ሳይዙ ሜዳ ላይ መውደቃቸው የደረሰው ሰብዓዊ ቀውስ ምን ያህል የከፋ መሆኑን ያሳያል።

በጥቃቱ ሕይወታቸው ያለፈው ወገኖች ስም ዝርዝር እንደሚከተለው ቀርቧል፡-

1. አቶ ደምረው አበራ (70)
2. አቶ ከፈለኝ ልክየለው (56)
3. አቶ ሐይሉ ንጉሴ (70)
4. አቶ እሸቴ ዳመና (42)
5. አቶ አበባየሁ ዳኜ (42)
6. አቶ ሰሙ አባይነህ (70)
7. አቶ አማረ በላይነህ (80)
8. አቶ ተሬ ደሴ (25)
9. ወጣት ገነነ ጥላሁን (ሺርካ)
10. ወጣት ሙርቴሳ ጥላሁን (ሺርካ)
11. አቶ ንጉሱ ማንደፍሮ (ሆንቆሎ ዋቤ)
12. አቶ በቀለ ኃይለሚካኤል (ሆንቆሎ ዋቤ)
13. አንድ የመንግስት ሚሊሻ

ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ በተፈጸመው አሳዛኝ ድርጊት የተሰማቸውን ጥልቅ ሐዘን በመግለጽ፣ ለሟች ቤተሰቦች መጽናናትን ተመኝተዋል። "ስለ አንተ ሁልጊዜም ተገድለናል፣ እንደሚታረዱም በጎች ሆነናል።"

"መዝሙር 43፡22) በሚል ጥቅስ የተገለጸው ይህ ዘገባ፣ ችግሩን በዘላቂነት ለመቅረፍ እና የዜጎችን ደህንነት ለማረጋገጥ የሚመለከተው አካል ፈጣን ምላሽ እንዲሰጥ ጥሪ አቅርቧል።

Via የአርሲ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

ታዋቂው እራፐር አርሴናል ያሸንፋል ብሎ በአንድ ሚሊዮን ዶላር ተወራረደ። ወደ ኢትዮጵያ ብር ስንመነዝረው 161,247,000 birr ነው🤔 🚨 𝗕𝗥𝗘𝗔𝗞𝗜𝗡𝗚: Drake has reportedly ...
30/05/2026

ታዋቂው እራፐር አርሴናል ያሸንፋል ብሎ በአንድ ሚሊዮን ዶላር ተወራረደ። ወደ ኢትዮጵያ ብር ስንመነዝረው 161,247,000 birr ነው🤔

🚨 𝗕𝗥𝗘𝗔𝗞𝗜𝗡𝗚: Drake has reportedly placed a $1 MILLION bet on Arsenal to win the Champions League Final against PSG tonight. 🤯

30/05/2026
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባምባሲ ወረዳ መንገድ ላይ የህዝብ ማመላለሻ መኪና አስቁሞ ተሳፋሪዎችን ሲያሰቃይ እና ሲዘርፍ በነበረ የታጠቀ የዘራፊዎች ቡድን ላይ አንድ ያልተጠበቀ ጀግንነት ተመዝግ...
30/05/2026

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባምባሲ ወረዳ መንገድ ላይ የህዝብ ማመላለሻ መኪና አስቁሞ ተሳፋሪዎችን ሲያሰቃይ እና ሲዘርፍ በነበረ የታጠቀ የዘራፊዎች ቡድን ላይ አንድ ያልተጠበቀ ጀግንነት ተመዝግቧል። ዘራፊዎቹ መኪናውን ዘግተው የሰዎችን ገንዘብ እየለቀሙ በድምሩ ከ6 ሚሊዮን 117 ሺህ ብር በላይ በእጃቸው አስገብተው በነበረበት በዚያ አስፈሪ ሰዓት ላይ ነው ረዳት ኢንስፔክተር ወግድ ወምፑ የተባለው የኮሚኒቲ ፖሊስ አባል ለብቻው ደርሶ ተአምር የሰራው።

ረዳት ኢንስፔክተር ወግድ ንጹሃን ዜጎች ሲንገላቱና ጥሪታቸውን ሲቀሙ ሲመለከት ለአፍታም አላንገራገረም፤ ወይም የኃይል እገዛ እስኪመጣ አልጠበቀም። ወዲያውኑ የታጠቁትን ወንበዴዎች ለብቻው ፊት ለፊት በመጋፈጥ ከባድ የተኩስ ልውውጥ ውስጥ ገባ። በዚህ ፍጹም የጀግንነት ውጊያ የዘራፊዎቹን ጉልበት መስበር የቻለው ይህ ፖሊስ፣ በቡድኑ ላይ የማያወላውል እርምጃ በመውሰድ አንዱን የሰደፍ ክላሽ ጠመንጃ ከነ20 ጥይቱ ማርኮታል። ይህ የብቸኛ ሰው ቆራጥነት የዘረፋውን መስመር ሙሉ በሙሉ አበላሽቶታል።

ይህን ተከትሎ ነው እንግዲህ የወረዳው ፖሊስና ሚሊሻዎች አካባቢው ላይ ደርሰው አሰሳ በማድረግ፣ በጀግናው ፖሊስ የተበተነውን የዘራፊዎች ቡድን አባላት በቁጥጥር ስር ማዋል የቻሉት። በክትትሉም ከህዝቡ ተዘርፎ የነበረው ሙሉ 6,117,550 ብር እና ዘራፊዎቹ ለምግብነት ይዘውት የነበረው ብስኩት ሳይቀር ሊመለስ ችሏል። ምንም እንኳን የባምባሲ ወረዳ ፖሊስ ጽህፈት ቤት ከክስተቱ በኋላ የተለመደውን የ"መረጃ ስጡ" እና የምስጋና መግለጫ ቢያወጣም፣ የዕለቱ እውነተኛ ታሪክ ግን ለብዙዎች ህይወትና ንብረት መዳን ብቸኛ ምክንያቱ የሆነው የዚህ የፖሊስ አባል አስገራሚ የልብ ጥንካሬና ጀግንነት ነው።

Address

Wolaita
S**o

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Boditti Times 360 posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Boditti Times 360:

Share