08/08/2026
ውስብስብ ሀገራዊ ፈተናዎችን እና ዘላቂ መፍትሔ የሚሹ ጉዳዮችን በጠረጴዛ ዙሪያ ለመፍታት ታስቦ የተጀመረው ሀገራዊ ምክክር እነሆ ዛሬ በየ500 ቡድን የመጨረሻ ምክረ ሀሳብ ቀርቦ በማጠቃለያ 4000 ላይ ለውሳኔ የሚቀርቡ ለቀጣይ ትውልድ ዘላቂ የመፍትሄ ሀሳብ እንድሆን እኛም በየቡድናችን ጠንካራ የሀሳብ መግት በማድረግ የሕዝባችንን አንገብጋቢ አጀንዳዎችን ከኢትዮጵያ ሀገራችን መጻኢ ዕድል ጋር እንድታይ በአጽኖት አስመዘግበናል ..💪
ከአጀንዳዎች መኃል እነዚህን በዋናነት አስመዘግበናል👇
1. ☞ ታላቁ የዎላይታ ሕዝብ ለሀገር ግንባታ ባለፉት ጊዜያቶች ለሀገርቱ አንድነት፥ ለነጻነትና ለዲሞክራሲ የከፈለው ውድ ዋጋ አንጻር የሕዝባችን ታርክ በኢትዮጵያ ታርክ ውስጥ በተገቢይው አልተቀመጠምና በቀጣይ በሚዘጋጀው በጋራ ኢትዮጵያ ታሪክ ላይ የሕዝባችን ታርክ በጉልህ እንዲመዘገብ በ500 ቡድን አጽድቀን ለማጠቃለያው ለ4000 ብድን አሸጋግረናል።
2. ☞ ከደቡብ እስከ ሞያሌ በከፍል የሚደመጥ ቋንቋችን #ዎላይትኛን ስድስተኛ የሀገሪቱ የሥራ ቋንቋ እንድሆን አጄንዳ አስዘናል፤
3. ☞ ኢ_ህገመንግስታዊ በሆነ መንገድ የተነጠቅነውን ዎላይታ ብሔራዉ ክልላዊ መንግስትን የመመስረት መብት በመሆኑ ለታላቁ ዎላይታ ህዝብ መብቱ ልከበርለት ይገባል።
4. ☞ ለአራት /ለ4 አመታት በመዋቅራዊ ሴራ በዎላይታ ህዝብ እየደረሰ ያለው ኢ-ፍትሀዊ የሀብት ክፍፍል፣ ኢ-ፍታሃዊ የፖለቲካና የማህበራዊ ውክልና በአስቾካይ ቆሞ በሁሉም ዘርፍ ትክክለኛ ፍታሃዊነት በተገቢይው ይረጋገጥ።
5. ☞ በተለያዩ ኃላፊነት ደረጃ ላይ እያሉ የህዝብን ውስን ሀብት እና የመንግስትን በጀትን በተደራጀ ሌብነት በማጥፋት ህዝብ በመንግስት ላይ እንዲማረር በሚያደርጉ ባለስልጣናት ላይ የተጠናከረ ክትትልና አስተማሪ የእርምት እርምጃ እንዲወሰድ በዋናነት በምክክሩ ካስመዘገብናቸው እና ወደ ቀጣዩ መጨረሻ ዙር ካሸጋገርናቸው አጀንዳዎች አንኳሮች ናቸው።
#ማሳሰቢያ፦ ይህ የዛሬ ለዛውም የአሁኑ በመሆኑ ዶ/ር ወልደማሪያም ሊሳኑ ታስሯል የሚባለው የሟርት መረጃ አሉባልታ በመሆኑ በዚህ አጋጣም እንድታውቁ ጭምር እናሳስባለን 🤓