Bench Maji Development Association

Bench Maji Development Association Bench Maji Development Association Is a local Non Governmental and Non Political Organization .

በክልሉ ጥራት ያለው የጤና አገልግሎትን ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ መሆኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጤና ቢሮ የበሸታዎች መከላከልና የጤና ማጎልበት የዳ...
15/07/2026

በክልሉ ጥራት ያለው የጤና አገልግሎትን ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ መሆኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጤና ቢሮ የበሸታዎች መከላከልና የጤና ማጎልበት የዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶ/ር እንዳሌ ሳህለ ገለጹ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጤና ቢሮ የበሸታዎች መከላከልና የጤና ማጎልበት የዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶ/ር እንዳሌ ሳህለ በሸኮ ወረዳ በሺሚና በግዝመሬት ቀበሌ ጤና ተቋማትን እና ሞደል ቤተሰብ መስክ ጉብኝት መልስ ማጠቃለያ ግብረ መልስ ሰጥቷል።

በማጠቃለያ መድረክ የመወያያ ሰነድ በበሽታ መከላከል እና በእናቶችና ህጻናት እንዲሁም በቤንች ማጂ ልማት ማህበር የተሰሩ ስራዎችን የሚዳስስ ሰነድ ቀርቦ ዉይይት ተደርጎበታል።

ዶ/ር እንዳለ ሳህሌ እንደተናገሩት፣የክልሉ ጤና ቢሮ ጥራት ያለው የጤና አገልግሎትን ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ ትኩረት ሰጥቶ እየተሰራም ይገኛል።

በወረዳው የዜጎችን ጤናን ለመጠበቅ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት አመርቂ ውጤት መሆናቸውን የገለፁት ዶ/ር እንዳለ ይህንኑ ለማጠናከር ዘርፈብዙ ተግባራት እየተከናወኑ ስለመሆናቸው ተናግሯል።

በዚህም የጤና አገልግሎት አሰጣጥን ማዘመን እና ግብዓቶችን የሟሟላት ስራን ጨምሮ ሌሎች በርካታ ተግባራት አጠናክሮ ማስቀጠል እንዳለበት አሳስቧል።

ወረዳው በጤናዉ ዘርፍ ከዚህን ቀደሞ ሞደል እና ግንባር ቀደም በመሆን በፌደራል ደረጃ እዉቅና የነበረ ሞሆኑን የጠቆሙት ዶ/ር እንዳለ አሁን ላይም ወደ ቀድሞ ለመመለስ በጤናው ዘርፍ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ጥሩ ነገር እንዳለ እና ድጋፍዊ ክትትል የሚፈልግ መሆኑንም ተናግሯል።

የወረዳዉ ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ተስፋነሽ እናቶች በሰለጠነ የጤና ባለሙያ እንዲወልዱ በቂ ክትትል በማድረግና በልማት ቡድን ደረጃ ግንዛቤ በመስጠት እየተሰራ እንደሆነ ገልጻለች።

ቤንች ማጂ ልማት ማህበር እና jsi ድርጅት ጤናን ለማሳለጥ ባደረግነው ስራችን ላደረጉት ድጋፍ እጅግ ለቅ አድርገው ኃላፊዋ አምስግናለች።

በጤና ዘርፍ በቀጣይ ጊዜያት የተሻለ ስራ ለማከናወን በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት በመፍጠር መድረኩ ተጠናቋል።
ከሸኮ ወረዳ መንግስት ኮሚንኬሽን የተወሰደ

የቤንች ማጂ ልማት ማህበር ከJSI ጋር በመተባበር በሸኮ ወረዳ እየተገበረ የሚገኘውን የጤና ልማት ስራዎች አፈጻጸም በሸኮ ወረዳ ሸኮ ከተማ ገመገመ።በመድረኩ ፕሮጀክቱ ከልማት ማህበሩ ጋር በመ...
14/07/2026

የቤንች ማጂ ልማት ማህበር ከJSI ጋር በመተባበር በሸኮ ወረዳ እየተገበረ የሚገኘውን የጤና ልማት ስራዎች አፈጻጸም በሸኮ ወረዳ ሸኮ ከተማ ገመገመ።

በመድረኩ ፕሮጀክቱ ከልማት ማህበሩ ጋር በመተባበር እያከናወነ ባለው ተግባር በእናቶችና ጨቅላ ህጻናት ፣ በጤና ተቋማት አደረጃጀትና የባለሙያዎችን አቅም በመገንባት ረገድ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማበርከቱም ተገልጿል።

ሚዛን አማን ሀምሌ 07/2018

የቤንች ማጂ ልማት ማህበር ከ ጄስአይ (JSI) ጋር በመሆን በባለፉት ወራት በፕሮጀክቱ እና በመደበኛው የጤና ትራንስፎርሜሽን አጀንዳ የተሰሩ የአፈፃፀም ሪፖርት ግምገማ መድረክ አካህደዋል።

በሸኮ ወረዳ በ2018 ዓም ከተሰሩ የአፈፃፀም ሪፖርት ግምገማ በተጨማሪ በግዝሜረት ጤና ጣቢያና በሺሚ መሰረታዊ ጤና ኬላ የተሰሩ ስራዎችን ጨምሮ እስከ ግለሰብ መኖሪያ ቤቶች አጠቃላይ የጤና ኤክስቴሽ ስራዎች ያሉበት የመስክ ምልከታ ተደረገዋል።
በመድረኩ ተገኝቶ መድረኩን የመሩት የክልል ቢሮ ተወካይ እና የክልሉ ጤና ቢሮ በሽታ መከላከል እና ጤና ማጎልበት ዳይሮክቶሬት ዳይረክተር የሆኑት ዶክተር እንዳለ ሳህለ እንዳሉት በወረዳው በጤናዉ ዘርፍ የተፈፀመው ተግባራት እስከታችኛው እባወራ ቤት ድረስ በታየዉ ምልከታ ወረዳዉ በአጭር ጊዜ ተጨባጭ ለዉጥ እያስመዘገበ መሆኑን በመስክ ምልከታዉ ማረጋገጥ መቻሉ ይህም በእናቶች እና ህፃናት ሞት ቅነሳ ላይ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማበርከቱን ገልፀዋል።
በመድረኩ የልማት ማህበሩ ቦርድ ሰብሳቢ የሆኑት ክቡር አቶ ጨነቁ ኮንታርን ጨምሮ የልማት ማህበሩ አመራሮች፣ከክልሉ ጤና ቢሮ፣ከዞኑ ጤና መምሪያ እና ከወረዳዉ ጤና ፅ/ቤት አመራሮች እና የምመለከታቸዉ ከፍተኛ ባለሙያዎች እንድሁም ከሁሉም ጤና ጣብያ እና ጤና ኬላ የተወጣጡ የጤና ባለሙያዎች ተገኝተዋል።
መድረኩ ከመስክ ምልከታ መልስ በቤንች ማጂ ልማት ማህበር JSI ፕሮጀክት በወረዳው የተሰሩ የአቅም ግንባታ እና ድጋፍ ስራዎች አፈፃፀም እንድሁም የወረዳው የበጀት ዓመት የጤና ዘርፍ አፈፃፀም ሪፖርት ቀርቦ ዉይይት የተደረገበት ስሆን በነገው እለትም እንደምቀጥል ከተዘጋጀው መርሀግብር ለማወቅ ተችሏል።
ልማት የጋራ ጥረት ዉጤት ነው !!

የቤንች ማጂ ልማት ማህበር የባለ ልዩ ተሰጥኦ አዳሪ ትምህርት ቤት የመጀመሪያዎቹ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተናቸውን በሰላም አጠናቀቁ፡፡ሀምሌ 1/2018 ዓም የቤንች ማጂ ልማት ማህበር ...
10/07/2026

የቤንች ማጂ ልማት ማህበር የባለ ልዩ ተሰጥኦ አዳሪ ትምህርት ቤት የመጀመሪያዎቹ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተናቸውን በሰላም አጠናቀቁ፡፡
ሀምሌ 1/2018 ዓም የቤንች ማጂ ልማት ማህበር የባለ ልዩ ተሰጥኦ አዳሪ ትምህርት ቤት የመጀመሪያዎቹ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና በሰላም ተጠናቀዋል፡፡
ልማት ማህበሩ ለመጀመሪያ ጊዜ በ2015 ዓም ከዞኑ ከሁሉም መዋቅሮች ከ8ተኛ ክፍል ወደ 9ኛ ክፍል የተዛወሩ 50 ተማሪዎችን በመቀበል ከቤንች ሸኮ ዞን አስተዳደር፤ከሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ እና ከሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ጋር በመተባበር በራስ አቅም የተማሪዎችን ሙሉ የትምህርት ግብአት፤ምግብ፤ መኝታን እና ህክምና ወጪዎችን ሙሉ በሙሉ በመሸፈን ለ4 ተከታታይ ዓመታት ካስተማራቸው የመጀመሪዎቹ ተማሪዎች መካከል 39 ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ መግብያ ፈተና በሰላም አጠናቀዋሉ፡፡
ተማሪዎቹ ፈተናውን ባጠናቀቁበት ሰዓት ተገኝቶ መልእክት ለተማሪዎቹ ያስተላፉት የልማት ማህበሩ ዋና ስራ አስክያጅ አቶ አጽናኝ ፈለቀ ተማሪዎቹ ባለፉት 4 ዓመታት ያሳዩት ቁርጠኝነት፤ጽናት እና አንድነት በምቀጥሉት ፈታኝ የትመህርት ህደቶችም ተጠናክሮ እንድቀጥል የጠየቁ ሲሆን ተማሪዎቹ የመጀመሪያው ተማሪዎች እንደመሆናቸው መጠን በርካታ የትምህርት ግብአት ሳይሟላላቸው በራሳቸው ጥረት እና በመምህራን ትጋት ለዛሬ መብቃታቸውን የገለጹት ስራ አስክያጁ እንደዞን በዞኑ ታርክ የምያኮራ ውጤት እንደምያስመዘግቡ እንደምተማመኑ እና በቀጣይም በከፍተኛ ትምህርት እርከኖች በምኖራቸው የትምህርት ወቅት ልማት ማህበሩ ባለው አቅም መጠን ድጋፉን በማጠናከር ከጎናቸው እንደምሆን አረጋግጠዋል፡፡ በመጨረሻም ይህ ትውልድን የማስቀጠል ስራን በማስተባበር ቀጥተኛ በጀት ድጋፍ በማድረግ ስራው እንድቀጥል እና ለዛሬ እንድደር በየደረጃው ያለው የዞኑ ማህበረሰብ ክፍል ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከታቸውን በመግለጽ በተለይም የቤንች ሸኮ ዞን አስተዳደር ፤የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሰቲ እና የሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ያበረከቱት አስተዋጽኦ ከፍተኛ እንደሆነ በመግለጽ በቀጣይም ትምህርት ቤቱ ራሱን አስችሎ ለመተዳደር ለምያደረገው ጥረት ድጋፋቸውን አጠናክሮ እንድያስቀጥሉ ጥሪ በማቅረብ ለተማሪዎች መልካም የእረፍት ጊዜ እና መልካም ውጤትን በመመኘት መልእክታቸውን አጠናቀዋሉ፡፡
ልማት የጋራ ጥረት ውጤት ነው !!

10/07/2026
10/07/2026
የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ህትመት ተጠናቆ ሪክክብ ተካህዷል።የቤንች ማጂ ልማት ማህበር ከቤንች ሸኮ ዞን ትምህርት መምሪያ ጋር በመተባበር የ6ተኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ህትመት በስኬት በማጠናቀ...
13/06/2026

የ6ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ህትመት ተጠናቆ ሪክክብ ተካህዷል።
የቤንች ማጂ ልማት ማህበር ከቤንች ሸኮ ዞን ትምህርት መምሪያ ጋር በመተባበር የ6ተኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ህትመት በስኬት በማጠናቀቅ በዛሬዉ እለት ለዞኑ ትምህርት መምሪያ አስረክበዋል።
በዞኑ ከሁሉም መዋቅሮች ፈተናዉን ለምወስዱ ከ10,200 በላይ ተማሪዎች የአፍ መፍቻ ቋንቋ ትምህርቶችን ጨምሮ ስታንዳርዱን እና የፈተናዉን ደህንነት በጠበቀ ሁኔታ የህትመት ስራዉን በተሳካ ሁኔታ የተከናወነ መሆኑ የተገለፀ ስሆን የህትመት ስራዉን OM ማተሚያ ቤት አስፈላጊውን ግብአት እና የሰዉ ሀይል በሟሟላት ፈተናዉ በተያዘለት ጊዜ እንድጠናቀቅ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማበርከቱም ተገልፆዋል።
​የፈተና ሪክክብ ስረዓቱ በዞኑ ፖሊስ መምሪያ የዞኑ ትምህርት መምሪያ ሀላፍ አቶ አገኘሁ ወርቁ በተገኙበት ሪክክብ የተካሄደ ሲሆን ፈተናዉ በዛሬዉ እለት ለሁሉም መዋቅሮች ስሪጭት እንደምካሄድ እና በተያዘለት መረሀ ግብር እንደምካሄድ ተልፀዋል።

የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ለቤንች ማጂ ልማት ማህበር አዳሪ ትምህርት ቤት የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች የአጠናንና የፈተና አሰራር ስልት ስልጠና እየሰጠ ነው።የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ከቤንች ማጂ ልማት...
04/06/2026

የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ለቤንች ማጂ ልማት ማህበር አዳሪ ትምህርት ቤት የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች የአጠናንና የፈተና አሰራር ስልት ስልጠና እየሰጠ ነው።

የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ከቤንች ማጂ ልማት ማህበር ጋር በመተባበር በአዳሪ ትምህርት ቤቱ ለሚገኙ የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች ውጤታማ የጊዜ አጠቃቀም፣ ሳይንሳዊ የአጠናን ዘዴና የብሄራዊ ምርጫ ጥያቄዎችን የመመለስ ስልት ላይ ያተኮረ ሰፊ የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት ጀመረ።

ዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች በፈተና ወቅት የሚገጥሟቸውን ስነ-ልቦናዊና ቴክኒካዊ ተግዳሮቶች ቀድመው እንዲረዱና በሙሉ በራስ መተማመን ለፈተና እንዲቀመጡ ለማስቻል ካለው ቁርጠኝነት በመነሳት ይህንን ስልጠና በከፍተኛ የዩኒቨርሲቲው መምህራን አማካኝነት እያሰለጠነ ይገኛል።

​የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ሽግግርና ማህበረሰብ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር በሱፍቃድ መኮንን እንደገለጹት ተማሪዎች በፈተና ወቅት ሊኖራቸው የሚገባውን ዝግጅት ምን መምሰል እንዳለበት ታሳቢ ያደረገ ግንዛቤ እየተፈጠረ ነው።

ይህ በአዳሪ ትምህርት ቤቱ የተጀመረው ስልጠና የትብብሩ አንዱ አካል ሲሆን ተማሪዎቹ ካላቸው የተለየ አቅም አንጻር በብሄራዊ ፈተናው ከፍተኛ ውጤት እንዲያስመዘግቡ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑንም አብራርተዋል።

​ከፍተኛ በጀትን ጨምሮ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ የተመደበለትን ይህንን ሀገራዊ ፕሮጀክት በተመለከተ ዳይሬክተሩ ሲያብራሩ ዩኒቨርሲቲው ማህበረሰባዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ሰፊ ዝግጅት ማድረጉን ጠቅሰዋል።

በዚህም መሰረት በቤንች ሸኮ፣ በምዕራብ ኦሞ እና በሸካ ዞኖች ስር በሚገኙ 21 የመንግስት እና የአዳሪ ትምህርት ቤቶች ላይ ከ98 በላይ አንጋፋ የዩኒቨርሲቲ መምህራንን በማሳተፍ ተመሳሳይ አጋዥ ስልጠናዎች በስፋት እየተሰጡ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

​በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ኢንተራንስ ፈተና ከሶስቱም ዞኖች እጅግ የተሻለና አመርቂ ውጤት እንደሚጠበቅ የጠቆሙት ዳይሬክተሩ በተለይም በቤንች ሸኮ ዞን የሚገኘው የልማት ማህበሩ የተማሪዎችን የትምህርት ጥራትና ውጤታማነት ለማሻሻል ከፍተኛ ጥረትና ተከታታይነት ያለው ክትትል እያደረገ እንደሚገኝ አክለው ገልጸዋል።

​ለተማሪዎቹ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ ከዩኒቨርሲቲው ጋር በተደረገው ቀጣይነት ያለው ውይይትና ቅንጅት መሰረት ከዚህ ቀደምም የተለያዩ ስልጠናዎች ሲሰጡ መቆየታቸውን ያስታወሱት ረዳት ፕሮፌሰር በሱፍቃድ ተማሪዎች የተሰጣቸውን የዕውቀትና የስልት ሽግግር ወደ ውጤት እንዲቀይሩት በማሳሰብ ለሁሉም ተፈታኞች የመልካም እድል ምኞታቸውን አስተላልፈዋል።

ዘገባው ከቤንች ሸኮ መንግስት ኮሚንኬሽን የተወሰደ ነዉ

Address

Mizan Teferi

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bench Maji Development Association posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Bench Maji Development Association:

Shortcuts

Share