Jimma Chess Community

Jimma Chess Community Our goals is to promote chess in Jimma, Ethiopia and one day to have a very strong chess center in o

08/08/2022

ትኩረት የተነፈገው የኢትዮጵያ ቼዝ ብሄራዊ ቡድን በህንድ አስተናጋጅነት 187 ሀገሮች እየተሳተፉበት በሚገኘው የዓለም ቼዝ ሻምፒዮና (ኦሎምፒያድ) የኢትዮጵያ ብሄራዊ የቼዝ ቡድን ከመንግስት ምን አይነት ድጋፍ ሳያገኝ ብዙ ውጣውረድ አልፎ እየተሳተፈ ይገኛል። ቡድኑ በፌደሬሽኑ ፕሬዚዳንት እና በዓለም አቀፉ ቼዝ ፌደሬሽን ሙሉ ድጋፍ ነው ህንድ የተገኘው። መንግስት ህብረተሰቡን የስፖርት ተጠቃሚ ለማድረግ እየሰራ ያለውን ብናደንቅም ለቼዝ ስፖርት ግን የተሰጠው ትኩረት እጅግ አነስተኛ ነው። ኢትዮጵያ በአለም አቀፍ የቼዝ የውድድር መድረክ በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የወርቅ ሜዳሊያ ( 1ወረቅ፣2ብር፣1 ነሀስ) ብታስመዘግብም ለተገኘው ውጤት እስካሁን እውቅና አለመሰጠቱ ለስፖርቱ የተሰጠው ዝቅተኛ ትኩረት ማሳያ ነው። ሌላው አሳዛኝ ሁኔታ በህንድ ቼናይ ከተማ እየተሳተፈ የሚገኘው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን እንኳን አሸኛኘት ሊደረግለት ቀርቶ የሀገርን ውክልና ሊገልፅ የሚችል ትጥቅ የሚሰጠው አጥቶ (ለኦሎመፒከ ኮሚቴ ፌደሬሽኑ ደብዳቤ ቢፅፍም ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ ባለመሆናቸው) ቢሳተፍም የኢትዮጵያን ባንዲራ ከሌሎች ሀገሮች እኩል እንዲውለበለብ እያደረገ ይገኛል። ስለዚህ ለሌሎች የሚደረገው ድጋፍ የቼዝ ስፖርት ማህበረሰብን ታሳቢ በማድረግ ብሔራዊ ቡድኑ በአፍሪካ ዞን ውድድር ላመጣው ውጤትም ሆነ በህንድ እየተደረገ ላለው የዓለም ሻምፒዮና እውቅና ቢሰጠው ቼዝ ማህበረሰብን ለማንቃትና አሳቢ ትውልድ ለማፍራት ጠቀሜታው የጎላ በመሆኑ ስፖርቱ እንዲስፋፋ አጋዥ ይሆናል።

Aydu Gezachew the great💪💪💪💪
21/05/2022

Aydu Gezachew the great💪💪💪💪

12/05/2022

ኢትዮጵያ በዓለም ዓቀፍ ቼዝ ውድድር መድረክ፤🇪🇹‼️

ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ ቼዝ ፌደሬሽን አባል የሆነቸው በ1984 ዓ/ም እንደሆነ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ኢትዮጵያ በተለያዩ የዓለም አቀፍ ቼዝ ውድድሮች ላይ በወንድም በሴትም ተሳታፊ ሆናለች፡፡ በተሳተፈችባቸው ውድድሮች ላይ ምን ውጤት ተመዘገበ የሚለውን መረጃ ለቼዝ ማህበረሰቡ ማስተላለፍ እውቅና መስጠትም ስለሆነ ይህ አጭር መረጃ ለማዘጋጀት ተሞክሯል፡፡ አንዳንድ የቦታ፤ የቀንና የውጤት መፋለስ ቢኖር ማስተካከል ይቻላል፡፡
ኢትዮጵያ በኦሎምፒያድ መሳተፍ የጀመረችው በ1993 ዓ/ም በ34ኛው ቱርክ ኢስታንቡል ጀምሮ ሲሆን እስካሁን ያልተሳተፈችው የስፔኑን ብቻ ነው፡፡ ቱርክ ኢስታንቡል ከተማ በተካሄደው ውድድር ዳዊት ወንድሙ በታሪክ የመጀመሪያውን የብር ሜዳሊያ ሲያገኝ በ35ኛው ስሎቪኒያ ብሌድ ከተማ ላይ በተካሄደው ውድድር ወሰንየለው ሀይሉ የነሀስ ሜዳሊያ ለሀገሩ አስገኝቷል፡፡ እንዲሁም በቡድን 1ኛ በመውጣት ዋንጫ ተሸላሚ ሆነዋል፡፡ ጆርጂያ ከተካሄደው እስከ 43ኛው ኦሎምፒያድ ድረስ ሜዳሊያ አልተገኘም፡፡ እንዲሁም በታይትል ደረጃ አዘርባጃን ባኩ ከተማ በተካሄደው ኦሎምፒያድ ለይኩን መስፍን የፊዴ ማስተር ታይትል አግኝቷል፡፡ ጆርጂያ ላይ በተካሄደው ኦሎምፒያድ አይዳኙህም ግዛቸው የፊዴ ማስተር (ያልፀደቀ)፤ በሴቶች መቅደስ ደምሴ ካንዲዴት ማስተር ደረጃ አግኝተዋል፡፡

በመላው አፍሪካ ጨታዎች ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በቼዝ የተሳተፈችው በ1996 ዓ/ም ናይጄሪያ ላይ በተካሄደው ሲሆን ቡድኑ ዲፕሎማ አግኝቷል፡፡ አልጀሪያ ላይ በተካሄደው ውድድር ብርሀኔ ገ/እግዚአብሄር የነሀስ ሜዳሊያ አስገኝቷል፡፡ በሞዛምቢክና ሞሮኮም ላይ ኢትዮጵያ በቼዝ ተሳታፊ ነበረች፡፡

በአፍሪካ ዞናል ውድድር ኢትዮጵያ መሳተፍ የጀመረችው ግብፅ ላይ በ1990 ዓ/ም በተካሄደው ሲሆን በወቅቱ ከተሳተፉት ሁለት ስፖርተኞች መካከል ይማም አበራ የፊዴ ማስተር ታይትል ማግኘት ችሏል፡፡ ጅቡቲ (2018) ላይ በተካሄደው የዞን 4.2 ውድድር ለይኩን መስፍን እና ፌቨን ገ/መስቀል ለኢትዮጵያ በዞናል ውድድር የመጀመሪያውን የነሀስ ሜዳሊያ አስገኝተዋል፡፡ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ዓለም አቀፍ የቼዝ ውድድር ያስተናገደችው በ2009 ዓ/ም ጂማ ከተማ ላይ የተካሄደውን የዞን 4.2 ውድድር ነው፡፡ በዚህ ውድድር አይዳኙህም ግዛቸው 5ኛ ደረጃና የፊዴ ማስተር ታይትል (ያልፀደቀ) አግኝቷል፡፡
የዞን 4.2 ወደ ዞን 4.4 ሲለወጥ የመጀመሪያውን ውድድር በዚህ ዓመት 2014 ዓ/ም ያስተናገደችው ኢትዮጵያ በአዲስ አበባ ከተማ ሲሆን በዚህ ውድድር ኢትዮጵያ በውጤት የደመቀችበት ነው፡፡ ከበፊቱ በተለየ ሁኔታ ዝግጅት የተደረገበት፤ ብዙ ተወዳዳሪዎች የተሳተፉበት፤ እንዲሁም የፊዴ፤ የአፍሪካና የዞን 4.4 ፕሬዚዳንቶች የተገኙበት ነበር፡፡ በውድድሩ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በዓለም ዓቀፍ ቼዝ ውድድር መድረክ ወርቅ ያገኘችበት ነው፡፡ በወንዶች ደሳለኝ ፍቃዱ ወርቅ፤ አይዳኙህም ግዛቸው ብር ሲያስገኙ በሴቶች ለመጀመሪያ ጊዜ የብር ሜዳሊያ በልደት አባተ፤ አስቴር መላከ ነሀስ ሜዳሊያ ለኢትዮጵያ አስመዝግበዋል፡፡ ይህም ውጤት በዓለም አቀፍ ውድድር መድረክ ኢትዮጵያ የወርቅ ሜዳሊያ በሩጫ ብቻ ሳይሆን በቼዝም ማስመዝገብ እንደምትችል አሳይቷል፡፡ በታይትል ደረጃ ኢትዮጵያ የመጀመሪያውን ኢንተርናሽናል ማስተር IM ታይትል ያገኘችበት ውድድር ነው፡፡ ደሳለኝ ፍቃዱና አይዳኙህም ግዛቸው ኢንተርናሽናል ማስተር IM እንዲሁም ሀብታሙ አሸናፊ የፊዴ ማስተር ሲያገኙ በሴቶች ልደት አባተና አስቴር መላከ የፊዴ ማስተር (በተጨማሪም የኢንተርናሽናል ማስተር ኖርም) አግኝተዋል ፡፡ ካንዲዴት ማስተር ታይትል ያገኙ አዲስ ዓለም፤ሀብታሙ ባዩ፤ አክመል፤ ጴጥሮስ፤ ሰላማዊት፤ ሀና፤ የኔነሽ፤ እስራኤል፤ መቅደስ አግኝተዋል፡፡ በቀጣዩ የ2022 የህንድ ኦሎምፒያድ ምን ውጤት ይመዘገብ ይሆን??
ምንጭ፤ ከኢንተርኔትና ከተጫዋቾች፡፡
ፊዴ ኢንስትራክተር ተገኝ መሀድም
Photo;
Slovinia,2002 Men's Team: kneeling (from left to right) are Dawit Wondimu (Bd. 1), Fikreselassie Alemu (Bd. 2), Yimam Abera (Bd. 3); standing (from left to right) Abenet Bekele (Bd. 4), Mekitew Molla (Bd. 5), Wossenyelew Hailu (Bd. 6) and the Team Captain, Tsega Kumlachew. Photo by Jerry Bibuld.

11/05/2022

Congratulations to CM Desalegn Fekadu Jimma and WFM Sasha Mongeli for winning the 2022 Zone 4.4 Championships. 👏👏
65 players from 6 African federations participated in the event that took place in Addis Ababa, Ethiopia, May 2-9.

More info: https://fide.com/news/1747

📷: Kenya Chess Masala

Address

Jimma

Telephone

251911750818

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Jimma Chess Community posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Jimma Chess Community:

Share