Hadiyyi Lichchi Xaaxxitte - ሀድያ ልማት ማህበር - Hadiya Development Association

  • Home
  • Ethiopia
  • Hossana
  • Hadiyyi Lichchi Xaaxxitte - ሀድያ ልማት ማህበር - Hadiya Development Association

Hadiyyi Lichchi Xaaxxitte - ሀድያ ልማት ማህበር - Hadiya Development Association Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Hadiyyi Lichchi Xaaxxitte - ሀድያ ልማት ማህበር - Hadiya Development Association, Nonprofit Organization, Hossana.
(1)

ከመሬት ገጽ በታች ግንባታ  #በመጠናቀቅ ላይ!ከወንድ ተማሪዎች ማደርያ ሕንጻ ብሎክ ውጭ እየተሠራ ያለው የሊች ጎጎ የልህቀት አዳሪ ትምህርት ቤት የወንድ ተማሪዎች መጸዳጃና ሻወር ብሎክ ግንባ...
19/02/2026

ከመሬት ገጽ በታች ግንባታ #በመጠናቀቅ ላይ!

ከወንድ ተማሪዎች ማደርያ ሕንጻ ብሎክ ውጭ እየተሠራ ያለው የሊች ጎጎ የልህቀት አዳሪ ትምህርት ቤት የወንድ ተማሪዎች መጸዳጃና ሻወር ብሎክ ግንባታ ከመሬት ገጽ በታች የድንጋይ ግንባታ ሥራ (Substructure Stone Masonry Work) በመጠናቀቅ ላይ ነው።

የዚሁ ብሎክ የግንባታ ወጪ፣ የአሠሪነትና የአማካሪነት ሚና ሙሉ በሙሉ በተማሪ ወላጆች በራሳቸው እንዲሸፈን ታቅዶ መጀመሩ ይታወሳል።

— ማክሰኞ፤ የካቲት 10 ቀን 2018 ዓ.ም (ከሰዓት በፊት)

🤜 💪 🤛
«ልማት የጋራና የተቀናጀ ጥረት ውጤት ነው»

  በመቅረብ ላይ!በተማሪ ወላጆች ሙሉ ተሳትፎ ከተማሪዎች ማደርያ ሕንጻ ብሎክ ውጭ እየተሠራ ያለ የሊች ጎጎ የልህቀት አዳሪ ትምህርት ቤት የወንድ ተማሪዎች መጸዳጃና ሻወር ብሎክ ግንባታ የአፈ...
09/02/2026

በመቅረብ ላይ!

በተማሪ ወላጆች ሙሉ ተሳትፎ ከተማሪዎች ማደርያ ሕንጻ ብሎክ ውጭ እየተሠራ ያለ የሊች ጎጎ የልህቀት አዳሪ ትምህርት ቤት የወንድ ተማሪዎች መጸዳጃና ሻወር ብሎክ ግንባታ የአፈር ቁፋሮ ሥራ የተጠናቀቀ ሲሆን ወደ ግንባታው ለመሸጋገር የግንባታው ቁሳቁሶች በመቅረብ ላይ ናቸው።
🤜 💪 🤛
«ልማት የጋራና የተቀናጀ ጥረት ውጤት ነው»
— እሁድ፤ የካቲት 01 ቀን 2018 ዓ.ም (ከሰዓት በኋላ)

በተማሪ ወላጆች ሙሉ ተሳትፎ ከተማሪዎች ማደርያ ሕንጻ ብሎክ ውጭ እየተሠራ ያለ የሊች ጎጎ የልህቀት አዳሪ ትምህርት ቤት የወንድ ተማሪዎች መጸዳጃና ሻወር ብሎክ ግንባታ የአፈር ቁፋሮ ሥራ ተጠ...
03/02/2026

በተማሪ ወላጆች ሙሉ ተሳትፎ ከተማሪዎች ማደርያ ሕንጻ ብሎክ ውጭ እየተሠራ ያለ የሊች ጎጎ የልህቀት አዳሪ ትምህርት ቤት የወንድ ተማሪዎች መጸዳጃና ሻወር ብሎክ ግንባታ የአፈር ቁፋሮ ሥራ ተጠናቋል።
🤜 💪 🤛
«ልማት የጋራና የተቀናጀ ጥረት ውጤት ነው»
— ጥር 26 ቀን 2018 ዓ.ም (ከሰዓት በኋላ)

በተማሪ ወላጆች ሙሉ ተሳትፎ ከሕንጻ ውጭ እየተሠራ ያለ የሊች ጎጎ የልህቀት አዳሪ ትምህርት ቤት መጸዳጃና ሻወር ብሎክ ግንባታ በአበረታች ቅልጥፍና እየነጎደ ይገኛል። 🤜 💪 🤛«ልማት የጋራና ...
02/02/2026

በተማሪ ወላጆች ሙሉ ተሳትፎ ከሕንጻ ውጭ እየተሠራ ያለ የሊች ጎጎ የልህቀት አዳሪ ትምህርት ቤት መጸዳጃና ሻወር ብሎክ ግንባታ በአበረታች ቅልጥፍና እየነጎደ ይገኛል።
🤜 💪 🤛
«ልማት የጋራና የተቀናጀ ጥረት ውጤት ነው»
— ጥር 25 ቀን 2018 ዓ.ም (ከቀትር በፊት)

 #የወተመህ እና የሌሎች ባለድርሻ አካላት ምክክር ተካሄደጥር 13 ቀን 2018 ዓ.ም — ሆሳዕናየሊች ጎጎ የልህቀት አዳሪ ትምህርት ቤት የተማሪ ወላጆች፣ የተማሪዎች እና የመምህራን ህብረት (...
21/01/2026

#የወተመህ እና የሌሎች ባለድርሻ አካላት ምክክር ተካሄደ

ጥር 13 ቀን 2018 ዓ.ም — ሆሳዕና

የሊች ጎጎ የልህቀት አዳሪ ትምህርት ቤት የተማሪ ወላጆች፣ የተማሪዎች እና የመምህራን ህብረት (ወተመህ) አባላት እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበት የምክክር መድረክ በሀልማ ዋና ጽ/ቤት ተካሂዷል።

በምክክር መድረኩም በትምህርት ቤቱ ከምሥረታው ጀምሮ እስካሁንም በመሠረታዊነት ባልተፈቱ የመማር ማስተማር ማነቆዎች ሁሉም ባለድርሻ አካላት የሚጠበቅባቸውን የተናጠልና የጋራ ሚና በሚጫወቱበት ሁኔታ ጥልቅና ሰፊ ውይይት ተካሂዷል።

በመድረኩም በተለይም ባለፈው ሳምንት በተካሄደው የወላጆች ጠቅላላ ጉባኤ በወላጆች ሙሉና ሁሉአቀፍ ተሳትፎ እንዲገነባ የተወሰነው መፀዳጃ ቤት ግንባታ የትግበራ ምዕራፍ ላይ እንዲሁም ከትምህርት ቤቱ መምህራን ስምሪት እና ከጥቅመ ጥቅሞቻቸው ጋር የተያያዙ ችግሮች ተነስተው በሰፊው የተመከረባቸው ሲሆን በትምህርት ቤቱ ቋሚ የመምህራን ስምሪት በሚሰጥበት እና የጥቅመ ጥቅም ጥያቄ ተገቢ ምላሾች በሚሰጥበት ሁኔታ በሀልማና በዞኑ አስተዳደር የላዕላይ መዋቅር የአጥኚ ቲም ተቋቁሞ እየተሠራበት መሆኑን በሰፊው ተብራርቷል።

እነዚህና ሌሎችም ማነቆዎች የሚቀረፉበት ጥናት ተካሂዶ በሚመለከተው አካል ተገቢው ውሳኔ እስከሚሰጥበት ድረስ በሕዝባዊ ውግንና መንፈስ ሁሉም ኃላፊነቱን እየተወጣ በትዕግስት መጠባበቅ እንዳለበትም በምክክሩ ተመልክቷል።

የሀልማ ዋና ዳይሬክተር በሆኑት በአቶ አድነው ሎንሰቆ በተመራው በዚህ ስብሰባ አቶ ዴታሞ ጡምደዶ (የዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ)፣ አቶ ሀዳሞ አቡቴ (የሆሳዕና ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት ተወካይ ኃላፊ)፣ የወተመህ አባላትና የሀልማ ማኔጅመንት አባላት ተገኝተዋል።

የሊች ጎጎ ትምህርት ቤት   ማጎልበቻ የምክክር መድረክ ተካሄደጥር 06 ቀን 2018 ዓ.ም — ረቡዕበሀድያ ልማት ማህበር (ሀልማ) እየተዳደረ በሚገኘው ሊች ጎጎ የልህቀት አዳሪ ትምህርት ቤት ...
15/01/2026

የሊች ጎጎ ትምህርት ቤት ማጎልበቻ የምክክር መድረክ ተካሄደ

ጥር 06 ቀን 2018 ዓ.ም — ረቡዕ

በሀድያ ልማት ማህበር (ሀልማ) እየተዳደረ በሚገኘው ሊች ጎጎ የልህቀት አዳሪ ትምህርት ቤት የሥራ እንቅስቃሴ የተማሪ ወላጆች ሚና ማጎልበቻ የምክክር መድረክ በትምህርት ቤቱ በዛሬው ዕለት ተካሂዷል።

የአዳሪ ትምህርት ቤቱ ብሎኮችና ተያያዥ የመሠረተ ልማት አቅርቦት ጥረቶች በሂደት ላይ እያሉ ጎን ለጎን የመማር ማስተማር ሥራው #በ2012 ዓ.ም በሆሳዕና መምህራን ትምህርት እና በሆሳዕና ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች ግቢ መጀመሩን፤ በግንባታዎቹ ሂደትና በተያያዥ ሥራዎች ላይ እምብዛምም ለውጥ ሳይመዘገብበት በኮሌጆቹ የአንድ ዓመት ያክል ብቻ ቆይታ በማድረግ የመማር ማስተማር ሥራው ወደ ትምህርት ቤቱ ተዛውሮ እንዲቀጥል መደረጉን የምክክር መድረኩን የመሩት የሀልማ ዋና ዳይሬክተር አቶ አድነው ሎንሰቆ አስታውሰዋል።

በቅደም ተከተል መፈጸም የነበረባቸውን ተግባራት በዞኑ የትምህርት ሥራ በነበረው ቁጭት ጎን ለጎን እንዲካሄዱ መደረጉ ( ) አድናቆት የሚቸረው ውሳኔ ቢሆንም በዓመቱም ሆነ ቀጥሎ ባሉ ዓመታት በተለይም የመማር ማስተማሩ ሥራ ከማህበሩ የውስጥ ገቢ በሚመደብ የሥራ ማስኬጃ በጀት እና ከአንዳንድ ግለሰቦችና ድርጅቶች በተገኙ የቁሳዊ ግብዓቶች ልግስና ብቻ መወሰኑን፤ ከብሎኮች ግንባታ 3 (ሶስት) Lots ሁለቱ እስከ 2015 ዓ.ም ተጠናቀው መመረቃቸውን፤ ግንባታው ያልተጠናቀቀለት 3ኛው Lot እስካሁን ቆሞ መቅረቱን፤ በየዓመቱ «ያላለቁ የት/ቤቱ ግንባታዎች ማስጨረሻ እና የሥራ ማስኬጃ በጀት ድጋፍ» በሚል ከመንግስት በኩል ቢታቀድም በተጨባጭ ለትምህርት ቤቱ የተፈጸመ የበጀት ድጋፍ አለመኖሩን ዋና ዳይሬክተሩ ጨምረው ገልጸዋል።

ከትምህርት ቤቱ ምሥረታ አንስቶ እስካሁን በበጀት እጥረት ምክንያት ያልተፈቱ፤ የአጭር ጊዜ መፍትሔ እየተሰጣቸው የቆዩ ነገር ግን ዘላቂ የመፍትሔ እርምጃ ያልተወሰደባቸው ማነቆዎች ዝርዝር በዋና ዳይሬክተሩ አማካይነት ለተማሪ ወላጆቹ ከቀረበ በኋላ ወላጆቹም በማነቆዎቹ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ አሳስበዋል።

በትምህርት ቤቱ የማደሪያ ሕንጻዎች ላይ የተገነቡ ዘመናዊ መጸዳጃ ቤቶች ቢኖሩም በውሃ አቅርቦት ችግር ምክንያት ለመገልገል ባለመቻሉ ከሕንጻ ውጭ ያለውና ሁሉም ተማሪዎች በአንድ ላይ የሚጸዳዱበት መጸዳጃ ብሎክ ለሴቶች ብቻ ሆኖ ለወንድ ተማሪዎች አንድ ባለ10 ክፍሎች መጸዳጃ ብሎክ በራሳቸው የገንዘብ፣ የምህንድስና ሙያ፣ የክትትልና ቁጥጥር ... ወዘተ ተሳትፎ በተወሰኑ ወራት አሠርተው በማጠናቀቅ ለትምህርት ቤቱ ለማስረከብ ወላጆቹ ያለ ልዩነት ከመስማማታቸውም በላይ በቀጣይም ከሌሎች አካላት ጋር በመሆን በሌሎች ማነቆዎች ላይ ለመረባረብ ቁርጠኝነታቸውን አክለው ገልጸዋል።

በዕለቱም ይህንን የተጨማሪ መጸዳጃ ብሎክ ግንባታ ፕሮጀክት የሚያስተባብሩ፤ በቀጣይም #የወተመህ (የወላጆች፣ የተማሪዎችና የመምህራን ተወካዮች ህብረት) አባላት በመሆን በህብረቱ መደበኛ ሥራዎችና በትምህርት ቤቱ ሌሎች ፕሮጀክቶች ህብረቱን በመወከል በአስተባባሪነት የሚያገለግሉ የኮሚቴ አባላት ምርጫ ተካሂዷል።

በሕብረቱ የሚገነባው የዚህ መጸዳጃ ቤት ግንባታም በያዝነው ጥር ወር ሊጀምር እንደሚችል የወተመህ ሰብሳቢ በሆኑት በአቶ አየለ ላምቤቦ ተጠቁሟል።

14/01/2026

28/11/2025

!!

ዋው! እንኳን ደስ አለን! #ሆሳዕና በሀገር አቀፍ ደረጃ ከምድቧ  #2ኛ ሆነች።ይገባታል!
21/11/2025

ዋው! እንኳን ደስ አለን!
#ሆሳዕና በሀገር አቀፍ ደረጃ ከምድቧ #2ኛ ሆነች።
ይገባታል!

የሻሾጎ ወረዳ የሀልማን ሥራ ራሱን አስችሎ የንቅናቄ መድረክ በማዘጋጀት የመተግበር አቅጣጫ መከተሉ እጅግ ከፍ ያለ አድናቆት የሚቸረው ነው፤ ምክንያቱም ይህ የሀልማን ሥራ በሌሎች አካቶ (mai...
17/11/2025

የሻሾጎ ወረዳ የሀልማን ሥራ ራሱን አስችሎ የንቅናቄ መድረክ በማዘጋጀት የመተግበር አቅጣጫ መከተሉ እጅግ ከፍ ያለ አድናቆት የሚቸረው ነው፤ ምክንያቱም ይህ የሀልማን ሥራ በሌሎች አካቶ (mainstream አድርጎ) ከመምራትም የተሻገረ ነው።

የሻሾጎ ወረዳ መንግስታዊ፣ የፓርቲ (ድርጅታዊ) እና ሕዝባዊ ተቋማት ሥራዎችን ተመጋጋቢና ተደጋጋፊ በሚሆን አግባብ አቀናጅቶ መምራትን በመያያዙ ውዝፍ ሥራዎችን በማካካስ እና የዘመኑን ደግሞ ባልተንጠባጠበ አግባብ በማስፈጸም በውጤቱ ከዞናችን ግንባር ቀደም ወረዳዎች አንዱ እንደሚሆን ተስፋ እናደርጋለን።

  የሀልማ ሥራዎች   በሻሾጎ ወረዳ ተካሄደ ሕዳር 08 ቀን 2018 ዓ.ም — ቦኖሻበሀድያ ልማት ማህበር (ሀልማ)   የ2017 ዓ.ም የዕቅድ አፈጻጸም እና የ2018 ዓ.ም ዕቅድ ላይ ያተኮረ ...
17/11/2025

የሀልማ ሥራዎች በሻሾጎ ወረዳ ተካሄደ

ሕዳር 08 ቀን 2018 ዓ.ም — ቦኖሻ

በሀድያ ልማት ማህበር (ሀልማ) የ2017 ዓ.ም የዕቅድ አፈጻጸም እና የ2018 ዓ.ም ዕቅድ ላይ ያተኮረ የንቅናቄ መድረክ ዛሬ ሕዳር 08 ቀን 2018 ዓ.ም በቦኖሻ ከተማ ተካሂዷል።

የንቅናቄ ሰነዱ የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ አስተባባሪ በሆኑት በአቶ አጋጎ ዳዶዬ አማካይነት ቀርቦ ሰፊና ጥልቅ ውይይት ተደርጎበታል።

የወረዳው ዋና አስተዳዳሪና የወረዳው ሀልማ ቅርንጫፍ አስተባባሪ ኮሚቴ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ግርማ ሎቤ እና የወረዳው ዋና የመንግስት ተጠሪና የወረዳው ሀልማ ቅርንጫፍ አስተባባሪ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ታደሰ ሙጎሮ ።

የሀልማ ሥራ የሕልውና ጉዳይ በመሆኑ በ2018 ዓ.ም የዓመቱንና ወደ ዓመቱ የተሻገሩ ውዝፍ ዓመታዊ የአባልነት መዋጮ አሰባሰብና ተያያዥ የገቢ መሰብሰቢያ ደረሰኝ አመላለስ ሥራዎችን በወቅቱና ሙሉ በሙሉ ለማሳካት በከፍተኛ የሕዝብ ውግንና መንፈስ ርብርብ ማድረግ እንደሚገባ የመድረኩ መሪዎች አጽንኦት ሰጥተው አሳስበዋል።

በተሰጠው ማሳሰቢያ መሠረት በሀልማ ሥራዎች ውጤታማነት ወረዳውን ግንባር ቀደም ለማድረግ ከመቼውም ጊዜ በላቀ ቁርጠኝነት እንደሚንቀሳቀሱ ተሳታፊዎቹ ቁጭት የተሞላበት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

በ2017 ዓ.ም አንጻራዊ አፈጻጸም #ዶዕሻ ከተማ፣ #ኡሼጎላ እና #ጀማያ ቀበሌያት እንደ ቅደም ተከተላቸው 1ኛ፣ 2ኛ፣ 3ኛ ደረጃ ያገኙ ሲሆን ዕቅዳቸውን ሙሉ በሙሉ ያሳኩ ሁለት ቀበሌያት (ማለትም #ዶዕሻ እና #ኡሼጎላ) ለላቀ አፈጻጸማቸው የተዘጋጀላቸውን የምሥክር ወረቀት ከክቡር አቶ ግርማ ሎቤ እና ከአቶ ታደሰ ሙጎሮ እጅ ተቀብለዋል።

በንቅናቄ መድረኩ የሀልማ ዋና ጽ/ቤት ማኔጅሜንት ኮሚቴ አባላት (ዳኛ በቀለ ሌሌ እና ወ/ሮ ኤራዬ አንሴ)፣ የወረዳው ምክትል የመንግሥት ተጠሪና የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ የሆኑት አቶ ወንድሙ ማርቆስ፣ የወረዳው አስተዳደር አመራር ፑል አባላት እና የቀበሌ ሊቀናመብርትና ሥራ አስኪያጆች መሳተፋቸው ታውቋል።

የሻሾጎ ወረዳ የሀልማን ሥራ ራሱን አስችሎ የንቅናቄ መድረክ በማዘጋጀት የመተግበር አቅጣጫ መከተሉ እጅግ ከፍ ያለ አድናቆት የሚቸረው ነው፤ ምክንያቱም ይህ የሀልማን ሥራ በሌሎች አካቶ (mai...
17/11/2025

የሻሾጎ ወረዳ የሀልማን ሥራ ራሱን አስችሎ የንቅናቄ መድረክ በማዘጋጀት የመተግበር አቅጣጫ መከተሉ እጅግ ከፍ ያለ አድናቆት የሚቸረው ነው፤ ምክንያቱም ይህ የሀልማን ሥራ በሌሎች አካቶ (mainstream አድርጎ) ከመምራትም የተሻገረ ነው።

የሻሾጎ ወረዳ መንግስታዊ፣ የፓርቲ (ድርጅታዊ) እና ሕዝባዊ ተቋማት ሥራዎችን ተመጋጋቢና ተደጋጋፊ በሚሆን አግባብ አቀናጅቶ መምራትን በመያያዙ ውዝፍ ሥራዎችን በማካካስ እና የዘመኑን ደግሞ ባልተንጠባጠበ አግባብ በማስፈጸም በውጤቱ ከዞናችን ግንባር ቀደም ወረዳዎች አንዱ እንደሚሆን ተስፋ እናደርጋለን።

Address

Hossana

Telephone

+251465551233

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hadiyyi Lichchi Xaaxxitte - ሀድያ ልማት ማህበር - Hadiya Development Association posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Hadiyyi Lichchi Xaaxxitte - ሀድያ ልማት ማህበር - Hadiya Development Association:

Share