02/05/2026
ሀገር አቀፍ የግል የበላይነት ቼስ ሻምፒዮና ተጠናቀቀ።
ሚያዚያ 24፣ 2018ዓ.ም አዲስ አበባ
በኢትዮጵያ ቼስ ፌዴሬሽን አዘጋጅነት ሲካሄድ የቆየው የ2018 ለሁሉም ክፍት የሆነው የቼስ የግል የበላይነት ሻምፒዮና ተጠናል።
በሻምፒዮናው ሀና ሙሉጌታ፣ ነፃነት ሉቃስ፣ አስቴር መለሰ በሴቶች ከ1-3 ያለውን ደረጃ በመያዝ የሜዳሊያ ተሸላሚ ሆነዋል።
ለብሔራዊ ቡድንም የሜዳሊያ አሸናፊዎቹን ጨምሮ ሰላማዊት ስለሽንና ሲና ታደሰ ተመርጠዋል።
በወንዶች ለይኩን መስፍን፣ ፍላወር ሀብቱ እና ሮቤል ብርሃነ የወርቅ፣ የብርና የነሀስ ሜዳሊያ ተሸላሚ ናቸው።
በተመሳሳይ ለብሔራዊ ቡድን ሚልኪ አብድሳ እና ጴጥሮስ ኦላና ጨምሮ የሜዳሊያ አሸናፊዎች ተመርጠዋል።
የኢትዮጵያ ቼስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አቶ ተሾመ በቀለ ሻምፒዮናው ተተኪ ስፖርተኞችን ማግኘት የተቻለበት እንደሆነ በማጠቃለያ መርሃ ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ገለፀዋል።
በሻምፒዮናው አሸናፊ የሆኑ ስፖርተኞች በቀጣይ ሀገራቸውን ወክለው በአለም አቀፍ መድረክ ይሳተፋሉ ብለዋል።
ፌዴሬሽኑ በቀጣይ ስልጠናዎችንም አጠናክሮ እንደሚቀጥል ፕሬዚዳንቱ አክለዋል።
ለሁሉም ክፍት በሆነው የግል የበላይነት ሻምፒዮና ከ142 በላይ ተወዳዳሪዎች ተሳትፈዋል።
You can view and join right away.