Mary Joy Hawassa Program Office

Mary Joy Hawassa Program Office It is a nongovernmental, non religious, non political and nonprofit making organization established under the Civil Societies and Charity Agency.

12/05/2026
የኛ ጊዜ ፕሮጀክት በተለያየ ጊዜ ለሜሪ ጆይ አረጋዊያን ማዕከል የዓይነት ድጋፍ እያደረጉ ሲሆን በዛሬውም ዕለት ለማዕከሉ አገልግሎት የሚውል  ፈሳሽ  የጽዳት መጠበቂያ ሳሙና ድጋፍ አድርገዋል።...
12/05/2026

የኛ ጊዜ ፕሮጀክት በተለያየ ጊዜ ለሜሪ ጆይ አረጋዊያን ማዕከል የዓይነት ድጋፍ እያደረጉ ሲሆን በዛሬውም ዕለት ለማዕከሉ አገልግሎት የሚውል ፈሳሽ የጽዳት መጠበቂያ ሳሙና ድጋፍ አድርገዋል።

የፕሮጀክቱን አስተባባሪዎችን ከልብ እናመሰግናለን እግዚአብሔር ይስጥልን!!

ሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ
ኢትዮጵያዊያን ለኢትዮጵያዊያን
#0462204705 ,09554646

11/05/2026

እንኳን ለእናቶች ቀን አደረሳችሁ!
ሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ
"ሁሌም ስሰጥ የምቀበለው አለ"

የሀዋሳ ከተማ ስራ አሰሪ እና ሰራተኛ መምሪያ ከሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ለከተማዋ ወጣቶች የስራ ፈጠራ እና የልቦና ውቅር (Mindset) ስልጠና ተሰጠየሀ/ከ/አስ/የመ/ኮሙ/መምሪያሀ...
10/05/2026

የሀዋሳ ከተማ ስራ አሰሪ እና ሰራተኛ መምሪያ ከሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ለከተማዋ ወጣቶች የስራ ፈጠራ እና የልቦና ውቅር (Mindset) ስልጠና ተሰጠ

የሀ/ከ/አስ/የመ/ኮሙ/መምሪያ
ሀዋሳ፤
ግንቦት 1/2018 ዓ.ም

ስልጠናው ወጣቶች በስራ ፈጠራ ዘርፍ የተሻለ አቅም እንዲገነቡ፣ የንግግር እና የተግባቦት እንዲያሳድጉ፣ በራሳቸው የመተማመን ስሜት እንዲያዳብሩ እና ለስራ ዓለም የሚያስፈልጉ አመለካከቶችን እንዲያጎለብቱ ታልሞ የተዘጋጀ ሲሆን፣ በተለይም የራስ አቅምን አውቆ እና አጎልብቶ የበቃ የስራ ፈጠራ፣ የንግድ ሀሳብ ማመንጨት፣ የቡድን ስራ ክህሎት እና አዎንታዊ የአስተሳሰብ መፍጠር ላይ ትኩረት ያደረገ ነው።

የሀዋሳ ከተማ ስራ አሰሪ እና ሰራተኛ መምሪያ ኃላፊ አቶ ሽታ ኤቢሶ እንደገለፁት፣ ወጣቶችን በክህሎት እና በአመለካከት ማብቃት የስራ እድል ፈጠራን ለማሳደግ ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው፣ እንደዚህ ያሉ ስልጠናዎች ወጣቶች ራሳቸውን በተሻለ ሁኔታ እንዲያዩ እና ከስራ ፈላጊነት ወደ ስራ ፈጣሪነት እንዲሸጋገሩ ከፍተኛ ሚና ይኖራቸዋል በማለት አስረድተዋል።

መምሪያው ከተለያዩ አጋር ተቋማት ጋር በመስራት ወጣቶችን በኢኮኖሚያዊ ተሳትፎ ለማበረታታት እና ስራ እንዲፈጥሩ የሚያግዙ ፕሮግራሞችን በቀጣይነት እንደሚያስፋፋም ሀላፊው ገልፀዋል።

በስልጠናው የተሳተፉ ወጣቶች በበኩላቸው ያገኙት ዕውቀትና ተሞክሮ በቀጣይ ህይወታቸው እና በስራ መስካቸው ጠቃሚ እንደሚሆን ገልፀው፣ እንደዚህ ያሉ ስልጠናዎች በተከታታይነት መሰጠታቸው ለወጣቶች የተሻለ ተስፋ እና አቅጣጫ የሚያመላክት መሆኑን ተናግረዋል።

ስልጠናው ከማስተር ካርድ ፋውንዴሽን በተገኘ ድጋፍ የሚተገበረው “የኛ ጊዜ” ፕሮጀክት አካል ሲሆን፣ በሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ እና በገርልስ ኢፌክት ትብብር የተዘጋጀ መሆኑ ታውቋል ሲል የዘገበው የሀዋሳ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ቤት ነው።

10/05/2026
የዳግም ትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ አቶ ጥሩዘር በላይ እና ባለቤታቸው ወ/ሮ የምስራች ታደሰ በሜሪ ጆይ አረጋዊያን ማዕከል በመገኘት ለአረጋዊያን የማዕድ ማጋራት አደረጉ።በዕለቱም የሜሪ...
20/04/2026

የዳግም ትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ አቶ ጥሩዘር በላይ እና ባለቤታቸው ወ/ሮ የምስራች ታደሰ በሜሪ ጆይ አረጋዊያን ማዕከል በመገኘት ለአረጋዊያን የማዕድ ማጋራት አደረጉ።በዕለቱም የሜሪ ጆይ የቦርድ አባል የሆኑት ወ/ሮ አዲስ ዘለቃ እና ባለቤታቸው አቶ መሰለ መኮንን በእንግድነት የተገኑ አረጋዊያኑን በጋራ አስተናግደዋል። ከአረጋዊያንም ምርቃትና በረከት አግኝተዋል።
እግዚአብሔር ይስጥልን ከልብ እናመሰግናለን
ሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ
ኢትዮጵያዊያን ኢትዮጵያዊያን
#0462204705, 0955464646

ጊዮን በጎአድራጎት ወጣቶች በሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ አረጋዊያን ማዕከል በመገኘት  በሜሪ ጆይ የሚደገፋትን የጎዳና ሕፃናትን እና አረጋዊያንን ማዕድ በማጋራት ከአባቶች ምርቃትና በረከት አግኝተዋል።...
17/04/2026

ጊዮን በጎአድራጎት ወጣቶች በሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ አረጋዊያን ማዕከል በመገኘት በሜሪ ጆይ የሚደገፋትን የጎዳና ሕፃናትን እና አረጋዊያንን ማዕድ በማጋራት ከአባቶች ምርቃትና በረከት አግኝተዋል።

እግዚአብሔር ይስጥልን ከልብ እናመሰግናለን
ሜረ ጆይ ኢትዮጵያ
ኢትዮጵያዊያን ለኢትዮጵያዊያን #0462204705 ,0955464646

የእውቁ ተመራማሪ,ምዕሁር እና  ትልቅ የአገር ባለውለታ  የተከበሩ የዶ/ር መታሰቢያ በቀለ የሙት ዓመታቸውን መታሰቢያ ተዝካር ምክንያት በማድረግ ቤተሰቦቻቸው እና ወዳጅ ዘመዶቻቸው እንዲሁም ሚ...
17/04/2026

የእውቁ ተመራማሪ,ምዕሁር እና ትልቅ የአገር ባለውለታ የተከበሩ የዶ/ር መታሰቢያ በቀለ የሙት ዓመታቸውን መታሰቢያ ተዝካር ምክንያት በማድረግ ቤተሰቦቻቸው እና ወዳጅ ዘመዶቻቸው እንዲሁም ሚዲያዎች በተገኙበት በሜሪ ጆይ አረጋዊያን ማዕከል በመገኘት የማዕድ ማጋራት ፕሮግራም አደረጉ።
የአባታችንን የዶክተርን ነብስ ይማርልን።
ለቤተሰቦቹም በሙሉ መጽናናትን ይስጥልን
እግዚአብሔር ይስጥልን ከልብ እናመሰግናለን!!
ሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ
ኢትዮጵያዊያን ለኢትዮጵያዊያን
#0462204705 ,0955464646

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
12/04/2026

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

Address

Diaspora
Hawassa

Telephone

0913121177

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Mary Joy Hawassa Program Office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share