Sidama Roads Authority/Sidaamu dooggate biilloonya

Sidama Roads Authority/Sidaamu dooggate biilloonya we construct gravel roads and bridges for Sidama people settling at rural areas.

በሲዳማ ክልል የመንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ቃል የችግኝ ተከላ ፕሮግራም በወንዶ ገነት ወረዳ ተካህዷል:: ==========================በተከላ...
12/08/2026

በሲዳማ ክልል የመንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ቃል የችግኝ ተከላ ፕሮግራም በወንዶ ገነት ወረዳ ተካህዷል::

==========================
በተከላ መረሃግብር ላይ ተገኝተው ንግግር ያድረጉት የቢሮ ኃላፊ ክቡር ጎሳዬ ጎዳና እንደተናገሩት በሀገር ደረጃ እንዲሁም በክልል ደረጃ የተጀመረው ንቅናቄ አካል እንደሆነ ገልፆዎ በቢሮ በኩል አጠቃላይ ሰራተኞችና አመራር ተሳትፎ በማድረግ አሻራቸውን እንዲያኖሩ ታሳብ የተደረገ እንደሆነ ተናግረዋል::

በሀገር ደረጃ የተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ለምግብነት እና ለኢኮኖሚ ጥቅም የሚውሉ የፍራፍሬ፣ ቡና እና ሌሎች የተፈጥሮ ሀብት ተክሎች ላይ በማድረጉ ቀጥተኛ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን ይበልጥ ማረጋገጥ እየተቻል እንደሆነ ገልፆዋል።

በደን መመናመን ምክንያት እየደረሰ ያለውን ጉዳትን ለመቀነስ ወሳኝ መሆኑን ጠቅሶ አመራሩና ሰራተኞች በጠቅላይ ሚኒስቴሩ ይፋ ከተደረገ አንስቶ ተሳትፎ በማድረግ የዜግነት ግድታቸውን እየተወጡ እንደሆነ ተናግሯል::

ችግኝ መትከል ለነገ ትውልድ ተስፋን መትከል በመሆን ከመትከል ባሻገር በየጊዜው እንክብካቤ በማድረግ የፅድቀት መጠኑን ለማሳደግ ይበልጥ መስራት እንደሚገባ ገልፆዋል::

ዛሬ የተተከሉ ችግኞችን መንከባከብ መኮትኮትና እንዲያድጉ ማድረግ የአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አከባቢን ለመፍጠር እጅግ ወሳኝ መሆኑ ገልፆዎ በተፈጥሮ በተዋበች የወንዶ ገነት ወረዳ በመገኘት አሻራ ማሳረፍ መቻሉ የታሪክ አካል መሆን የሚያስችል ነው ተብለዋል::

በመረሃግብሩ ላይ የተገኙት የወንዶ ገነት ወረዳ አስተዳደሪ አቶ ሃማሮ ሀይሶ እንደገለፁት በቢሮ በኩል የወንዶ ገነት ወረዳን መርጣችሁ የአረንጓዴ አሻራ ለማሳረፍ መምጣታችሁ ለነገ ትውልድ የሚሆን ተስፋን በወረዳችን ማሳረፋችሁ የወንዶ ገነት ወረዳን ይበልጥ በደን ሽፋን እንዲትሽፈን ከማድረግ ባሻገር በእለቱ የተተከለው የአቭካዶ ችግኝ በመሆኑ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እንደሚረዳ አብራርቷል::

በመረሃ ግብሩ ላይ የቢሮ ኃላፊ ክቡር ጎሳዬ ጎዳና ;የቢሮ ምክትል ኃላፊዎች ;የወረዳ አስተዳዳሪ አመራሮች እንዲሁም የቢሮ ሰራተኞች በሙሉ ተገኝተው ተሳታፊ ሆነዋል::

===========================
የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት
ሐምሌ, 06/2018 ዓ.ም
ወንዶ ገነት ሲዳማ
============================

ከቱላ - ወተራረሳ - ያዬ - ወራንቻ የአስፋልት መንገድ ሥራ በኢፌዴሪ የመንገዶች አስተዳደር (ERA) በኩል ለመገንባት ወደ ሥራ የተገባ መሆኑ ይታወቃል።​ይሁን እንጂ መንገዱ በተለያዩ ምክን...
11/08/2026

ከቱላ - ወተራረሳ - ያዬ - ወራንቻ የአስፋልት መንገድ ሥራ በኢፌዴሪ የመንገዶች አስተዳደር (ERA) በኩል ለመገንባት ወደ ሥራ የተገባ መሆኑ ይታወቃል።

​ይሁን እንጂ መንገዱ በተለያዩ ምክንያቶች በተያዘለት የጊዜ ገደብ ተጠናቆ ለኅብረተሰቡ አገልግሎት መስጠት ባለመቻሉ በአካባቢው ማኅበረሰብ ዘንድ የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ሆኖ ቆይቷል።

​የክልሉ መንግሥት የመንገዱ ግንባታ ፈጥኖ እንዲጠናቀቅ ለማድረግ ከፌደራል መንግሥት ጋር በመሆን በቅርበት ክትትል እያደረገ ይገኛል።

በERA በኩል መንገዱን ለማጠናቀቅ የተጀመረው የአስፋልት ሥራ እንዲቀጥልና ፈጥኖ እንዲጠናቀቅ የሚደረገው ክትትል እንደተጠበቀ ሆኖ የሕዝባችንን ችግር እና በመንገዱ ላይ እያጋጠመ የሚገኘውን እንግልት ከግምት ውስጥ በማስገባት በሲዳማ ክልል መንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ በኩል ጥገና እንዲደረግ መጠነ ሰፊ እንቅስቃሴ እየተደረገ ይገኛል።

​የክልሉ መንግሥት ከፍተኛ በጀት በመመደብ በተለያዩ አካባቢዎች ያሉ ማሽነሪዎችንና የሰው ኃይል በማንቀሳቀስ መንገዱ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲሰጥ ከፍተኛ ርብርብ እያደረገ የሚገኝ ሲሆን ከፍተኛ ብልሽት ባሉባቸው ቦታዎች በክልሉ የመንገዶች ባለሥልጣን በኩል የጥገና ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።

​በቀጣይም ሥራው ሙሉ በሙሉ እስኪጠናቀቅ ድረስ መንግሥት በትኩረት እንደሚሠራ እንገልጻለን።

የሲዳማ ክልል መንገዶች ባለስልጣን

Ga'a Itophiya ragidhanno wedellinke ga'a ragidhannore calla ikkitukki techono gobba loossannonna lossitanno ilama ikkans...
08/08/2026

Ga'a Itophiya ragidhanno wedellinke ga'a ragidhannore calla ikkitukki techono gobba loossannonna lossitanno ilama ikkansanni ga'a dona techo wodhate hawadi aganna yannansa babbaxxitinno dancha fajjo loossanni saysate feeffattanni afantanno. Wedellu ledante mittimmatenni gobbansanna dagansa owaatate rosaminonte gede rosichonna budensa assidhe gobbate baxille leellishshanni leeltanno. Tenne danchumma biso ikkitinnoti Sidaamu qoqqowi wedellino hawadi aganna yannansa danchumatenni saysate babbxxino loosinni beeqqo assitanni afantanno.

baalinkera gutu mine ikkitinno gobbanke jireenyaame assate afi'ni kaayyo baalantey owaata daganna gobbate lopho hale ikkasinni tiiu kassonni sae gobba baxanna daga owaatate balchooma bude assira ikkinohura bilchaatanna feeffata ilama wedellinke heedhanno qarqari baalaho dancha fajjo danchumate loossa beeqqaano ikkansa mamootinniino roo're kaajjishshe sufa hasiissannoxa tawisanni dancha fajjo loossa s***a gede assine la'nannikkitanna horono daanni no gumino hakko deerriha ikkasi qaagiissa baxeemmo.

''halammo, loonso, gutammo, gobbankenna daganke danchummatenni owaanto''.

የነገይቱ ኢትዮጵያ ተረካቢ ወጣቶቻችን ነገ የሚረከቡ ብቻ ሳይሆን ዛሬም የሚሰሯት ዓሻራቸውን በበጎነት የሚያኖሩባት በመሆኗ የክረምት ወራትን ሀገራቸውንና ሕዝባቸውን በተለያዩ ዘርፎች በበጎ ፈቃደኝነት ለማገልገል እንደ ከዚህ ቀደሙ ልማድና ባህል አድርገው በተለመደው ሀገር ወዳድነታቸው እየተሳተፉ ይገኛል። የዚሁ በጎ ትውልድ አካል የሆኑት የሲዳማ ክልል ወጣቶች ክረምቱን በበጎነት ስራ ለማሳለፍ ተደምረው (የመደመር ትውልድ) ሀገራቸውን ከፍ ለማድረግ እየተጉ ይገኛል።

የጋራ ቤታችን የሆነቺውንና ነገ እኛኑን የምትጠብቅ ሀገራችንን ለማበልጸግ በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ የበጎነት ጠጠር መጣል ሀገርንና ሕዝቡን ማገልገል ስለሆነ ከሕሊና እርካታ ባሻገር ሀገር ወዳድነትን እና ሕዝብን ማገልገልን ባህል የማድረግ እሴት ያለው ተግባር ስለሆነ ትጉዕና ታታሪ ወጣቶቻችን በጎነታቸውን በየአካባቢያቸው ይበልጥ አጠናክሮ መቀጠል ይገባል እያልኩኝ የክረምት ወራት የበጎ ፈቃድ ወጣቶች ተሳትፎና ውጤቱ እንዲሁ በቀላሉ የሚታይ አለመሆኑን ለማሳሰብ እወዳለሁ።

የሲዳማ ክልል የ2019 የበጀት ዓመት የመጀመሪያ ዙር የ100 ቀናት ልዩ ልዩ የልማት እና የመልካም አስተዳደር ስራዎች ዕቅድ ውይይት መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።የ100 ቀናት ዕቅድ ዋነኛ ዓላ...
06/08/2026

የሲዳማ ክልል የ2019 የበጀት ዓመት የመጀመሪያ ዙር የ100 ቀናት ልዩ ልዩ የልማት እና የመልካም አስተዳደር ስራዎች ዕቅድ ውይይት መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።

የ100 ቀናት ዕቅድ ዋነኛ ዓላማው በክልሉ በድህረ-ምርጫ በፍጥነት ፊትን ወደ ስራ በመመለስ ፈጣን ውጤቶችን ማስመዝገብ፣ ተከታታይና አዳዲስ ነገሮችን መተግበር እንዲሁም ህብረተሰቡ ለሚያነሳቸው ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት በላቀ ትጋትና ያለ እረፍት መፈጸም የሚያስችል ዕቅድ ተዘጋጅቶ በልዩ ትኩረት ወደ ተግባር ለመግባት የሚያስችል ነው።

የሲዳማ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አብርሃም ማርሻሎ በ100 ቀናት ዕቅድ ማስጀመሪያው ላይ ባስተላለፉት መልዕክት በእነዚህ 100 ቀናት ውስጥ ህዝባችንን በምርጫ ወቅት ለሰጠን ይሁንታ በሚመጥን መልኩ የተለዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መፍታት እና አገልግሎትን የማሻሻል ስራን በማጠናከር እንዲሁም ለ2019 በጀት ዓመት መሰረት በሚጥል መልኩ ተግባራትን ለመምራት የሚያስችል ዕቅድ መዘጋጀቱን አንስተዋል።
ኃላፊው አክለው እንዳነሱት የኑሮ ውድነትን ማረጋጋት፣ የንግድ ሥርዓቱን መግራት፣ የስራ እድል ፈጠራ እንዲሁም የወጣቶችና ሴቶች ተጠቃሚነት ላይ በትኩረት እንደሚሰራም አብራርተዋል።

የሲዳማ ክልል የ2019 የበጀት ዓመት የመጀመሪያ ዙር የ100 ቀናት ልዩ ልዩ የልማት እና የመልካም አስተደር ስራዎች ዕቅድን የክልሉ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ዕቅዱን እያቀረቡ ሲሆን በቀረበው ዕቅድ ላይ ውይይት በማድረግ እስከታችኛው መዋቅር ድረስ ለመተግበር ሰፊ ውይይት እና ምክክር ተደርጎበት ወደ ተግባር ይገባል።

14/07/2026

ማስታወቂያ

በክልላችን አድስ ባጃጅ እና ኪዩቲ የገዛችሁ ባለንብረቶች በሙሉ ነገ በ8/11/2018 ዓ.ም
እና በ9/11/2018 ዓ.ም በክልል መንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ እና በሀዋሳ ከተማ መንገድ ልማትና ትራንስፖርት መምሪያ በአካል በመምጣት አሰፈላጊ ህጋዊ የሠነድ መረጃ ይዛችሁ በመቅረብ እንድታስመዘግቡ እና ተሽከርካሪውን ይዞ በመምጣት የቴክኒክ ምርመራ እንድታደርጉ እናስታውቃለን ::

ማሳሰቢያ :-
ተሽከርካሪውን በአካል ይዞ ለማይቀርቡ እና ህጋዊ ሰነድ ለሌላቸው ባለንብረቶች ምንም ዓይነት አገልግሎት የማይሰጥ መሆኑን እንገልፃለን::

የሲዳማ ክልል የመንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ
ሐምሌ, 07/2018 ዓ.ም

Sidaamu Buni kilewe 2018 M.D Itiyophiyu primiyerliige shaampiyoone ikkite boowe haadhe Hawaasira  dagganna assinoonni wo...
13/07/2026

Sidaamu Buni kilewe 2018 M.D Itiyophiyu primiyerliige shaampiyoone ikkite boowe haadhe Hawaasira dagganna assinoonni wosinsirate amanyootira Sidaamu dooggate biilloonyi massagaanonna loosaasinete hagiirri akata fototenni.

የ2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን ሲዳማ ቡና ወደ ሀዋሳ ስገባ በተደረገው የጀግና አቀባበል ወቅት፣ የሲዳማ መንገዶች ባለሥልጣን አመራሮችና ሠራተኞች የደስታ ድባብ በፎቶ።

Ijaarsu aana afantanno buussa mereerinni.Muli yannara yaano 2018 Baajetete diro Sidaamu dooggate biilloonyinni ijaarsa h...
08/07/2026

Ijaarsu aana afantanno buussa mereerinni.

Muli yannara yaano 2018 Baajetete diro Sidaamu dooggate biilloonyinni ijaarsa hananfoonni buussa mereerinni Ciroone woradira Yaanootu olliira loosamanni afamannohu Mittu Bidirsu buusa ikkanna safote loosi(Foundation) ollonketenni loosantanni afantannoho.

Konne buusa baxxinoha assannosiri Oromiyu qoqqowi Guji zoone Daggalu ollii widoonni xaadisannoha ikkasinni lamente dagara dagoomitte xaadooshshe kalaqannoha ikkasiiti.

Layiinkihu Ciroone woradi giddo Bidirsu buusinni 4 K.M ikkannokki xeertinyira ijaaranna afamannohu Namicha Kiiro 2 buusi afamannoha ikkanna buusu Bidirsa massitanno doogo iima ijaaramanni afamannoho.

Sayiikkihu, Bansanna Burru woradda xaadisannote Shantaweenne - Burra- Gaaxa doogo iima ijaarranna safote loosi jeefeenna xaphoomu loosi 40% iille afamanno buusaati.

Buussa ijaarate loosi jawa woxu fulo xa'mannoha ikkirono dagate doogote latishshi xa'mo qola batinye danchu gashshooti xa'mo qola ikkitinohura qoqqowu mootimma 10% nni kayiise 95% geeshsha iillite afantannota haammata buussate ijaarsi loossa Dooggate biilloonyi annimmanni ijaarantanno gede assitanni afantanno.

2018 Baajetete diro Badheessu agani kawa calla 8 haaro buussa addi addi qooxora ijaarsate loosi aleenni xawinsi jeefishshi bisooti.

Maaja 1/2018M.D Si/Do/Biilloonyi Mootimmate komunikeeshiine !!

የባረ ድልድይ ግንባታ አፈጻጸም አሁናዊ ሁኔታ፣ባረ ድልድይ እየተገነባ የሚገኘው በምስራቃዊ ሲዳማና ማዕከላዊ ሲዳማ ዞን አዋሳኝ ወረዳዎች ቡራና አርበጎ መካከል ባረ ወንዝ ላይ ነው።ድልድዩ በደ...
11/06/2026

የባረ ድልድይ ግንባታ አፈጻጸም አሁናዊ ሁኔታ፣

ባረ ድልድይ እየተገነባ የሚገኘው በምስራቃዊ ሲዳማና ማዕከላዊ ሲዳማ ዞን አዋሳኝ ወረዳዎች ቡራና አርበጎ መካከል ባረ ወንዝ ላይ ነው።

ድልድዩ በደቡብ ክልል ዘመን የተጀመረ ፕሮጀክት ብሆንም ፣ከድዛይን ጋር ተያይዞ የሚታይ ክፍተት ግንባታው ተጠናቆ ሕብረተሰቡ ወንዙን እንደልብ ተሻግሮ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መስተጋብሮችን ለመከወን ሳይደርስ ቆይቷል።

ችግሩን ለመፍታት ሲዳማ መንገዶች ባለሥልጣን በድልድዩ ድዛይን ላይ ማሻሸያ በማድረግ ( መነሻ የዲዛይን ለውጥ መጀመሪያ ከነበረበት masonry retaining wall ወደ RCC or shear wall) ተቀይሮ ግንባታውን በጨረታ ላሸነፈው ኮንትራክተር በመስጠት ስራው በተገባው ውል መሠረት እየተገባደደ ይገኛል።

የሪቴንግ ዎልና ሮድ አፕሮች ስራ ከፍተኛ ዋጋ የሚያስከፍል ብሆንም የባለሥልጣን መስሪያቤት፣የመንገድ ልማትና ትራንስፖርት ቢሮ፣ እንድሁም ጉዳዩ የሚመለከታቸው የክልሉ አመራር አካላት በሚያደርጉት ክትትልና ድጋፍ ባሁኑ ስዓት ግንባታው ወሳኝ ምዕራፍ ላይ መድረስ ችሏል።

የግንባታው ቀሪ ስራ የባክ ፊልና ሮድ አፕሮች ስራ ስሆን ፣ አጠቃላይ የድልድዩ ግንባታ ስራ በሁለት ወር ውስጥ እንደሚጠናቀቅ የባለስልጣኑ የድዛይንና ኮንትራት አስተዳደር ክፍል ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት አቶ ወገነ ተሾሜ እና አቶ እንዳሌ እሽኔ የባለሥልጣኑ መንግስት ኮሙኒኬሽን ክፍል ሀላፊ አቶ አንድነት አሰፋና ባለሙያዎች ስራው ያለበትን ደረጃ በጎበኙበት ወቅት ገልጸዋል ።

።ሲዳማ መ/ባ/ሥልጣን የመ/ኮሚዩኒኬሽን ፣

የዳዬ - ግርጃ - መልካደስታ እና  መለያ - መጆ   የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ባጠረ ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነውአዲስ አበባ፣ ሰኔ 2፣ 2018 (ኢመአ)፦ የሲዳማ  እና...
09/06/2026

የዳዬ - ግርጃ - መልካደስታ እና መለያ - መጆ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ባጠረ ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 2፣ 2018 (ኢመአ)፦ የሲዳማ እና የኦሮሚያ ክልሎችን በመንገድ የሚያስተሳስረው እና 65 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው የዳዬ-ግርጃ - መልካደስታ እና መለያ -መጆ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክትን በአጠረ ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ይገኛል።

ከአጠቃላይ የግንባታ ሥራው አሁን ላይ 63 ነጥብ 4% በመቶው የተጠናቀቀ ሲሆን የአስፋልት ንጣፍ ፣ አፈር ቆረጣ እና ሙሌት ፣ የድሬኔጅ ስራዎች ፣ ሰብ ቤዝ ንጣፍ ፣ ቤዝ ኮርስ ንጣፍ እንዲሁም በርካታ የስትራክቸር ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛል።

የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ መነሻውን በምስራቃዊ ሲዳማ ዞን ውስጥ ከሚገኘው ዳዬ ከተማ አድርጎ እስከ ግርጃ/መልካ ደስታ እና መጆ ከተማ ድረስ የሚዘልቅ ነው ።

ለግንባታ ማስፈጸሚያ የሚውለውን ገንዘብ 1,555,708,167.88 (አንድ ቢሊዮን አምስት መቶ ሃምሳ አምስት ሚሊዮን ሰባት መቶ ስምንት ሺህ አንድ መቶ ስልሳ ሰባት ብር ከሰማንያ ስምንት ሳንቲም) በኢትዮጵያ መንግስት ነው የሚሸፈነው ።

ግንባታውን ቻይና ቲሲጁ ሲቪል ኢንጂነሪንግ ግሩፕ የተባለ የሥራ ተቋራጭ በማካሄድ ላይ የሚገኝ ሲሆን ፣ የማማከሩንና የቁጥጥሩን ሥራውን ደግሞ ስታዲያ ኢንጂነሪንግ ወርክስ ኮንሰልታንት በማከናወን ላይ ይገኛል።

የዚህ መንገድ ፕሮጀክት ደረጃውን በጠበቀ አስፋልት መገንባቱ ለአካባቢው ማህበረሰብም ሆነ ለመስመሩ ተጠቃሚዎች ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ እድገት ላይ ከፍተኛ ለውጥን ያመጣል።

ይህ የመንገድ ፕሮጀክት ተገንብቶ ሲጠናቀቅ በአካባቢው የሚመረቱ እንደ ቡና፣ እንሰት፣ እንዲሁም የተለያዩ ማዓድናትን ወደ ገበያ ለማቅርብ ምቹ ሁነታ ይፈጥራል።

በተጨማሪም በተሽከርካሪ ለመጓጓዝ ይወስድ የነበረውን የ 4 ሰዓት የጉዞ ጊዜ ወደ 1 ሰዓት ከማሳጠሩም ባለፈ የትራንስፖርት ተጠቃሚዎችን አላስፈላጊ እንግልት ያቃልላል።

በመስመሩ ላይ ያሉ ከተሞችን ከማስተሳሰሩም ባለፈ የከተሞችን እድገት ያፋጥናል።

የመንገድ ግንባታው በከተማ 21 ሜትር፣ በገጠር 10 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ እየተገነባ ይገኛል ።

ምንጭ፣ ኢመአ

በሀዋሳ ከተማ ለ7ኛ ሀገራዊ ምርጫ ለብልጽግና ፓርቲ   ድጋፍ ለመስጠት የተካሄደው የድጋፍ ሰልፍ ድባብ በፎቶ።
27/05/2026

በሀዋሳ ከተማ ለ7ኛ ሀገራዊ ምርጫ ለብልጽግና ፓርቲ ድጋፍ ለመስጠት የተካሄደው የድጋፍ ሰልፍ ድባብ በፎቶ።

Address

Hawassa
Hawassa
251

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Sidama Roads Authority/Sidaamu dooggate biilloonya posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share