10/05/2026
ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ የአለም አቀፍ ቀይ መስቀል እና ቀይ ጨረቃ ቀንን በታላቅ ድምቀት አከበረ።
በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር የሀረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በአለም አቀፍ ደረጃ "ትብብር ለሰብአዊነት "በሚል መሪ ቃል የሚከበረውን የአለም አቀፍ ቀይ መስቀል እና ቀይ ጨረቃ ቀንን የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ የባርድ አባላት፣ ሰራተኞች ፣ ወጣት በጎ ፍቃደኞች በጋራ በመሆን የተለያዩ የሰብአዊ ተግባራትን በማከናወን በታላቅ ድምቀት አክብረዋል።
የቅርንጫፍ ፅ/ቤቱ ሀላፊ የሆኑት አቶ አስፋው ስንበቶ የእንኮን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፈዋል ። በማስከተል የቀይ መስቀል ወጣቶች ቀኑን የሚያወሳ ስነግጥም ፣ ትያትር እና የደም የመለገስ ተግባር አድርገዋል።
በመጨረሻም የቦርድ ሊቀመንበሩ ኢንጂነር አቶ ነቢል የሱፍ የመዝጊያ ንግግር እና አራት አመት ቅ/ጽ/ቤቱን አገልግለው ለተሰናበቱ የቦርድ አባላት ሽኝት በማድረግ ኘሮግራሙ ተጠናቆል።
ግንቦት 1/2018 ዓ/ም
ለሰብአዊነት እንኖራለን!!
---------------