09/04/2026
እንኳን አደረሳችሁ
ምስጋና ለጎንደር ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ጽሕፈት ቤት!
መና የአረጋውያንና የአዕምሮ ሕሙማን መርጃ ማዕከል ከ2006 ዓ.ም ጀምሮ በማዕከሉ የሚኖሩ አረጋውያንን፣ ሕፃናትንና የአዕምሮ ሕሙማንን በምገባና በተለያዩ አገልግሎቶች በመደገፍ ላይ ይገኛል። ለነዚህ ወገኖቻችን የምገባ ፕሮግራም ዋነኛውና ከፍተኛ ወጪ የሚጠይቅብን የማገዶ እንጨት ግዢ ነበር።
ይህንን ችግራችንን በመረዳት የጎንደር ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ጽሕፈት ቤት በጠየቅነው ቅፅበት፣ እጅግ በሚያስደንቅ ፍጥነት ምላሽ በመስጠት ለማዕከላችን የሚሆን የማገዶ እንጨት በዛሬው ዕለት በድጋፍ አበርክቶልናል። ለዚህ አርአያነት ያለው በጎ ተግባራችሁ በማዕከሉ ስም ከልብ እናመሰግናለን!
ሌሎች ተቋማትና በጎ አድራጊዎችም ይህንን ቅን ተግባር በመከተል፣ መጪውን በዓል ምክንያት በማድረግ የተለያዩ የግብዓት ድጋፎችን በማድረግ ከጎናችን እንድትቆሙ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
📍 አድራሻችን፦
ጎንደር ከተማ፣ ቀበሌ 15 (ከስታድየም ጀርባ ወይም ከቅርጫት ኳስ ሜዳ ጎን)
🏦 የባንክ ሂሳብ ቁጥሮቻችን፦
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፦ 1000089064868
አማራ ባንክ፦ M1818
📞 ለበለጠ መረጃና ድጋፍ፦
WhatsApp፦ 0934641310 0934641309
Telegram፦
Facebook፦ መና የአረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል
Email፦ [email protected]
#ሆሳዕና #ጎንደር #ትንሣኤ #ምስጋና