07/06/2026
በጎንደር ከተማ አስ/ባ/ቱ/ ስፖርት መምሪያ ከጥር 30 እስከ ግንቦት 30/2018 ዓ.ም በመካሄድ ላይ የነበረው ሮድ 2028 የእግር ኳስ ጨዋታ ፍፃሜውን አግኝቷል።
የመዝጊያ ፕሮግራም ላይ የጎንደር ከተማ አስ/ባ/ቱ ስፖርት መምሪያ ኃላፊ ወ/ሮ ማርያም ካሳሁን ባስተላለፉት መልዕክት አገራችን ኢትዮጵያ የአፍሪካን እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከመሰረቱት አገራት መካከል የምትገኝ ሲሆን በዘርፉ ያላትን ተሳታፊነትና ተጠቃሚነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀነሰ መምጣቱ የሚታወቅ ነው፡፡
ለዚህም እንደ ምክንያት ከሚነሱት መካከል የስፖርት ማዘውተሪያ እጥረት ሲሆን ይህን ችግር ለመፍታት ከኮሪደር ልማት ጋር በተያያዘ በከተማችን ጎንደር የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እግርኳስ፤ ቅርጫት ኳስ ፤ ግራውንድ ቴንስ፤እና ሌሎች የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራወች ተገንብተዋል ብለዋል።
በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ በርካታ ሀገራት ለላቁ ስፖርተኞች ልማት የተለየ ትኩረት በመስጠት ከታዲጊ ወጣቶች መሠረታዊ የስፖርት ስልጠና ጀምሮ እስከ ከፍተኛ ደረጃ የስፖርት ስልጠናዎች ድረስ ሀገራዊ ስትራቴጂዎችን እና ፕሮግራሞችን በመቅረፅ ከፍተኛ የመንግስት በጀት መድበው ሲንቀሳቀሱ ይስተዋላል፡፡
የተተኪ ስፖርተኞች ልማትን በማጠናከር የአሸናፊ አገርን ግብ ለማሳካትና ስኬቱን ለማስቀጠል የተለያዩ እንቅስቃሴዎች ቢደረጉ በሚፈለገው መጠን ውጤታማ ለማድረግ ይቻል ዘንድ ክቡር የኢ.ፌ.ዳ.ሪ. ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ለጉዳዩ ልዩ ትኩረት በመስጠትና በተለየ አግባብ (Intervention) በመውሰድ የተተኪ
ስፖርተኞች ልማት ስራን በተለይም በእግር ኳስ ስፖርት በአገሪቷ ያለውን የህዝቡን ፍላጎት እና ኢትዮጵያን የሚመጥን ውጤት በአህጉራዊ እና አለም አቀፋዊ መድረኮች ላይ ለማስመዝገብ በእርሳቸው ተነሳሽነት (Initiative) ልዩ ስልት በመቀየስ ከመላ አገሪቱ በተወጣጡ አሳታፊ በሆነ መንገድ እና ልዩ እምቅ አቅም ያላቸውን (Talent) ታዲጊዎች በስፋት በመምመልና ልዩ ስልጠና በመስጠት አሸናፊ ብሔራዊ ቡድን መፍጠርን ያለመ ልዩ ፕሮግራም መሆኑን ገልፀዋል።
በውድድሩ ከ13 ዓመት በታች 27 ቡድን
ከ 15 ዓመት በታች 14 ቡድን
በአጠቃላይ 41 ቡድኖች 74 ጨዋታዎች በማድረግ ከ13 ዓመት በታች የቆየ ተስፋ 2 ለ 0 አራጋው ከ 15 ዓመት በታች ጎንደር ዮኒቨርስቲ 3 ለ 0 ጌች ማድሪድን በማሸነፍ የዋንጫ ባለቤ ሆነዋል።
ለአሸናፊዎች ዋንጫ ለኮከብ ተጫዋቾች፣ግብ አግቢዎች፣አሰልጣኞች ሽልማት ተበርክቶላቸዋል ብዛት ያላቸው ታዳሚዎች ፕሮግራሙን ተከታትለዋል።