17/09/2025
ዛሬ ገንዘብ ልመና አይደለም አመጣጤ የቀና ልቦና እና የጊዜ እንጅ
ግን እስከመጨረሻው ይነበብ
ሸር ሸር ሸር አድርጉልን
መሰሉ እንዳልክ ይባላል የ22 አመት ወጣት ሲሆን 9ኛ ክፍል እያለ ድንገት ታሞ ከትምህርት ገበታ ቀረ በኋላም በህክምና ቢረዳም መድሐኒት መውሰድ ላይ የሚቆጣጠረው በማጣቱ የተነሳና በተስፋ መቁረጥ ወደ መጠጥ በመግባት መድሐኒቱን አቋርጦ ዛሬ በቀላሉ መዳን የሚችል ወጣት በሰንሰለት ታስሮ በቤት ተቀምጧል። ዶክተሮችን ቤት ወስጀ ለማሳየት ሞከርሁ እናም በህክምና ቋንቋ የህመሙን አይነት Schizophrenia with psychotic feature plus Epilepsy(የአዕምሮ ጤና ችግር እና የሚጥል በሽታ በጋራ) በሚል ገልፀውልኛል
በመድሐኒት መከታተል የሚቻል ቢሆንም ከልጁ ከጎኑ ሰው አለመኖርና ጠባቂ ማጣት መድሐኒቱን በተገቢው አለመውሰድ ወደ ከፋ ደረጃ ያደርሰዋል የሚል ሙያዊ አስተያየታቸውን ሰጠዋል።
በመሆኑም ይህንን ወጣት ከአንድ ደካማ እናቱ ጋር ተነጋግረን የተደረሰበት ውሳኔ በአዲስ አበባ የአእምሮ ማገገሚያ ቦታ በተለይም መቄዶንያ; ጌርጌሶን እና መሰል በጎ አድራጎት ማህበራትና ማገገሚያ ቦታዎች ሂዶ መቀመጥ ቢችል በቀላሉ ለውጥ ማምጣት የሚችል በመሆኑ እስኪ አዲስ አበባ ያላችሁ ወንድም እህቶቼ ማገገሚያ ቦታ የምታውቁ ካላችሁ አለያም አፈላልጋችሁ አለያም ስልክ ካወቃችሁ በውስጥ መስመር ላኩልንና እና ልጁ ለተወሰኑ ጊዚያት አብሮ የሚቆይበትን እድል እንፍጠርና እንታደገው
ለበለጠ መረጃ 0952346172