ጨለሚት ኪዳነምህረት ገዳም

ጨለሚት  ኪዳነምህረት  ገዳም ሌቦች ታቦቶን ለመሰረቅ ሲሉ ዓይናቸዉን በማጨለም በዚያዉ ዙሪያ ሲሸከረከሩ በመገኘታቸዉ ልዩ ቦታዉ ጨለሚት ኪዳነምህረት ተብሎ ሊጠራ ችሎል፡፡
(7)

በሰመ አብ ወወልድ ወመንፈሰ ቅድሰ አሐድ አምላክ አሜን፡፡
“ ኪዳነ ተካየድኩ ምሰለ ኅሩያንየ/ ከመረጥኃቸዉ ጋር ቃል ኪዳንን አደረግሁ”
መዝ 88፡3
ይህ ገጽ የተከፈተው በስለት ነውና
ገዳሞ ቆላ ስለሆነች በአካባቢው ስው ስለሌላ ቅዳሴ የሚቀድስ ካህናትም ሆነ አስቀዳሽ ስው ስላልነበረ በየወሩ በኪዳነምህረት ዕለተ ቀን የቅዳሴ እንዲቀደስ ነበር ኪዳነምህረት ስለት ስምታ ይሀው በጸበሎ ታላቅ ፈውስ እየስራች ያለች ጥንታዊና ታሪካዊ ገዳም ነች።
•••
እኛን የስማች ወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያም በቃል ኪዳኖ ሁላችንም ከመከራ ስጋ፣ ከመከራ ነፍስ ትጠብቀን።

።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ጨለሚት እመ ገነት ቅድሰ

ት ኪዳነምህረት ቤተ-ክርሰቲያን ገዳም አጭር ታርክ፤-
•••
አመሰራረት፡- ዘመንፈሰ ቅድሰ እና አርከ ሥሉሰ የተባሉት ወንድማማች የቤተ ክርሲትያን ካህናት አባቶች ከጎንደር ተቦተ ኪዳነምህረትን ይዘው ሲመጡ በራዕይ ቦታውን እየመራቻቸው " ሸዋ ውሰጥ አረቆ ቆላ በተባለዉ በረሃ ዉሰጥ አኑሩኝ " በማለት አሁን በምትገኝበት ቦታ ላይ ለማረፍ ችላለች ፡፡
•••
ዘመኑም ከአባቶች በተገኘ መረጃ መሰረት በአፄ ይኩኑ አምላክ ዘመነ መንግሰት (ከ1270-1285) ባለዉ ዘመን ጀምሮ በሳር በተሰራ ቤተመቅደሰ እሰከ ጣሊያን ወረራ ድረሰ ነበር ፡ በአምሰት አመት ከ1928-1933 ዓ.ም. ውሰጥ በሳር የተሰራዉ ቤተ-መቅደሰ ሊፈርሰ ችላል በድጋሚ የሳር ቤተመቅደሰ ተሰርቶ እሰከ 1988 ዓ.ም በዚሁ አመት በቆርቆሮ ልትሰራ ችላለች በዝሁ ቤተመቅደሰ በገዳም መሰረት ትገኛለች፡፡
•••
የገዳሙ ሰም አወጣጥ እና ትርጉም፡-
•••
እመንግሰት እንደሆነ ይነገር ነበር ፡፡ በመጀመሪያ ዘመን አካባቢዉ በሚገኝ ዋሻ ዉሰጥ ለብዙ ዘመናት የቆየች ሲሆን ከዋሻው ከወጣች በሆላ የሳር ቤተ መቅደሰ በመሰራት በዚያ ዉሰጥ እያለች ሌቦች ታቦቶን ለመሰረቅ እዚያዉ አረቆ ቆላ በረሃ ዉሰጥ መጥተዉ ታቦቶን ከቤተ-መቅደሰ አዉጥተዉ ለመዉሰድ ሲሉ ዓይናቸዉን በማጨለም በዚያዉ ዙሪያ ሲሸከረከሩ በመገኘታቸዉ ልዩ ቦታዉ ጨለሚት ኪዳነምህረት ተብሎ ሊጠራ ችሎል፡፡
የገዳሙ አጭር ታሪክ እና ገቢረ ተአምር፡- ቤተክርሲትያኒቱ ጥንታዊ በመሆኖ በአፄ ይኩኑ አምላክ ዘመነ መንግሰት ጀምሮ የምትተዳደረዉ በእርሻ መሬት በሚገኘዉ አዝመራ ወይም ገቢ ነበር፡፡ የእርሻ መሬት የሚገኝበት ልዩ ሰሙ በጦል አራትያ፤ በምሰቃንቻ፤ በገዳም ምድር እና በአረቆ ቆላ በሚባለዉ ቦታ በሚገኘዉ ገቢ መሰረት ለሰሞነኞች ካህናት ደመዋዝ እና ለቤተክርሰትያን ንዋየ ቅድሳት መግዣ ይዉል ነበር፤ ይህን የእርሻ መሬት ገዳሙን የመሰረቱት አባቶች ዘመንፈሰ ቅድሰ ደጋ ላይ ያለዉን የጦል አራትያ ሲያርሱ ዉለዉ ሲያበቁ እዚያዉ አካባቢ ለክርሰትና ለማንሳት ወደ ቤተክርሰትያን ሄደዉ ቅዳሴ ቀድሰዉ ሲያበቁ በተሰጣቸዉ ፀጋ መነንፈሰ ቅድሰ መሰረት አሁን ደጋ ወይም አፈፍ ካለዉ ቅድሰ ጊዌርጊሰ ቤተክርሰትያን በመነሳት በክንፍ ጨለሚት ኪዳነምህረት ገዳም ይገቡ ነበር፤ ይህንን ድርጊታቸዉን ያየ ገበሬ እንደነርሱ እሆናለሁ ሲል ርዝመቱ በግምት 200 ሜትር በሚሆን በአራትያ በተባለ ገደል ዉሰጥ ገብቶ ሞቶል፡፡
•••
ታቦቶን ከቦታዉ ላይ በማንሳት ወደ ቃያ ገብረኤል ልዩ ሰሙ ገሜ ቅድሰት ማርያም በተባለ ቦታ ወሰደዋት የነበረ ሲሆን በሐሩር በጋ በረዶ ዝናብ በመጣል እንዲሁም በአካባቢ በሚኖሩት ሰዋች ላይ ፅኑ ደዌ እና ተዉሳክ በማምጣቶ እና በማድረሳ ወዲያዉኑ ወደ ሕየት ቅድሰ ገብረኤል ቤተክርሲትያን ወሰደዉ አዳብለዋት ነበር ፤ ከዚህም የከፋ ችግር በአካባቢዉ ነዋሪዋች ላይ በማድረሳ ወደ ደላንቻ ኢየሱስ ቤተክርሲትያን በመዉሰድ

አይ የኔታበትምህርት ዓለም ዕድለኛ ከሆናችሁ ከታላላቅ ሰዎች እግር ስር ቁጭብላችሁ ትማራላችሁ። እኔ ዕድለኛ ነኝ ብየ እግዚአብሔርን ከማመሰግንባቸው ምክንያቶች አንዱ ከመምህራኖቼ ያገኘሁት በረ...
12/06/2026

አይ የኔታ

በትምህርት ዓለም ዕድለኛ ከሆናችሁ ከታላላቅ ሰዎች እግር ስር ቁጭብላችሁ ትማራላችሁ።

እኔ ዕድለኛ ነኝ ብየ እግዚአብሔርን ከማመሰግንባቸው ምክንያቶች አንዱ ከመምህራኖቼ ያገኘሁት በረከትነው።

የኔታ ክፍሌ ብሉዩን ይተረጉማሉ በክርስቶስ ፍቅር ሁሉን ይወዳሉ። የብሉይ ኪዳን ትርጓሜ በቃል ነግረውህ የሐዲስ ኪዳኑን ትርጓሜ ደግሞ በኑሯቸው ያስጠኑሃል። እኛ ስንገባ ይተረጉማሉ፤ ለቅጸላ ወደ ውጭ ስንወጣ እስከምንመለስ ዳዊት ይደግማሉ።

አይ የኔታ!
አሁን እኛም አስተማርን ብለን።
አንድ ቀን የማይቋጠር ፊት፤ ፈገግታ የማይለየው ጥርስ። አወ የኔታከት ብለው አይስቁም እንጂ ፈገግታ ተለይቷቸው አያውቅም። የኔታ በቃላቸው እንደሚናገሩት ከንቱ ውዳሴ የራቀላቸው፣ ፍቅረ ንዋይየጠፋላቸው፣ ከሁሉም በላይ የዘመኑ በሽታ መቅደሳችንን ያረከሰውዘረኝነት ፈጽሞ ያላረፈባቸው፣ እውነተኛ የእንጦንስ የመቃርስ ተከታይንጹሕ መነኩሴ የተማሩትን የሚኖሩ የሚኖሩትን የሚያስተምሩ አባቴ መሆናቸውን እኛ ደቀ መዛሙርቶቻቸው ምስክሮች ነን።

የኔታ!
ከንቱ ውዳሴ እንዳያጠቃችሁ፤ ፍቅረ ንዋይ እንዳያሸንፋችሁ አደራ ብለውን የለ ? እያለቀስሁ ነው እምጽፍልዎት እኛ ልጆቻችሁ እንደ እናንተ ብርቱዎች አይደለንም እባክዎ በሰማይም ሆነው ይጸልዩልን?

በቤተ ክርስቲያን መኖር ማለት የቤተ ክርስቲያን ደመዎዝ ተከፋይ መሆን መስሎን የምኖርባትን ቤተ ክርስቲያን ሳናውቃት በመንፈስ ልንመላለስባት ሲገባን በሥጋ ገብተን እየኖርን ነው።

አንድ ቀን ታሪክዎትን እጽፈው/እናገረው ይሆናል የኔታ ለእርስዎ የእረፍት ቀን ዛሬ ተጀመረ። እንግዲህ ይሂዱ እንጂ ከሚወዷት ገዳምዎ ከጻድቁ ሐዋርያ ጋር በመዐርግ ከሚመስሉዎ የጻድቁ ልጆች ጋር በዚያ ይኑሩ።

የኔታ ጉልበትዎን ስሜ አጠገብዎ ቆሜ መሸኘት አልታደልሁም እባክዎ አይቀየሙኝ?
ሀገሬ እንጂ ልቤ ከእርስዎ ሩቅ አይደለም። በቃ ወደ ገዳምዎ ይግቡ።

ስምዓኮነ መልአከ / Simakone Melak የተዋስንው

ነገ በዚህ ገዳመ ኢየሱስ ቤ/ክ ታላቅየወንጌል ድግስ አለአድራሻ:-ከደብረ ገሊላ ቅዱስ አማኑኤል ቤ/ክ ወረድ ብሎ ወይም ከጦር ሃይሎች ከፍ ብሎ ሆላንድ ኢንባሲ ፊትለፊት
12/06/2026

ነገ
በዚህ ገዳመ ኢየሱስ ቤ/ክ ታላቅ
የወንጌል ድግስ አለ
አድራሻ:-
ከደብረ ገሊላ ቅዱስ አማኑኤል ቤ/ክ
ወረድ ብሎ ወይም
ከጦር ሃይሎች ከፍ ብሎ ሆላንድ ኢንባሲ ፊትለፊት

ዜና ዕረፍት+++++++++++++++++ለበርካታ ዘመናት በታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም እና በደብረ ሊባኖስ ገዳማት የብሉያት ትርጓሜ መምህር ኾነው ያገለገሉት መጋቤ ብሉይ የኔታ ክፍሌ ወ/ጊዮ...
12/06/2026

ዜና ዕረፍት
+++++++++++++++++
ለበርካታ ዘመናት በታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም እና በደብረ ሊባኖስ ገዳማት የብሉያት ትርጓሜ መምህር ኾነው ያገለገሉት መጋቤ ብሉይ የኔታ ክፍሌ ወ/ጊዮርጊስ ከዚኽ ዓለም ድካም በሥጋ ዐረፉ።

ታላቁ ሊቅ የኔታ ክፍሌ በርካታ ሊቃውንትን ያፈሩ የቤተ ክርስቲያናችን ተጠያቂ ዓይናማ ሊቅ ነበሩ።

የብሉይ ኪዳን ትርጓሜን ወንበር ዘርግተው አስቀድመው በታላቁ ደብረ ሊባኖስ ገዳም ለ 15 ዓመታት ያኽል፤ በኋላም ከ 1986 ዓ.ም ዠምሮ በታላቋ ገዳማችን ታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ የመምህራንና ቀሳውስት ማሠልጠኛ መንፈሳዊ ት/ቤት እስካረፉበት ጊዜ ድረስ አስተምረው በሺዎች የሚቆጠሩ መምህራንን አፍርተዋል።

ከተማሪዎቻቸውም መካከል ሊቃነ ጳጳሳት፣ የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች እንዲኹም በርካታ ሊቃውንት ይገኙበታል።

ትምህርትን ከብህትውና ባስተሳሰረ ሕይወታቸው ፍጹም ንጹሕ ባህታዊ የነበሩት መጋቤ ብሉይ የኔታ ክፍሌ ወ/ጊዮርጊስ ከትርጓሜ ብሉያት ባሻገር የጸዋትወ ዜማ፣ የቅኔ፣ የአቋቋም፣ የትርጓሜ ሐዲሳት እንዲኹም የፍትሐ ነገሥት ትርጓሜን ጠንቅቀው የተማሩ ይኽ ቀረኽ የማይባሉ ሊቅ ነበሩ።

መጋቤ ብሉይ የኔታ ክፍሌ ወ/ጊዮርጊስ ዛሬ ሰኔ 4 ቀን 2018 ዓ.ም ከድካመ ዓለም በሥጋ ያረፉ ሲኾን ከ 30 ዓመታት በላይ ባስተማሩባት በታላቋ ገዳማችን ታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም ዛሬ ሰኔ 4 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 9 ሰዓት ክቡር አስከሬናቸው መጥቶ ምሽት ከ 3 ሰዓት ዠምሮ እስከ ንጋት 12 ሰዓት ድረስ ጸሎተ ፍትሐታቸው በአደራረስ፣ ማሕሌት፣ ሰዓታት ይከናወናል።

በማስቀጠልም በገዳማችን ዓውደ ምሕረት የሽኝት ሥርዓቱ ከተከናወነ በኋላ ሥርዓተ ቀብራቸው በተማሩበት በመነኰሱበት እንዲኹም ጉባኤ ዘርግተው ባስተማሩበት በታላቁ ደብረ ሊባኖስ ገዳም ዛሬ ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ይፈጸማል።
++++++++++++++
የታላቁ ሊቅ አባታችን ክቡር መጋቤ ብሉይ የኔታ ክፍሌ ወ/ጊዮርጊስ በረከታቸው ይደርብን።

የታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም ገዳም መሠረተ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት

12/06/2026

የአይሁድ ምኞት

እግዚአብሔር ለነቢያት ያናገረው ተስፋ ዘመን ሲደርስ

አካላዊ ቃል በሥጋ ተገልጾ ሲያስተምር በክረስቶስ ትምህርትና ፈውስ የቀኑ የአይሁድ ሹማምንት በምክራቸው “እርሱን ብንገድለው ትምህርቱና ተአምራቱ ይቆማል ተከታዮቹም ይበተናሉ ” ብለው መክረው ነበር ።

«"ስለዚህ የካህናት አለቆችና ፈሪሳውያን የሸንጎውን አባሎች ሰብስበው እንዲህ አሉ፦ “ይህ ሰው ብዙ ተአምራት ስለሚያደርግ ምን ብናደርግ ይሻላል?"
እንዲሁ ብንተወው ሰው ሁሉ በእርሱ ያምናል፤ ሮማውያንም መጥተው ቤተ መቅደሳችንንና ሕዝባችንን ሁሉ ይደመስሳሉ »
— ዮሐ11-48

በዚህ ምክር መሠረት በጌታ የሚነገረውን ወንጌል ለማስቆም ተብሎ ክርስቶስ በአደባባይ እንዲሰቀል አደረጉ ።

ግን ምኞታቸው አልተፈጸመም አይሁድ በአዘጋጁት ሞት ክርስቶስ የሞት መ*ግ*ደያ አደረገው ። በትንሣኤውም ምኞታቸው ምኞት ብቻ ሆኖ ቀርቷል ።

ይልቁንም የጌታ ደቀመዛሙርት የወንጌል ሰባኪዎች ሆነው በዓለም ሲበተኑ ምኞታቸው ሞቶ ተቀበረ

►ሌላም ጌዜ በሐዋርያት ሥራ ምዕ 7 እንደ ጻፈው መንፈስ ቅዱስን ተሞልቶ የነበረ እስጢፋኖስ ወንጌልን ሲያስተምር ስምንት ሽኽ ማኅበር ሰብስቦ ሲያስተምር
ይሄንን ወንጌል ለማስቆም ምን ምን እናድርግ ብለው መከሩ
የሸንጎው ምኞት

የእስጢፋኖስን ስብከት ማስቀረት ስለ ነበር የማኅበሩ አለቃ በአሰቃቂ ሁኔታ በደንጋይ ተወግሮ ይ*ge*ደል ማኅበሩም ይበተናል አሉ ።

ያሉትንም ሁሉ አደረጉ እስጢፋኖስ በግፍ ተ*ገ*ደ*ለ ። ማኅበሩም በእስጢፋኖስ ምክንያት በዓለም ሁሉ ተበተኑ ነገር ግን በየሄዱበት ሁሉ ወንጌልን ሰብከው ክርስትና በዓለም ሞላ ። የእስጢፋኖስ ሞት የቤተ ክርስቲያን እውነት ክርስቶስ በዓለም ሀሉ እንዲነገር ምክንያት ሆነ ።

የአይሁድ ምኞት ምንጊዜም አልተሳካም ። የቤተክርስቲያን አምላክ ሞ*ታ*ቸውን ለሕይወት ማስፈራራታቸውን ለብርታት እያደረገባቸው ምኞታቸው ሁሉ ብቻ ምኞት ሆኗል ።

ብቸኛዋ የክርስቶስ ቤተክርስቲያን ዛሬም እስጢፋኖስ አላት ዛሬም ቁጭ ብሎ የሚመክርባት ሸንጎ አለባት ። ሸንጎው የአይሁድ ምኞት

እግዚአብሔር ለነበቢያት ያናገረው ተስፋ ሲደርስ

አካላዊ ቃል በሥጋ ተገልጾ ሲያስተምር በክረስቶስ ትምህርትና ፈውስ የቀኑ የአይሁድ ሹማምንት በምክራቸው “እርሱን ብን*ge*ድ*ለው ትምህርቱና ተአምራቱ ይቆማል ” ብለው መክረው ነበር ።

"ስለዚህ የካህናት አለቆችና ፈሪሳውያን የሸንጎውን አባሎች ሰብስበው እንዲህ አሉ፦ “ይህ ሰው ብዙ ተአምራት ስለሚያደርግ ምን ብናደርግ ይሻላል?"

— "እንዲሁ ብንተወው ሰው ሁሉ በእርሱ ያምናል፤ ሮማውያንም መጥተው ቤተ መቅደሳችንንና ሕዝባችንን ሁሉ ይደመስሳሉ።”"

— ዮሐንስ 11:48

በዚህ ምክር መሠረት በጌታ የሚነገረውን እውነት ለማስቆም ተብሎ በአደባባይ እንዲሰቀል አደረጉ ግን አይሁድ ያዘጋጁት ሞት ለሞ*ት ሞ*ት ነው የሆነበት ።

ነገር ግን የአይሁድ ምኞት በክርስቶስ መነሣት ምኞት ብቻ ሆኖ ቀርቷል ።

ይልቁንም የጌታ ደቀመዛሙርት የወንጌል ሰባኪዎች ሆነው በዓለም ሲበተኑ ምኞታቸው ሞቶ ተቀበረ

ሌላም ጌዜ በሐዋርያት ሥራ ላይ መንፈስ ቅዱስን ተሞልቶ የነበረ እስጢፋኖስ ወንጌልን ሲያስተምር ስምንት ሽኽ ማኅበር ሰብስቦ ሲያስተምር
ይሄንን ወንጌል ለማስቆም ምን ምን እናድርግ ብለው መከሩ
የሸንጎው ምኞት

የእስጢፋኖስን ስብከት ማስቀረት ስለ ነበር የማኅበሩ አለቃ በአሰቃቂ ሁኔታ በደንጋይ ተወግሮ ይge*ደ*ል ማኅበሩም ይበተናል አሉ ።

ያሉትንም ሁሉ አደረጉ እስጢፋኖስ በግፍ ተገደለ ። ማኅበሩም በእስጢፋኖስ ምክንያት በዓለም ሁሉ ተበተኑ ነገር ግን በየሄዱበት ሁሉ ወንጌልን ሰብከው ክርስትና በዓለም ሞላ ። የእስጢፋኖስ ሞት የቤተ ክርስቲያን እውነት ክርስቶስ በዓለም ሀሉ እንዲነገር ምክንያት ሆነ ።

የአይሁድ ምኞት ምንጊዜም አልተሳካም ። የቤተክርስቲያን አምላክ ሞታቸውን ለሕይወት ማስፈራራታቸውን ለብርታት እያደረገባቸው ምኞታቸው ሁሉ ብቻ ምኞት ሆኗል ።

#ብቸኛዋ #የክርስቶስ #ቤተክርስቲያን ዛሬም እስጢፋኖስ አላት ዛሬም ቁጭ ብሎ የሚመክርባት ሸንጎ አለባት ። ሸንጎው ዛሬም መበተኗን ይጠባበቃል እንዲትበተንም በሙሉ ኃይሉ እየሠራ ነው ።

የምእመናኖቿ ገ*ዳ*ነ*ዮች ፍርድ የለባቸውም ተሳዳቢዎቿም ከልካይ የለባቸውም ።

ይሄ ሁሉ #መንግሥታዊ ዝምታ #በቤተክርስቲያኗ ላይ ሁሉንም ማድረግ ትችላላችሁ የሚል የሕግ ከለላ መስጠት ይመስላል ።

የተገለጠው እውነት ግን የቤተ ክርስቲያን ጠባቂ መንፈስ ቅዱስ አንዱ እስጢፋኖስ ሲታሠር ሌላ እስጢፋኖስ ያስነሳል ።
አንዱን እስጢፋኖስ ስት*ድ*ሉት ሌላ ያስነሳል ።

ስለሆነም ብዙ አትድከሙ ከአባቶቻችሁ አትበልጡምና
ሊቀ ሊቃውንት ነቢየ ልዑል አዳሙ

12/06/2026
ጳስኮር ጳስኮር /አሽሁር/ በት ኤር ላይ የተገለጸ በቤተ መቅደስ የሚኖር ክፉ ሰው ነው ። ነቢዩ ኤርምያስ ስለ ሕዝቡና ቀጣይ ሀገር ሊገጥማት ስላለው ነገር በእውነት ሲናገር የዘመኑ ሹም ጳስኮ...
12/06/2026

ጳስኮር

ጳስኮር /አሽሁር/ በት ኤር ላይ የተገለጸ በቤተ መቅደስ የሚኖር ክፉ ሰው ነው ።

ነቢዩ ኤርምያስ ስለ ሕዝቡና ቀጣይ ሀገር ሊገጥማት ስላለው ነገር በእውነት ሲናገር የዘመኑ ሹም ጳስኮር ሰማና ኤርምያስን አሥሮ በጽኑ ገረፈው ብዙም መከራ አደረሰበት

«አሽሁርም ነቢዩን ኤርምያስን መታው፤ በእግዚአብሔርም ቤት በነበረው በላይኛው በብንያም በር ባለው በእግር ግንድ ውስጥ ውስጥ አሰረው» ኤር 20-1

የኤርምያስ መታሠርና መገረፍ ለእውነት የተከፈለ መሥዋዕትነት ነው ኤርምያስን ማሠር ግን ከተማዋን ከጥፋት አላዳናትም ። የተናገረውንም እውነት ሀሰት አያደርገውም ።

እነ ጳስኮር ግን ሁልጊዜም የሚያደርጉት ከእውነት ተቀራኒ ሁነው « ሰላም ነው ። ረሐብ የለም ። አይመጣም ። ምርኮ የለም ። አይመጣምም ። ጌታ እንዲህ አለኝ ። ተናገረኝ ...» እያሉ ሕዝብ ማደንዘዝ ነው ።

አንተ ጳስኮር ያለን ነገር የለም በማለት እንደሌለ ማድረግ ይቻላል ?

የሆነን ነገር እንዳልሆነ በማውራት እንዳልሆነ ማድረግስ ይቻላል .?

ኤርምያስ እየተናገረ ያለው ነገር ሁሉ እኮ እየሆነ ያለውን ነገር ብቻ ነው ።

ኤርምያስ ምን ውሸት ተናገረ ?

የምእመናን መገደል በአደባባይ የተደረገ ነው
የቤተመቅደስ መቃጠል በጠራራ ጸሐይ የሆነ እውነት ነው
የክርስቲያኖች መፈናቀል ዓለም ሁሉ ያየነው እውነታ ነው
ቆይ ኤርምያስ ምን ውሸት ጻፈ ምንስ ሀሰት ተናገረ .?

አይ ጳስኮር 🤔 ለካ ዛሬም አለህ

ነቢየ ልዑል አዳሙ

" ሌቦች ታቦቶን ለመሰረቅ ከቤተ-መቅደሰ አዉጥተዉ ለመዉሰድ ሲሉ ዓይናቸዉን በማጨለም ዙሪያ ሲሸከረከሩ በመገኘታቸዉ ልዩ ቦታዉ ጨለሚት ኪዳነምህረት ተባለ"።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።የጨ...
10/06/2026

" ሌቦች ታቦቶን ለመሰረቅ ከቤተ-መቅደሰ አዉጥተዉ ለመዉሰድ ሲሉ ዓይናቸዉን በማጨለም ዙሪያ ሲሸከረከሩ በመገኘታቸዉ ልዩ ቦታዉ ጨለሚት ኪዳነምህረት ተባለ"
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የጨለሚት ኪዳነምህረት ገዳም
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
አድራሻ፣

ስሜን ሽዋ ሀገረ ስብከት መንዝ ላሎ ምድር ወረዳ ቤ/ክ ፣ ወገሬ ከተማ ልዩ ስሙ አረቆ ትምህርት ቤት ተወርዶ ከደጋ ወደ ቆላ ውስጥ በእግር ከግማሽ ስዓት ቁልቁለት ተወርዶ ገዳሞ ትገኛለች።
•••
ትራንስፖርት
ከአዲስ አበባ ከላምበረት መናኃሪያ ግቢ በዘብር ገብርኤል በሚል ወይም፣ ከስሜን አቅጣጫ ለሚመጣ ከደብረ ብርሀን ከተማ በመምጣት ወገሬ ወይም ዘብር ገብርኤል በሚለው በትራንስፓርት ማግኘት ይቻላል።

" #ሼር"ማድረግ ለእናንተ አይነገርም???
10/06/2026

" #ሼር"ማድረግ ለእናንተ አይነገርም???

ዛሬ የተነበበታምረ ማርያምከበዓታ ነገሥት በዓታ ማርያም አራት ኪሎ ታላቁ ቤተመንግሥትግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም.
10/06/2026

ዛሬ የተነበበ
ታምረ ማርያም
ከበዓታ ነገሥት በዓታ ማርያም
አራት ኪሎ
ታላቁ ቤተመንግሥት
ግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም.

ይህን ..."ድንግል ሆይ አንገታቸውን እንደሚያገዝፉ  እንደ ዕብራዊያን ሴቶች ልጆች በዋዛ ያደግሽ አይደለም፡፡ በንጽህና በቅድስና በቤተ-መቅደስ ኖርሽ እንጂ"  ቅዳሴ ማርያምልመናዋ ክብሯ የል...
10/06/2026

ይህን ...
"ድንግል ሆይ አንገታቸውን እንደሚያገዝፉ እንደ ዕብራዊያን ሴቶች ልጆች በዋዛ ያደግሽ አይደለም፡፡
በንጽህና በቅድስና በቤተ-መቅደስ ኖርሽ እንጂ" ቅዳሴ ማርያም
ልመናዋ ክብሯ የልጇ ቸርነት በሁላችን ላይ ይደርብን፡፡
********
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

ይህ ዕለት የልዑል እግዚአብሔር እውነተኛ መቅደስ የምትሆን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ወደ ቤተ መቅደስ የገባችበትን ዕለት የምናስብበት ነው፡፡ የአምላክ እናት ከእናት ከአባቷ ቤት ተለይታ እግዚአብሔር ወደመረጠላት ሥፍራ ወደ ቤተ መቅደስ ገባች፡፡ ዕድሜዋ ሦስት ዓመት ነበር፡፡
አባታችን ኢዮብ እንደተናገረው “ሁሉን ማድረግ እንደሚቻለው፤ በባሕርይው የሚሣነው እንደሌለ አሳቡንም ይከለከል ዘንድ ከቶ እንደማይቻል” 《 ኢዮ 42፡2 》አውቀን ለተጠራንበት ዓላማ መልስ መስጠት ክርስቲያናዊ ግዴታ ነው፡፡
እግዚአብሔር ሲጠራ፣ ልዑል ሲናገር የዕድሜ ጉዳይ የጾታ ጉዳይ የዜግነት ጉዳይ የአቅም ጉዳይ የጊዜ ጉዳይ የስልጣን ጉዳይ የእውቀት ጉዳይ ሥፍራ አይገኝላቸውም፡፡ ጥያቄ ውስጥም የሚገቡ አይደሉም፡፡ እኛ ግን እንኳንስ ራሳችንን ለሕይወት ዘመን አገልግሎት ልንሰጥ ይቅርና በተወሰነ ሰዓት ለሚሆነው መውጣት መግባት እየተቸገርን ነው፡፡ አገልግሎት ለእግዚአብሔር ያለንን ፍጹም ፍቅር የምንገልጽበት በሕይወታችንም ተጠቃሚ የምንሆንበት ምሥጢር ነው፡፡
ወደ ቀደመ ነገራችን እንመለስ ጥንተ ነገር አባቷ ቅዱስ ኢያቄም እናቷ ቅድስት ሐና እንደ መጽሐፍ ቃል፥ እንደ አባቶች ሥርዓት፥ እንደኦሪቱ ሕግ በእግዚአብሔር ትእዛዛትና ሕግጋት ሁሉ እየሄዱ በእግዚአብሔር ፊት ፍጹም ጻድቅ ነበሩ፡፡ ነገር ግን ልጅ አልነበራቸውም፡፡ ስዕለት ተሳሉ፤ እግዚአብሔር ልጅ ብቻ ሳይሆን ፈጣሪዋን የምትወልድ ከመልኳ ደም ግባት ይልቅ የልቡናዋ ደም ግባት ደስ የሚያሰኝ፤ አሸናፊ የሚሆን የእግዚአብሔር አብን የባሕርይ ልጅ በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ በድንጋሌ ኅሊና ጸንሳ የወለደች የብርሃን እናትን ወለዱ፡፡
ሊቃውንቱ “ማኅጸነ ሐና ሕያው ሰማያተ ገብረ”፤ ሕያው የሆነ የሐና ማኅጸን ሰማይ የተባለች ቅድስት ድንግል ማርያምን አስገኘ በማለት ዘመሩ፡፡ እግዚአብሔር ስጦታው ድንቅ ነው የለመኑትን ሳይሆን ሰዎች ፈጽሞ ሊያስቡት ቀርቶ ሊገምቱት የማይቻለውን ስጦታ ይሰጣል፡፡
የአባታቸውን የነቢዩን ዳዊት ቃል ቃላቸው አድርገው በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ደጅ ይጠኑ የነበሩ ቅዱስ ኢያቄምና ቅድስት ሐና “እኔ ግን በምሕረትህ ብዛት ወደ ቤትህ እገባለሁ አንተን በመፍራት ወደ ቅድስናህ መቅደስ እሰግዳለሁ” 《 መዝ 5፡7 》 በማለታቸው የጸሎታቸው ውጤት ብቻ ሳትሆን የእግዚአብሔር ስጦታ የምትሆን፣ ፍጥረት ሁሉ ተሰብስቦ ቢመዘን የአንዲቱን የጸጉሯን ዘለላ የማያክል ቅድስት ድንግልን ወለዱ፡፡ ከእግዚአብሔር የተቀበሉአትን ቅድስት ለእግዚአብሔር ሊሰጡአት ስዕለት ተስለው ነበር፡፡
አስቀድሞ በቤተ እስራኤል ዘንድ ደናግል በቤተ መቅደስ ውስጥ የሚቀመጡበት ሥርዓት አልነበረም፡፡ በርግጥ በኦሪቱ ነቢይት በአፍአ እንደነበረች ተገልጧል፤ ነገር ግን የእመቤታችን ወደቤተ መቅደስ መግባትና የነቢይት ወደ ቤተ መቅደስ መግባት የተለየ ነው፡፡ በዓይነትም በመጠንም የሚነጻጸር አይደለም፡፡
ቅድስት ድንግል ማርያም ከሦስት ዓመቷ እስከ አሥራ አምስት ዓመቷ ለአሥራ ሁለት ዓመታት በቤተ መቅደስ ቆየች፡፡ ሕያው መቅደስ፥ እመቤትና የአምላክ እናት የምትሆን ቅድስት ድንግል በእነዚህ ዓመታት መላእክት ምግቧንና መጠጧን እያመጡ ከዜማው ጣዕም የተነሣ አጥንትን የሚያለመልም የመላእክትን ዝማሬ እያዳመጠች በቤተ መቅደስ ኖረች፤ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን “ንጽሕተ ንጹሐን ከወይና ከመ ታቦተ ዶር ዘሲና ውስተ ቤተ መቅደስ ነበረት በድንግልና ሲሳያ ኅብስተ መና ወስቴሃኒ ስቴ ጽሞና” እያሉ አዲስ ቅኔን ተቀኙላት፡፡
የበዓሉ ትርጉም በዘመኑ ለምንገኝ ክርስቲያኖች
እግዚአብሔር በማንኛውም የዕድሜ ጣራ ሥር የሚገኝ ክርስቲያንን እንደሚፈልግ የተመለከትንበት ዕለት ነው፡፡ በአቅማችን እንድንነጋገር ስለሚያስፈልግ እንጂ የበዓሉ ትርጉም ከዚህም በላይ ላይ ነው፡፡ በልዑል እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ስንኖር ልንከተለው የሚገባ ቅድስና በእግረ ሥጋ ለምንመላለስ ወገኖች ያለው አስተማሪነት የጎላ ነው፡፡
በሕይወት ዘመን በእግዚአብሔር ቤት ለመኖር እንፈልግ ዘንድ ፣ ሕይወታችንን በፍጹም ቅድስና እንመራ ዘንድ መቅደስ የተባለ ለእግዚአብሔር ማደሪያነት የተመረጠ ሰውነታችን ከኃጢአት ሁሉ እንጠብቅ ዘንድ የተማርነበት በዓል ነው፡፡
ይልቁንም በመከራ ጊዜ ከንፈሮቻችን የተናገሩትን ስዕለት ለእግዚአብሔር መፈጸም እንደሚገባን እግዚአብሔርን የሚያስደስተው ፍጹም ስጦታ ራሳችንን አሳልፈን ከመስጠት የበለጠ እንደሌለ ልንረዳ የሚገባን መሆኑን በዓሉ ያስተምራል፡፡
ልመናዋ ክብሯ የልጇ ቸርነት በሁላችን ላይ ይደርብን፡፡

Address

በስሜን ሽዋ መንዝ ላሎ-ምድር ወረዳ ወገሬ ከተማ ልዩ ስሙ አረቆ ቅ/ሚካኤል ወይም አረቆ ት/ቤት
Debre Birhan

Opening Hours

07:30 - 01:00

Website

ለግዜው ይህን ይጠቀሙ

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ጨለሚት ኪዳነምህረት ገዳም posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share