Reach One Touch One Mission/ ROTOM - Ethiopia ሮቶም ኢትዮጵያ

Reach One Touch One Mission/ ROTOM - Ethiopia ሮቶም ኢትዮጵያ ROTOM-Ethiopia is a CSO that help elders and their dependents to live with dignity and fulfillment.

🙌ትልቅ ምስጋና🙌ዕድሜ እየገፋ ሲመጣ፣ጉልበት አቅም ሲያጣ ፣አይኖች እየፈዘዙ ሲመጡ ፣ጆሮም ለመስማት ሲርቅ ተፈጥሮ እርጅናን እያሳበቀች ትመጣለች።እርጅናውም ሲመጣ እንደ ቀድሞ ሰርጉን፣ክርስትና...
09/06/2026

🙌ትልቅ ምስጋና🙌

ዕድሜ እየገፋ ሲመጣ፣ጉልበት አቅም ሲያጣ ፣አይኖች እየፈዘዙ ሲመጡ ፣ጆሮም ለመስማት ሲርቅ ተፈጥሮ እርጅናን እያሳበቀች ትመጣለች።እርጅናውም ሲመጣ እንደ ቀድሞ ሰርጉን፣ክርስትናውን፣ሀዘኑን፣ተስካሩን ...መድረስ መካፈል መጨዋወት፣እየቀረ ይመጣና በቤት ውስጥ ብቻ ማሳለፍ ይሆናል።ይህ ደግሞ የሰው ልጅ ተስፋ መቁረጥ ላይ፣ሞትን መመኘት ላይ በትንሹም ቢሆን ያዋ*ጣል።
😊ዛሬ የከበረ ምስጋናችንን እነሆን ለማለት ነው ፤ከላይ በትንሹ ለመንደርደር የሞከርነው።
🙋የኢንጂነር አቶ ገስግስ እና የወ/ሮ ረድኤት ቤተሰቦች የሁለተኛ ልጃቸውን ክርስትና በዕለተ ዕሁድ በማዕከላችን ውስጥ ከአረጋውያን በማክበር ቁርስ በማብላት አሳልፈዋል።ስላደረጋችሁት መልካም ነገር
ምስጋናችን እጅግ ከፍ ያለ ነው።ሁልግዜም በዙሪያችን አሉ ከምንላቸው መካከል እናንተ ፊተኞችስለሆናችሁ፣ድጋፋችሁ እና እርዳታችሁ በፈለግን ግዜ ሁልግዜም ቀኝ እጃችሁን ሰለምትሰጡን እናመሰግናችኃለን!ምን እንላለን? የአረጋውያን ምርቃት ይከተላችሁ!!

🤔እርስዎስ መቼ ሊመጡ አስበዋል?ከታች ባለው አድራሻ ደውለው ያግኙን

ይምጡ #ይጎብኙን #ይመረቁ #ለአረጋውያን ደስታን ይፍጠሩ

አድራሻ :ቀበሌ 5 ኮንዶሚኒየም ሳይደርስ ከውሀ ልማት አጠገብ

⭐️ክብር የተሞላበት የተሟላ ህይወት ለአረጋውያን ይገባቸዋል!⭐️

ለድጋፍ 1000256601951 ROTOM Ethiopia (CBE)

📞0999000444/0989707777

😱እንደዚህም መደገፍ ይቻላል ለካ😱በወቅቱ ሙቀት ምክንያት ማዕከላችን በትንንሽ እና በሽታ አስተላላፊ በሆኑ ነፍሳት ተቸግረን ነበር።ይህን ተከትሎ ማዕከላችንን ለማፅዳት በቀጠርነው ግዜ ውስጥ ለ...
04/06/2026

😱እንደዚህም መደገፍ ይቻላል ለካ😱

በወቅቱ ሙቀት ምክንያት ማዕከላችን በትንንሽ እና በሽታ አስተላላፊ በሆኑ ነፍሳት ተቸግረን ነበር።ይህን ተከትሎ ማዕከላችንን ለማፅዳት በቀጠርነው ግዜ ውስጥ ለፅዳት የምንፈልጋቸውን pest control ስንፈልግ #አቢሲኒያ ፀረ ነፍሳት(Abyssinia pest control)ያገኘናቸው።እነሱም የምትሰሩት ስራ መልካምነት ነው።እኛም ከመልካም ስራ ጋር እንተባበራለን፤ስለዚህ ሙሉ የፀረ ነፍሳት አገልግሎት እና ፅዳቱን #በነፃ እናደርጋለን በማለት ቃላቸውን ሰጡ እንዳሉትም አደረጉትም።ምን እንላለን ሁሌም እንደምንለው የአረጋውያኑ ምርቃት ዕድሜ ዘመናችሁን ይከተላችሁ!ለእኛ እንደቆማችሁልን ለእናንተም ቀኝ ዕጁን የሚሰጣችሁ ይስጣችሁ!
በዕለቱም
👉ከ40,000 birr በላይ የፀረ ነፍሳት መድሐኒት ለአገልግሎት ውሏል።
👉6 ትልልቅ የአጋረውያን መኝታ ክፍሎች፣2ሰፋፊ የዕቃ ማካማቻ፣ትልቅ አዳራሽ፣የምግብ ማብሲያ የሰራተኛ ቢሮች ፀረ ነፍሳት መድሐኒት መርጨት
🙌በቢሾፍቱና አካባቢው ለምትገኙ ሆቴሎች፣ሪዞርቶች፣ካምፓሶች፣የጋራ ማደሪያ ቤቶች፣የዕቃ ማከማቻ ቤቶች....በበረሮ፣በትኃን ፣በትንኝ ፣አይጥ እናም በሌሎች የተቸገራችሁ ደውላችሁ አግኟቸው።በዕውቀት የተመሠረተ፣በልምድ የካበተ፣በቅልጥፍና የተሞላ ሙሉ አገልግሎት ታገኛላችሁ!!
pest control
at our centre
cleaning
Ethiopia
and fullfilled lives for elders.

እናንተስ በምን እናግዝ አላችሁን?በወደዳችሁት ፣በዕውቀታችሁ፣በሀሳባችሁ፣በሙያችሁ፣.....
ይምጡ #ይጎብኙን #ይመረቁ #ለአረጋውያን ደስታን ይፍጠሩ

አድራሻ :ቀበሌ 5 ኮንዶሚኒየም ሳይደርስ ከውሀ ልማት አጠገብ

⭐️ክብር የተሞላበት የተሟላ ህይወት ለአረጋውያን ይገባቸዋል!⭐️

ለድጋፍ 1000256601951 ROTOM Ethiopia (CBE)

📞0999000444/0989707777

🕌 EID Al ADHA🕌ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች ለሆናችሁ ቤተሰቦቻችን፣አብሮ ሰራተኞች፣አጋዥ ወዳጆቻችን፣በጎ ፈቃደኞቻችን እንዲሁም በሮቶም ኢትዮጵያ ድጋፍ የሚደረግላችሁ አቶ እንድሪ...
27/05/2026

🕌 EID Al ADHA🕌

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች ለሆናችሁ ቤተሰቦቻችን፣አብሮ ሰራተኞች፣አጋዥ ወዳጆቻችን፣በጎ ፈቃደኞቻችን እንዲሁም በሮቶም ኢትዮጵያ ድጋፍ የሚደረግላችሁ አቶ እንድሪስ ዑመር እና ወ/ሮ ዘሙ እና ቤተሰቦቻቸው ሁሉ እንኳን ለ1447ኛው የኢድ አል-አድሃ(አረፋ)በዓል በሰላም አደረሳችሁ!አደረሰን!

🌙በዓሉ የሰላም፣የደስታ፣የመደጋገፍ፣የመከባበር እንዲሆን ሮቶም ኢትዮጵያ የአረጋውያን መርጃ ማዕከል ይመኛል።

🌟ክብር የተሞላበት የተሟላ ህይወት ለአረጋውያን ይገባቸዋል🌟

🙌ትልቅ ምስጋና🙌"መልካምነት ለክፉ ቀን ስንቅ ነው፤ነገን ያሳምራል፤መልሶም ይከፍላል።"መልሶ ይከፍላል ሲባል ግን ነገ ላይ ምን ያህል እንደምንቀበል አስበን፣ደምረን፣ቀንሰን፣ አባዝተን ፣አካፍለ...
25/05/2026

🙌ትልቅ ምስጋና🙌

"መልካምነት ለክፉ ቀን ስንቅ ነው፤ነገን ያሳምራል፤መልሶም ይከፍላል።"
መልሶ ይከፍላል ሲባል ግን ነገ ላይ ምን ያህል እንደምንቀበል አስበን፣ደምረን፣ቀንሰን፣ አባዝተን ፣አካፍለን ዛሬ የምናደርገው ሳይሆን ፣ለምናደርግላቸው ሰዎች ምን ያክል ብናደረግ ይገባቸዋል ብለን በብዙ ቸርነት የምናሳየው ፍቅር እንጂ!!

👉የወ/ሮ ዘውድአለም አካሉ ቤተሰቦች በማዕከላችን በመገኘት አረጋውያንን ስለጎበኛችሁ ማዕድ ስላጋራችሁ ምስጋናችን የላቀ ነው።
😊መምጣት ፣መጎብኘት ለምትፈልጉ ከታች ባሉት አድራሻዎች አግኙን።
መልካም ቀን

ይምጡ #ይጎብኙን #ይመረቁ #ለአረጋውያን ደስታን ይፍጠሩ

አድራሻ :ቀበሌ 5 ኮንዶሚኒየም ሳይደርስ ከውሀ ልማት አጠገብ

⭐️ክብር የተሞላበት የተሟላ ህይወት ለአረጋውያን ይገባቸዋል!⭐️

ለድጋፍ 1000256601951 ROTOM Ethiopia (CBE)

📞0999000444/0989707777

ትልቅ ምስጋና ለዳንፈር አካዳሚ😇መልካምነትን ቀድመን ከቤተሰቦቻችን እንማራለን።ቀጥለን ከማህበረሰባችን ከዛን ደግሞ ቤተሰቦቻችን እና ማህበረሰቡ ከላከን ከዕውቀት መንደር ከሆነው ከትምህርት ቤቶ...
15/05/2026

ትልቅ ምስጋና ለዳንፈር አካዳሚ
😇መልካምነትን ቀድመን ከቤተሰቦቻችን እንማራለን።ቀጥለን ከማህበረሰባችን ከዛን ደግሞ ቤተሰቦቻችን እና ማህበረሰቡ ከላከን ከዕውቀት መንደር ከሆነው ከትምህርት ቤቶቻችን ከዛን ..እያልን ብዙ መጥቀስ እንችላለን።
👨‍🏫በዚህ አጋጣሚ ከዕውቀት ባለፈ ትውልዱን በመልካም ስነምግባር ስለምትቀርፅሉን መምህራን እና ት/ቤቶች፣እኛም ሁሉ የእናንተ ውጤቶች ነን እና የከበረ ምስጋናችን ከልባችን ይድረሳችሁ!!
🏣በዱከም ከተማ መቀመጫውን ያደረገው #ዳንፈር primary,secondary and preparatory Academy," are for the community "በሚል project ተማሪዎችን በመልካምነት ማሳ እያሰማራ ለሌሎች መቆረስን ከህፃናት እስከ ትልቁ ድረስ እያስተማረ ዱከም ላይ ብዙ ድጋፎችን በማድረግ ላይ ያለ አንጋፋ ት/ቤት ነው።እኛም ከጎናችን እንዲሆኑ፣ እየተሰራ ያለውን ስራችን እንዲያዩ ባቀረብንላችሁ ጥሪ መሰረት "ነገ ፣ቆይ፣ሳምንት ፣next year "ሳይሉ ምሳሌ የሆኑላቸውን ተማሪዎቻቸውን፣መምህራኖችን፣ወላጆችን እና ርዕሰ መምህራኖችን ይዘው ከተፍ አሉልን።
✨በዕለቱም አረጋውያንን፣የተሰሩ ስራዎችን፣ በዕቅድ የተያዙ እና ወደ ስራ የተገቡባቸው እቅዶች ላይ ማብራሪያ ተሰጥቷል።
👉25 ፍሬ የታሸገ ፓስታ፣29.5kg መኮረኒ፣11&1/2 kg ሩዝ፣1እሽግ ፓስቲኒ የንፅህና መጠበቂያ ሳሙናዎች ልገሳ ተደርጓል።
👉በማዕከላችን ለሚኖሩ አረጋውያን ምገባ ተደርጓል።
👉ከአረጋውያን ጋር የጨዋታ እና የመዝናናት ግዜ በማድረግ በደማቅ እና በደስታ ቀኑ አልፏል።
ምስጋናችን የላቀ ነው!ገና ብዙ ስራዎች አብረን እንሰራለን!

🙋አረጋውያን ማለት የሀገር ባለውለታዎች ፣የትውልድ አባቶች፣መንገድ ጠራጊዎች፣የታሪክ ባለቤቶች ምናልባትም ታሪክ ናቸው ብንል የሚቃወም አይኖርም።,,,ስለዚህም እነዚህን በትውልድ መሐል ያሉ ሀብቶችን በማዕከል በመምጣት ከእነሱ ጋር ግዜያችሁን አሳልፉ!!
ይምጡ
#ይጎብኙን #ይመረቁ #ለአረጋውያን ደስታን ይፍጠሩ

አድራሻ :ቀበሌ 5 ኮንዶሚኒየም ሳይደርስ ከውሀ ልማት አጠገብ

⭐️ክብር የተሞላበት የተሟላ ህይወት ለአረጋውያን ይገባቸዋል!⭐️

ለድጋፍ 1000256601951 ROTOM Ethiopia (CBE)

📞0999000444/0989707777

🙌ትልቅ ምስጋና ለወ/ሮ ዝናሽ መርጊያ ቤተሰቦች እና ለአቶ ሰለሞን🙌😊የዕለቱ መጋጣጠም ቆንጆ አጋጣሚ ፈጥሮ አልፎልናል።የአረጋውያን ህይወት ወደ ኃላ ሄደን ብንበረብር ለዚች ውድ ሀገር ያልተዋጋ...
08/05/2026

🙌ትልቅ ምስጋና ለወ/ሮ ዝናሽ መርጊያ ቤተሰቦች እና ለአቶ ሰለሞን🙌

😊የዕለቱ መጋጣጠም ቆንጆ አጋጣሚ ፈጥሮ አልፎልናል።የአረጋውያን ህይወት ወደ ኃላ ሄደን ብንበረብር ለዚች ውድ ሀገር ያልተዋጋ፣ ዋጋ ያልከፈለ ለማግኘት ያስቸግራል።ሚያዚያ 27 የአርበኞች ቀን ካልን በተዘዋዋሪ የአረጋውያን ቀን ማለት እንችላለን።ቀኑ ለሰራተኛ የዕረፍት እንደመሆኑ አረጋውያን" ሰራተኛ ዛሬ አይገባም ቀኑ ሊረዝም ነው" ብለው ሳይጨርሱ የወ/ሮ ዝናሽ መርጊያ ቤተሰቦች እና አቶ ሰለሞን "እኛ አለን የአባታችን የአቶ ሀይሌን የ7ኛ ሙት አመት መታሰቢያን አብረን እናሳልፋለን እንዲሁም ዕለቱ መድሐኒያለም ነው በማለት ቆንጆ የሀበሻ ዳቦ እና የጣፈጠ ቁርስ ይዘውልን በጠዋት መጡ።
በዕለቱም
👉 25 በማዕከላችን የሚኖሩ አረጋውያንን
👉7 የማዕከሉ ሰራተኞች
👉2 የማዕከሉን በጎ ፈቃደኞች
ዕጅግ የጣፈጠ ቁርስ ፣ ሻይ እና ዳቦ ማግኘት ችለዋል።
😇የወ/ሮ ዝናሽ ቤተሰቦች እንዲሁም አቶ ሰለሞን (ሶል) የሁልግዜም ቤተሰቦቻችን ናችሁ።ለአረጋውያን ያላችሁን ፍቅር እና እንክብካቤ ከልባችን አይጠፋም።
አቶ ሀይሌ ነፍሶት በሰላም ከደጋጎች ጎን ትረፍ!ነፍስ ይማር!!እናመሰግናለን የአረጋውያን በረከት ይከተላችሁ!!

ልደት፣ የምርቃት በዓል፣ ወይም ማንኛውንም የግል ደስታችሁን በማእከላችን ካሉ አረጋውያን ጋር በማሳለፍ የነፍስ እርካታን እንድታገኙ ጥሪያችንን እናቀርባለን። የእናንተ ትንሽ ድጋፍ ለእነሱ ትልቅ ደስታ ነው።

ይምጡ #ይጎብኙን #ይመረቁ #ለአረጋውያን ደስታን ይፍጠሩ

አድራሻ :ቀበሌ 5 ኮንዶሚኒየም ሳይደርስ ከውሀ ልማት አጠገብ

⭐️ክብር የተሞላበት የተሟላ ህይወት ለአረጋውያን ይገባቸዋል!⭐️

ለድጋፍ 1000256601951 ROTOM Ethiopia (CBE)

📞0999000444/0989707777

🙌የላቀ ምስጋና ለ NOVA Gym🙌."እኛን የተንከባከቡንን መልሶ መንከባከብ ኃላፊነትም መታደልም ነው።"😊NOVA Gym  አባላት ከዚህ ዓላማችን ጎን በመቆም ለአረጋውያን ያሳያችሁት በጎነት እ...
30/04/2026

🙌የላቀ ምስጋና ለ NOVA Gym🙌.

"እኛን የተንከባከቡንን መልሶ መንከባከብ ኃላፊነትም መታደልም ነው።"
😊NOVA Gym አባላት ከዚህ ዓላማችን ጎን በመቆም ለአረጋውያን ያሳያችሁት በጎነት እና ፍቅር ይለያል።

💥ቀኑ እሁድ ነው።ወዳጆቻችንን፣ዘመዶቻችንን የምናገኝበት፣ከእነሱ ጋር ግዜ ለማሳለፍ የማይበቃበት፣የምንሄድበት የቀጠርነው ብዙ የሆነበት ነገር ግን ይሄን ሁሉ ትታችሁ ከአረጋውያን ጋር እናሳልፍ በማለት በእሁድ ማዕከላችን ሞቅ ስላረጋችሁ እና ግዜ ስላሳለፋችሁ ክብረት ይስጥልን።የዕድሜያችሁ ማታ የደመቀ ያማረም ይሁንላችሁ!

😱በዕለቱም
👉ለ25 አረጋውያን እና ከ6 በላይ በጎ ፈቃደኞችና የማዕከሉ ሰራተኞች የጣፈጠ ምገባ ተደርጓል።
👉ቆንጆ የቡና ግዜ እና ከአረጋውያን ጋር የመጨዋወት ግዜ ተደርጓል።
👉2 ካርቶን ባለ 5 litre ጤና የምግብ ዘይት ድጋፍ ተደርጎልናል።

በድጋሚ ፈጣሪ ያክብርልን፤የአረጋውያኑ ምርቃት ይከተላችሁ!

#ይምጡ #ይጎብኙን #ይመረቁ #ለአረጋውያን ደስታን ይፍጠሩ
አድራሻ :ቀበሌ 5 ኮንዶሚኒየም ሳይደርስ ከውሀ ልማት አጠገብ

⭐️ክብር የተሞላበት የተሟላ ህይወት ለአረጋውያን ይገባቸዋል!⭐️

ለድጋፍ 1000256601951 ROTOM Ethiopia (CBE)

📞0999000444/0989707777

😊ትላንትማ አለም ነበር😊የሰንበት ብርሀን ጨምሮ የበራበት፣የምስጋና እና እልልታ ድምፅ ከሮቶም አዳራሽ የተሰማበት፣የሙሽሪት(ቤቲ) እና የሙሽራው(በዕምነተ) ውበት ከፀሀዪ በላይ እጅግ ያየለበት፣...
27/04/2026

😊ትላንትማ አለም ነበር😊

የሰንበት ብርሀን ጨምሮ የበራበት፣የምስጋና እና እልልታ ድምፅ ከሮቶም አዳራሽ የተሰማበት፣የሙሽሪት(ቤቲ) እና የሙሽራው(በዕምነተ) ውበት ከፀሀዪ በላይ እጅግ ያየለበት፣ደካማ አረጋውያን ናፎቆት የሰመረበት፣የካህን አባታችን የቅዱስ ቃሉ ትምህርት የተሰማበት ፣የመዘምራን ድምፅ እንደ መላዕክት ዝማሬ ዕጅግ የደመቀ ቀን ትላንት ዕሁድ(18/08/2018) የእነ በዕምነት & የቤቲ ሰርግ በማዕከላችን የሆነ ለታ ነበር።

"ልጅ የለኝ የልጄን ሰርግ አልበላ፣ዘመድ የለኝ ሰው አይጠራኝ" ብለው የተረሱትን አረጋውያን አስታወሳችሁልን።
በረከታቸው ይከተላችሁ፣ይቺ ቀን የበረከት መታሰቢያ ትሁንላችሁ!

👩‍❤️‍👨 ለእኛ ድርብ ደስታ ሆነልን።እናንተ በቅዱስ ቁርባን ጋብቻ ተጣመራችሁ፤እንዲሁም አረጋውያንን አስታውሳችሁ የደስታችሁ ተካፋይ አደረጋችኃቸው።ላሳያችሁን ትልቅ ፍቅር እና አክብሮት ልዑል አምላክ ትዳራችሁን በፍቅር ፣በደስታ፣በሀሴት ይባርክላችሁ!

🙌በዕለቱም
👉የዝማሬ፣የቃለ እግዚአብሔር ትምህርት፣የሙሽሮች መልዕክት የተላለፈበት
👉ሙሽሮች ፣ ቤተሰቦቻቸው እና ዘማሪዎች ያስተናገዱበት
👉በመኖሪያ ቤታቸው ሆነው ለምንረዳቸው ጭምር ጥሪ ተደርጎ የሚመጡበትም የሚመለሱበት የትራንስፖርት ወጪ በሙሽሮች በሙሉ ተሸፍኖ ቆንጆ የጣፈጠ እና ሙሉ የምሳ ግብዣ፣የቡና ፣የኬክ ስነስርዓት ከአረጋውያኖቻችን ጋር የተደረገበት ዕጅግ የተዋበ እና የደመቀበት ድንቅ ቀን ነበር።

በዕምነት እና ቤቲ መልካም የትዳር ዘመን ይሁንላችሁ! ምስጋናችን ከልብ ነው!

እናንተስ በልዩ ቀኖቻችሁ አረጋውያንን በማስደሰት በረከትን መካፈል ትፈልጋላችሁ?

ልደት፣ የምርቃት በዓል፣ ወይም ማንኛውንም የግል ደስታችሁን በማእከላችን ካሉ አረጋውያን ጋር በማሳለፍ የነፍስ እርካታን እንድታገኙ ጥሪያችንን እናቀርባለን። የእናንተ ትንሽ ድጋፍ ለእነሱ ትልቅ ደስታ ነው።

ይምጡ #ይጎብኙን #ይመረቁ #ለአረጋውያን ደስታን ይፍጠሩ

አድራሻ :ቀበሌ 5 ኮንዶሚኒየም ሳይደርስ ከውሀ ልማት አጠገብ

⭐️ክብር የተሞላበት የተሟላ ህይወት ለአረጋውያን ይገባቸዋል!⭐️

ለድጋፍ 1000256601951 ROTOM Ethiopia (CBE)

📞0999000444/0989707777

የተስፋ ማለዳ በፀሀያማዋ ቀን ለአረጋውያኖቻችን! ☀️✨ዛሬ በሮቶም ኢትዮጵያ የአረጋውያን ማዕከላችን ያለው ድባብ ልክ እንደ ማለዳዋ ፀሐይ ብሩህና በተስፋ የተሞላ ነው። የአረጋውያን አባቶቻችን...
23/04/2026

የተስፋ ማለዳ በፀሀያማዋ ቀን ለአረጋውያኖቻችን! ☀️✨

ዛሬ በሮቶም ኢትዮጵያ የአረጋውያን ማዕከላችን ያለው ድባብ ልክ እንደ ማለዳዋ ፀሐይ ብሩህና በተስፋ የተሞላ ነው። የአረጋውያን አባቶቻችንንና እናቶቻችንን ህይወት በብርሃን ለመሙላት ያቀድናቸው ስራዎች ፍሬ እያፈሩ ይገኛሉ። ለአረጋውያኖቻችን የአይን ማየት ብርሃን መመለስ ማለት የተሰረቀ ማንነታቸውንና ክብራቸውን እንደመመለስ ነው።

በ ✨Engage Now Africa እና ✨በቢሾፍቱ ሆስፒታል (Bishoftu Hospital) በተዘጋጀው ነፃ የአይን ምርመራ አረጋውያኖቻችን ተጠቃሚ ሆነዋል።

በምርመራውም፦
📍 **62 አረጋውያን** የአይን ምርመራ አግኝተዋል።
📍 **10 አረጋውያን** ደግሞ ሙሉ በሙሉ ነፃ የዓይን ሞራ (Cataract) ቀዶ ጥገና እንዲያገኙ ተለይተዋል።

በቅርቡ እነዚህ እናትና አባቶቻችን በድጋሚ ማየት ሲጀምሩ የሚሰማቸውን ስሜትና ታሪካቸውን የምናካፍላችሁ ይሆናል።

✨ የአረጋውያኖቻችንን ተስፋና ክብር ለመመለስ ለምታደርጉት ድጋፍ **Engage Now Africa** እና **የቢሾፍቱ ሆስፒታል**ን ከልብ እናመሰግናለን።

ይህ ሁሉ ስራ ስኬታማ እንዲሆን ለተጋቹ ለደከማችሁ፣ አረጋውያኑን በምርመራው ወቅት ስታስተባብሩና ስታደርሱ ለነበራችሁ የሮቶም ኢትዮጵያ ሰራተኞችና በጎ ፈቃደኞች ላቅ ያለ ምስጋና ይገባችኋል። የእናንተ ቅንነትና ትጋት የተቋማችን የጀርባ አጥንት ነው።👏

**የጥሪ ግብዣ!** 🤝
እንደዚህ ያሉ በጎ ተግባራት ላይ በሙያችሁ መሳተፍ የምትፈልጉ የጥርስ ሐኪሞች፣ የዓይን ሐኪሞች፣ ጠቅላላ ሐኪሞችና ሌሎች የጤና ተቋማት በጋራ ለመስራት በራችን ሁሌም ክፍት ነው። በሙያችሁ የአረጋውያንን ህይወት መለወጥ ትችላላችሁ!

አብረን በጎ እንስራ፣ የአረጋውያንን ህይወት እንለውጥ!

ለበለጠ መረጃ በ0989707777/ 0999000444 ይደውሉ

Address

Hirna To Chelekleka Condominium
Bishoftu
1478

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:00
Tuesday 09:00 - 17:00
Wednesday 09:00 - 17:00
Thursday 09:00 - 17:00
Friday 09:00 - 17:00
Saturday 09:00 - 17:00

Telephone

+251989707777

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Reach One Touch One Mission/ ROTOM - Ethiopia ሮቶም ኢትዮጵያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Reach One Touch One Mission/ ROTOM - Ethiopia ሮቶም ኢትዮጵያ:

Share