18/06/2026
“Healthy Village” Project Successfully Concludes with Workshop in Bahir Dar
ORDA Ethiopia held a closing workshop for the integrated "Healthy Village Programme," which was implemented over five consecutive years (2020–2025) across two woredas (districts) in the East Gojjam Zone (Goncha Siso Enese, and Enbise Sar Midir). The project significantly contributed to reducing child stunting and waterborne diseases caused by poor sanitation.
Funded by the government and led by the Foundation, the project was primarily executed by ORDA Ethiopia in collaboration with other partners.
Key Achievements:
• Health and Sanitation Improvements: The prevalence of diarrhea among local children dropped from 28% to 7%, driven by community-led latrine construction and behavioral change education.
• Clean Water Supply: New water facilities were constructed, and existing ones were rehabilitated, benefiting communities living in challenging terrains.
• Nutrition and Job Creation: Nutritional support ("Mitin") was provided to pregnant and lactating mothers, alongside the promotion of year-round vegetable production and modern agricultural technologies. Additionally, youth and women's entrepreneurship was supported through the establishment of Village Economic and Social Associations (VESA).
የ«ጤናማ መንደር» ፕሮጀክት የማጠናቀቂያ ወርክሾፕ በባሕርዳር ከተማ ተካሄደ፡፡
አመልድ ኢትዮጵያ በምሥራቅ ጎጃም ዞን በሁለት ወረዳዎች ለ5 ዓመታት (2020–2025) ሲተገብር የቆየውን የ«ጤናማ መንደር ፕሮግራም» (Healthy Village Programme) የማጠናቀቂያ ወርክሾፕ አካሄደ። በኔዘርላንድስ መንግሥት የገንዘብ ድጋፍ እና በማክስ ፋውንዴሽን መሪነት የተከናወነው ይህ ፕሮጀክት፣ በሕፃናት ላይ የሚከሰተውን መቀጨጭ እና የንጽሕና ጉድለት በሽታዎችን ለመቀነስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርጓል።
ዋና ዋና ስኬቶች፦
• የጤና መሻሻል፦ በሕፃናት ላይ ይከሰት የነበረው የተቅማጥ በሽታ ምጣኔ ከ28% ወደ 7% ዝቅ ብሏል።
• የንጹሕ ውሃ አቅርቦት፦ በአስቸጋሪ መልክዓ-ምድር ለሚኖሩ ማኅበረሰቦች አዳዲስ የውሃ ተቋማት ተገንብተዋል፤ ነባሮቹም ተጠግነዋል።
• ሥርዓተ-ምግብ እና የሥራ ፈጠራ፦ ለእናቶች የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትና የግብርና ቴክኖሎጂዎች የተስፋፉ ሲሆን፣ በገጠር የመንድር ማህበራዊ ቁጠባና ብድር ማኅበራት (VESA) አማካኝነት የወጣቶችና የሴቶች የሥራ ፈጠራ ተደግፏል።
ይህ ስኬታማ ተሞክሮ በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር አማካኝነት በአገር አቀፍ ደረጃ ጥቅም ላይ ይውላል ተብሏል። «ከሥርዓተ-ምግብ እጥረት የጸዳ ሰጤናማ መንደር» ፍኖተ-ካርታ እንደ ዋና መነሻ ሆኖ እንዲያገለግል መደረጉ ታውቋል።