19/05/2026
በተንታ ወረዳ በአማራ ልማት ማህበር (አልማ) የገንዘብ ድጋፍ በአጅባር ከተማ የተገነባው ሞደል ቅድመ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ግንባታ ተጠናቆ ተመረቀ።
-------//////------
በተንታ ወረዳ በአማራ ልማት ማህበር (አልማ) የበጀት ድጋፍ በአጅባር ከተማ የተገነባው ሞደል ቅድመ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ግንባታ ተመርቋል። ለግንባታው 9 .5 ሚሊዮን ብር ወጪ እንደተደረገበት የተንታ ወረዳ አልማ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍስሃ ጌታሁን ተናግረዋል።
በምርቃት ፕሮግራሙ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የተንታ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ መሀመድ ሠይድ እንደተገለጹት አልማ በወረዳችን ውስጥ ዘርፈ ብዙ የልማት ተግባራት እያከናወነ መሆኑን ገልፀው ዛሬ ለምረቃ የበቃው ዘመናዊ ቅደመ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ግንባታ የአልማን አጋርነት በትልቁ የሚያሳይና የእኛው፤ በእኛው፣ ከእኛው የሆነ የልማት አጋር መሆኑን ያመላከተ ነው ብለዋል።
የት/ቤቱ መገንባት ከ350 በላይ ህፃናትን በስታንዳርዱ መሠረት እንዲማሩ ትልቅ አስተዋፅኦ የሚያበረክት ከመሆኑ ባሻገር በቀጣይም በሌሎች ቦታዎች መሠል ግንባታዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የሚያስችል ነው።
በምርቃት ሥነ-ስርዓቱ ላይ የደቡብ ወሎ ዞን መሬት መምሪያ ኃላፊ አቶ አብዱሮህማን ይመር ጨምሮ ሌሎች የወረዳው የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም የአካባቢው ነዋሪዎች ታድመዋል።መረጃው የተንታ ወረዳ ኮሙኒኬሽን ነው ፡፡
አልማ ፡11/09/2018 ዓ.ም
በራስ አቅም የመልማት ምልክት- አልማ
የአልማ ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ ፡ https://web.facebook.com/profile.php?id=100067437643052
ቴሌግራም ፡-https://t.me/AmharaDevtAssociation
ዮቱዮብ፡-https://www.youtube.com/
ዋትስ አፕ:https://chat.whatsapp.com/H9JxxgVUcdo5NRENaUCSYK
ቲክቶክ:tiktok.com/.devt.assoc
ዌብሳይት: www.ada.org.et
ሺህ ሆነን እንደ አንድ፤ አንድ ሆነን እንደ ሺህ!