Amhara Development Association- ADA Head office

Amhara Development Association- ADA Head office Amhara Development Association was established as a nongovernmental organization in 1992 to fill the Social development gap of the Region.

በተንታ ወረዳ በአማራ ልማት ማህበር (አልማ) የገንዘብ ድጋፍ በአጅባር ከተማ የተገነባው ሞደል ቅድመ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ግንባታ ተጠናቆ ተመረቀ።-------//////------በተንታ ወረዳ በ...
19/05/2026

በተንታ ወረዳ በአማራ ልማት ማህበር (አልማ) የገንዘብ ድጋፍ በአጅባር ከተማ የተገነባው ሞደል ቅድመ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ግንባታ ተጠናቆ ተመረቀ።
-------//////------
በተንታ ወረዳ በአማራ ልማት ማህበር (አልማ) የበጀት ድጋፍ በአጅባር ከተማ የተገነባው ሞደል ቅድመ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ግንባታ ተመርቋል። ለግንባታው 9 .5 ሚሊዮን ብር ወጪ እንደተደረገበት የተንታ ወረዳ አልማ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ፍስሃ ጌታሁን ተናግረዋል።

በምርቃት ፕሮግራሙ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የተንታ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ መሀመድ ሠይድ እንደተገለጹት አልማ በወረዳችን ውስጥ ዘርፈ ብዙ የልማት ተግባራት እያከናወነ መሆኑን ገልፀው ዛሬ ለምረቃ የበቃው ዘመናዊ ቅደመ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ግንባታ የአልማን አጋርነት በትልቁ የሚያሳይና የእኛው፤ በእኛው፣ ከእኛው የሆነ የልማት አጋር መሆኑን ያመላከተ ነው ብለዋል።

የት/ቤቱ መገንባት ከ350 በላይ ህፃናትን በስታንዳርዱ መሠረት እንዲማሩ ትልቅ አስተዋፅኦ የሚያበረክት ከመሆኑ ባሻገር በቀጣይም በሌሎች ቦታዎች መሠል ግንባታዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ የሚያስችል ነው።

በምርቃት ሥነ-ስርዓቱ ላይ የደቡብ ወሎ ዞን መሬት መምሪያ ኃላፊ አቶ አብዱሮህማን ይመር ጨምሮ ሌሎች የወረዳው የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም የአካባቢው ነዋሪዎች ታድመዋል።መረጃው የተንታ ወረዳ ኮሙኒኬሽን ነው ፡፡
አልማ ፡11/09/2018 ዓ.ም
በራስ አቅም የመልማት ምልክት- አልማ
የአልማ ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ ፡ https://web.facebook.com/profile.php?id=100067437643052
ቴሌግራም ፡-https://t.me/AmharaDevtAssociation
ዮቱዮብ፡-https://www.youtube.com/
ዋትስ አፕ:https://chat.whatsapp.com/H9JxxgVUcdo5NRENaUCSYK
ቲክቶክ:tiktok.com/.devt.assoc
ዌብሳይት: www.ada.org.et
ሺህ ሆነን እንደ አንድ፤ አንድ ሆነን እንደ ሺህ!

የአማራ ልማት ማህበር (አልማ) በደቡብ ጎንደር ዞን ለሚገኙ ወጣቶችና ሴቶች የሚውል ከ130 ሚሊዮን ብር በላይ የሥራ ዕድል ፈጠራ ስምምነት ተፈራረመ፡፡----------/////---------የ...
19/05/2026

የአማራ ልማት ማህበር (አልማ) በደቡብ ጎንደር ዞን ለሚገኙ ወጣቶችና ሴቶች የሚውል ከ130 ሚሊዮን ብር በላይ የሥራ ዕድል ፈጠራ ስምምነት ተፈራረመ፡፡
----------/////---------
የአማራ ልማት ማህበር (አልማ) በደቡብ ጎንደር ዞን ለሚገኙ ወጣቶችና ሴቶች ሁለንተናዊ ዕድገትና ዘላቂ የሥራ ዕድል ፈጠራ የሚውል ከ130 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የፕሮግራም አጋርነት ስምምነት በይፋ ተፈራርሟል።

ይህ መርሃ ግብር አልማ ከማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር የቀረጸው "የወጣቶች የስራ ፈጠራ ፕሮግራም (Y-SYEPA)" አካል ሲሆን፣ በአካባቢው የሚንቀሳቀሱ ሰባት አገር በቀል የወጣቶችና የሴቶች አደረጃጀቶችን በቀጥታ ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው።

በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የአልማ ስትራቴጅክና ኢኖቬሽን ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ እና የዋና ሥራ አስፈጻሚ ተወካይ አቶ አበረ መኩሪያ፣ ማኅበሩ በትምህርት፣ በጤናና በሥራ ዕድል ፈጠራ ዘርፎች ያስመዘገባቸውን አንጸባራቂ ድሎች አስታውሰዋል። በአሁኑ ወቅትም በአልማ "ብቁ ወጣት" ፕሮግራም በ23 ወረዳዎች ውስጥ ከ67 ሺህ በላይ ወጣቶችን ተጠቃሚ ለማድረግ ሌት ተቀን እየተጋ መሆኑን የገለጹት አቶ አበረ፣ የዛሬው ስምምነት የወጣቶች የስራ ፈጠራ ፕሮግራም (Y-SYEPA) የወጣቶቹን ተጨባጭ ችግሮች ጠንቅቀው የሚያውቁ የአካባቢ ማኅበራትን በቀጥታ በማሳተፍ በተመረጡ ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች ላይ በትኩረት እንደሚሠራ አብራርተዋል።

በአልማ የወጣቶች የስራ ፈጠራ ፕሮግራም (Y-SYEPA) ሊድ የሆኑት አቶ ብርሃኑ አይቸው በበኩላቸው ፕሮጀክቱ ለሁለት ዓመታት እንደሚቆይ ጠቁመው ተመራጭ ማህበራቱ በታማኝነትና በቁርጠኝነት ወደ መሬት እንዲቀይሩት ክትትልና ድጋፍ እንደሚደረግ አረጋግጠዋል።

ይህን ከፍተኛ ኃላፊነት የሚጠይቅ ፕሮግራም ከአልማ ጋር በመሆን ለመምራት ጋፋት ንግድና ማማከር ኢንተርፕራይዝ፣ የአዲስ ዘመን ከተማ አስተዳደር ወጣቶች ማህበር፣ የሊቦና አዲስ ዘመን አካባቢ የአማራ ሴት ነጋዴዎች ማህበር ቅርንጫፍ፣ የወረታ ከተማ ቀበሌ 02 ሌጋምቦ ወጣቶች መረዳጃ ማህበር፣ የሊቦ ክምከም ወረዳ አስተዳደር ወጣቶች ማህበር፣ የፎገራ ወረዳ አስተዳደር ወጣቶች ማህበር እና የፋና አካታች ገንዘብ ቁጠባና ብድር ማህበር ውል ተፈራርመዋል።

እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር እስከ 2027 በሚቆየው በዚህ ፕሮግራም አማካኝነት በሊቦከምከም፣ በፎገራ፣ በአዲስ ዘመን እና በወረታ ከተማ አስተዳደሮች ውስጥ ለሚኖሩ 5,606 ወጣቶች አዲስ የሥራ ዕድል በመፍጠር የሕይወት መሥመራቸውን ለመቀየር ግብ ተጥሏል።

በይፋዊ የፊርማ ሥነ ሥርዓቱ ላይም ጥሪ የተደረገላቸው የሥራ ኃላፊዎች፣ ባለድርሻ አካላትና ባለሙያዎች በታደሙበት በስኬት ተጠናቋል።

አልማ ፡11/09/2018 ዓ.ም
በራስ አቅም የመልማት ምልክት- አልማ
የአልማ ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ ፡ https://web.facebook.com/profile.php?id=100067437643052
ቴሌግራም ፡-https://t.me/AmharaDevtAssociation
ዮቱዮብ፡-https://www.youtube.com/
ዋትስ አፕ:https://chat.whatsapp.com/H9JxxgVUcdo5NRENaUCSYK
ቲክቶክ:tiktok.com/.devt.assoc
ዌብሳይት: www.ada.org.et
ሺህ ሆነን እንደ አንድ፤ አንድ ሆነን እንደ ሺህ!

ለአመታት ያካበተውን በጥራት የመገንባት ልምድ ሰንቆ እንደአዲስ የመጣው አልማኮን
19/05/2026

ለአመታት ያካበተውን በጥራት የመገንባት ልምድ ሰንቆ እንደአዲስ የመጣው አልማኮን

1 like. "ለአመታት ያካበተውን በጥራት የመገንባት ልምድ ሰንቆ እንዳዲስ የመጣው አልማኮን በአሚኮ ዘጋቢ"

በአልማ እና በህብረተሰብ ተሳትፎ የተገነቡ የመማሪያ ክፍሎች የክልል እና የዞን ከፍተኛ አመራሮች በተኙበት ተመርቀዋል፡፡-------/////------በለገሂዳ ወረዳ በወይን አምባ አጠቃላይ አን...
18/05/2026

በአልማ እና በህብረተሰብ ተሳትፎ የተገነቡ የመማሪያ ክፍሎች የክልል እና የዞን ከፍተኛ አመራሮች በተኙበት ተመርቀዋል፡፡
-------/////------
በለገሂዳ ወረዳ በወይን አምባ አጠቃላይ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት በአልማ እና በህብረተሰብ ተሳትፎ የተገነቡ የመማሪያ ክፍሎች የክልል እና የዞን ከፍተኛ አመራሮች በተኙበት ተመርቀዋል፡፡

በወይን አምባ አጠ/አንደኛ ደረጃ ት/ቤት ከፍተኛ የመፍረስ አደጋ የነበረውን በአዲስ በመገንባት እና የመማሪያ ክፍል እጥረት ለመቅረፍ በአልማ በጀት 10 የመማሪያ ክፍሎች ያሉት ባለ 1 ወለል ህንጻ ግንባታ በ21 ሚሊየን 851 ሺህ 548 ብር ወጪ ተገንብቶ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል ።

የተጠናቀቁት የመማሪያ ክፍሎችም ከ1250 በላይ ለሚሆኑ ተማሪዎች አገልግሎት መስጠት የሚችሉ እንደሆኑ ተመላክቷል።

በተመሳሳይም በህብረተሰቡ ተሳትፎ ከ4.9 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው 4 የመማሪያ ክፍሎች ያሉት ህንጻ ግንባታ ተጠናቋል፡፡

ሁለቱም ግንባታዎች የክልል፣ የዞን ፣ ፣የወረዳ ከፍተኛ አመራሮች፣ የሀይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና ጥሪ የተደረገላቸዉ በተገኙበት ተመርቀዋል። መረጃው የለገሂዳ ወረዳ ኮሙኒኬሽን ነው፡፡

አልማ ፡10/09/2018 ዓ.ም
በራስ አቅም የመልማት ምልክት- አልማ
የአልማ ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ ፡ https://web.facebook.com/profile.php?id=100067437643052
ቴሌግራም ፡-https://t.me/AmharaDevtAssociation
ዮቱዮብ፡-https://www.youtube.com/
ዋትስ አፕ:https://chat.whatsapp.com/H9JxxgVUcdo5NRENaUCSYK
ቲክቶክ:tiktok.com/.devt.assoc
ዌብሳይት: www.ada.org.et
ሺህ ሆነን እንደ አንድ፤ አንድ ሆነን እንደ ሺህ!

የአማራ ልማት ማኅበር አልማ በ186 ሚሊዮን ብር የተገነቡ ፕሮጀክቶች መጠናቀቃቸውን አስታወቀ። -------/////--------አልማ በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ጎንደር ዙሪያ ወረዳ ማክሰኝት ሁለ...
18/05/2026

የአማራ ልማት ማኅበር አልማ በ186 ሚሊዮን ብር የተገነቡ ፕሮጀክቶች መጠናቀቃቸውን አስታወቀ።
-------/////--------
አልማ በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ጎንደር ዙሪያ ወረዳ ማክሰኝት ሁለት ትምህርት ቤቶች የማስፋፊያ ግንባታ አስመርቆ ለአገልግሎት ክፍት አድርጓል።

የጎንደር አካባቢ አልማ ልማት ጽህፈት ቤት ዳይሬክተር ደረጀ ዘውዴ በአራቱም ዞኖች 186 ሚሊዮን ብር ወጭ 38 የትምህርት ፣ የጤና እና የስራ እድል ፈጠራ ፕሮጀክት መጠናቀቁን አስታውቀዋል።

ከእነዚህ ፕሮጀክቶች መካከል 34 የትምህርት ተቋማት ናቸው ። በቀጣይም ሌሎቹን ፕሮጀክቶችን ለመፈፀም እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።

60 ፕሮጀክት በሂደት ላይ መሆናቸውን የገለፁት ዳይሬክተሩ እስከአሁን ባለው ሂደት 120 ሚሊዮን ብር ወጭ የተደረገባቸው ሲሆን 18 ፕሮጀክት እስከ ሰኔ 30 ድረስ ለማጠናቀቅ መታቀዱን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል ።

አልማ በበጀት ዓመቱ 510 ሚሊየን ብር ለመሰብሰብ አቅዶ 130 ሚሊዮን ብር እንዲሁም 35 ሚሊየን በአይነት ፣ በሙያ እና በቁሳቁስ መሰብሰብ ተችሏል።

በጎንደር እና አካባቢው አልማ 603 ሺ አባላት በላይ ያሉት ሲሆን በበጀት አመቱ 58 ሺ አዲስ አባላት ማፍራት ተችሏል።

በቀጣይ አልማ ከደባርቅ ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር ከ120 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት ባለ አራት ፎቅ ህንፃ ለመስራት ዝግጅት መጠናቀቁን ተናግረዋል ።

በገንዲት አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከ18 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የትምህርት ቤት ማስፋፋፊያ ለመገንባት የመሰረተ ድንጋይ መቀመጡን ገልጸዋል ። መረጃው የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ኮሙኒኬሽን ነው፡፡

አልማ ፡10/09/2018 ዓ.ም
በራስ አቅም የመልማት ምልክት- አልማ
የአልማ ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ ፡ https://web.facebook.com/profile.php?id=100067437643052
ቴሌግራም ፡-https://t.me/AmharaDevtAssociation
ዮቱዮብ፡-https://www.youtube.com/
ዋትስ አፕ:https://chat.whatsapp.com/H9JxxgVUcdo5NRENaUCSYK
ቲክቶክ:tiktok.com/.devt.assoc
ዌብሳይት: www.ada.org.et
ሺህ ሆነን እንደ አንድ፤ አንድ ሆነን እንደ ሺህ!

አልማ የሕዝቡን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ ነው ፡፡ የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አወቀ አስፈሬ ------/////-------በማዕከላዊ ጎንደር ዞን በጎንደር ዙሪያ ...
18/05/2026

አልማ የሕዝቡን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ ነው ፡፡ የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አወቀ አስፈሬ
------/////-------
በማዕከላዊ ጎንደር ዞን በጎንደር ዙሪያ ወረዳ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ፕሮጀክቶች ዛሬ ተመርቀዋል።

በመርሃግብሩ የተገኙት የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አወቀ አስፈሬ በዚህ ወቅት እንዳሉት በዞኑ አልማና በህብረተሰቡ ተሳትፎ የህዝብን ተጠቃሚነት ሊያሳድጉ የሚችሉ ፕሮጀክቶች ግንባታ ተጠናክሮ መቀጠሉን አንስተዋል።

እሄን ተከትሎም የአማራ ልማት ማህበር በትምህርት ዘርፉ ውጤታማ ተግባራት እያከናወነ እንደሚገኝ አስረድተዋል።

አልማ ባለፉት ዓመታት በመንግስት አቅም ያልተሰሩ ዘርፈብዙ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ የተናገሩት ዋና አስተዳዳሪው የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ከማሻሻል ባለፈ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ እንደሆነ ተናግረዋል።

በአማራ ልማት ማህበር በዚህም በበጀት ዓመት 62 ፕሮጀክቶች እየተሰሩ እንደሚገኙ የተናገሩ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 22ቱ የሚሆኑት መጠናቀቃቸውን እና ቀሪዎቹንም እስከ ሰኔ ወር መጨረሻ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነውም ብለዋል።

የአማራ ልማት ማህበር የማሕበረሰብ አቅምን በማጎልበት የሕዝቡን የልማት ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ የሚገኝ በመሆኑ ህብረተሰቡ የበኩሉን አስተዋጽኦ እያደረገ እንደሚገኝ ገልጸዋል። መረጃው የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ኮሙኒኬሽን ነው፡፡

አልማ ፡10/09/2018 ዓ.ም
በራስ አቅም የመልማት ምልክት- አልማ
የአልማ ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ ፡ https://web.facebook.com/profile.php?id=100067437643052
ቴሌግራም ፡-https://t.me/AmharaDevtAssociation
ዮቱዮብ፡-https://www.youtube.com/
ዋትስ አፕ:https://chat.whatsapp.com/H9JxxgVUcdo5NRENaUCSYK
ቲክቶክ:tiktok.com/.devt.assoc
ዌብሳይት: www.ada.org.et
ሺህ ሆነን እንደ አንድ፤ አንድ ሆነን እንደ ሺህ!

የአማራ ልማት ማህበር በአልማ - ብቁ ወጣት ፕሮግራም ያሰለጠናቸውን የህጻናት ማቆያ አመቻቾችን አስመረቀ፣ ---------///////--------የባህርዳር ከተማ አስተዳደር አልማ ልማት ጽ/ቤ...
18/05/2026

የአማራ ልማት ማህበር በአልማ - ብቁ ወጣት ፕሮግራም ያሰለጠናቸውን የህጻናት ማቆያ አመቻቾችን አስመረቀ፣
---------///////--------
የባህርዳር ከተማ አስተዳደር አልማ ልማት ጽ/ቤት በአልማ “ብቁ ወጣት” ፕሮግራም ከፍኖተ ሰላም መምህራን ኮሌጅ ጋር በመተባበር ለተከታታይ 48 ቀናት በህጻናት ማቆያ አመቻችነት ያሰለጠናቸውን 74ወጣቶችን አሰመረቀ።

በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር የአልማ ልማት ጽ/ቤት ቤት ዳይሬክተር ተወካይ አቶ ፍቃዱ ዓለሙ ባስተላለፉት መልዕክት ፣ የወጣቶች የስኬት ማማ እውን እንዲሆን መንገዱን ያመቻቸው የአልማ “ብቁ ወጣት” ፕሮግራም በባህር ዳር ከተማ በስራ ዕድል ፈጠራው ረገድ አዲስ ምዕራፍ እየቀደደና በርካታ አበረታች ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ አብራርተዋል፡፡

የባህር ዳር ከተማ የአልማ ብቁ ወጣት ፕሮግራም ቡድን መሪ አቶ ሃብታሙ ተሰማ፣ ፕሮግራሙ በተጀመረ በአጭር ጊዜ ውስጥ ከ560 በላይ ወጣቶችን በከተማ ግብርና፣ በልብስ ስፌትና በተለያዩ የሙያ ዘርፎች በማሰልጠን ወደ ስራ ለማስገባት ሰፊ ጥረት እየተደረግ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የፍኖተ ሰላም መምህራን ኮሌጅ ዲን ተወካይ መምህር አብዮት ፍሬው በበኩላቸው ሰልጣኞቹ በቆይታቸው ዘመኑ የሚጠይቀውን ክህሎትና ዕውቀት መቅሰም እንዲችሉ ዘጠኝ መሠረታዊ ኮርሶችን በንድፈ ሃሳብና በተግባር ልምምድ በባህር ዳር ከተማ በተለያዩ ማዕከላት ተገኝተው በተግባር ልምምድ እንዲያገኙ ተደርጓል። በሂደቱም ውጤታማ ተሞክሮ ተገኝቶበታል ብለዋል።

ተመራቂ ወጣቶች በበኩላቸው፣ የቀሰሙትን እውቀትና ክህሎት በመጠቀም ራሳቸውንና ቤተሰቦቻቸውን ከመጥቀም ባለፈ ለአገራቸው ልማትና እድገት የበኩላቸውን አዎንታዊ አስተዋፅኦ ለማበርከት ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸው ለአልማ ብቁ ወጣት ፕሮግራም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

የስልጠናው ተሳታፊዎች 80በመቶ የሚሆኑት ወጣት ሴቶች ፣ ቀሪዎቹ ደግሞ ወጣት ወንዶችና አካል ጉዳተኞች መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን ከተለያዩ ተቋማት ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች በተገኙበት ለተመራቂዎች የምሰክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል፡፡
አልማ ፡09/09/2018 ዓ.ም
በራስ አቅም የመልማት ምልክት- አልማ
የአልማ ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ ፡ https://web.facebook.com/profile.php?id=100067437643052
ቴሌግራም ፡-https://t.me/AmharaDevtAssociation
ዮቱዮብ፡-https://www.youtube.com/
ዋትስ አፕ:https://chat.whatsapp.com/H9JxxgVUcdo5NRENaUCSYK
ቲክቶክ:tiktok.com/.devt.assoc
ዌብሳይት: www.ada.org.et
ሺህ ሆነን እንደ አንድ፤ አንድ ሆነን እንደ ሺህ!

አልማ በተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ አሳታፊ ዕቅድ (ICBPP) ላይ ለወረዳና ለከተማ አሰተዳደር የፕላንና ልማት ጽሕፈት ቤት ኃላፊዎች  ስልጠና ሰጠ፡፡-------///-------የአማራ ልማት ...
18/05/2026

አልማ በተቀናጀ የማኅበረሰብ አቀፍ አሳታፊ ዕቅድ (ICBPP) ላይ ለወረዳና ለከተማ አሰተዳደር የፕላንና ልማት ጽሕፈት ቤት ኃላፊዎች ስልጠና ሰጠ፡፡
-------///-------
የአማራ ልማት ማህበር (አልማ) ከሄልቬታስ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በአማራ አካባቢያዊ አስተዳደር ፕሮጀክት (ALGP+) የተቀናጀ ማኅበረሰብ አቀፍ አሳታፊ የልማት ዕቅድ አስተቃቀድ ላይ ለወረዳዎችና ለከተማ አስተዳደሮች የፕላንና ልማት ጽሕፈት ቤት ኃላፊዎች በሁለት ዙር ስልጠና ሰጥቷል ፡፡

የአማራ ልማት ማኅበር (አልማ) ከሄልቬታስ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ላለፉት ሰባት ዓመታት በደቡብ ጎንደርና በሰሜን ጎጃም ዞኖች በሚገኙ ስድስት ወረዳዎች ላይ ሲተገብር የቆየው የተቀናጀ ማኅበረሰብ አቀፍ አሳታፊ ዕቅድ (ICBPP) ከፍተኛ ስኬት ማስመዝገቡ በሰልጠናው ላይ ተመላክቷል ።

አማራ ልማት ማህበር ሕዝቡን የተቀናጀ ማኅበረሰብ አቀፍ አሳታፊ የልማት ዕቅድ ላይ ቀጥተኛ ተሳትፎና የባለቤትነት እንደፈጠር በማድረግ በሊቦ ከምከም፣ ፎገራ፣ እብናት፣ ስማዳ፣ ጎንጂ ቆለላ እና ይልማና ዴንሳ ወረዳዎች ባከናወናቸው ተግባራት፣ ማኅበረሰብን ያሳተፈ የተቀናጀ ሥራ የአካባቢን የልማት ችግሮች መቅረፍ እንደሚችል በተጨባጭ አሳይቷል። በተለይም በድህነት ተኮር ዘርፎች ላይ የተመዘገበው ተጨባጭ ልማትና ውጤት አልማን የማህበረሰቡን ለልማት የማንቀሳቀስ አቅምና ውጤታማነት በተግባር ያረጋገጠ ነው ተብሏል።

በአልማ የተመዘገበውን ይህን አበረታች ስኬት መነሻ በማድረግ የክልሉ ፕላንና ልማት ቢሮ የተቀናጀ ማኅበረሰብ አቀፍ አሳታፊ የልማት ዕቅድ አስተቃቀድ ላይ ለወረዳዎችና ለከተማ አስተዳደሮች የፕላንና ልማት ጽሕፈት ቤት ኃላፊዎች እንዲሁም የቡድን መሪዎች ከግንቦት 04 እስከ 08/2018 ዓ.ም ድረስ በሁለት ዙር የአቅም ግንባታ ሰልጠና በአማራ ልማት ማህበር (አልማ) እና በሄልቬታስ ኢትዮጵያ ተሰጥቷል፡፡

አልማ ፡09/09/2018 ዓ.ም
በራስ አቅም የመልማት ምልክት- አልማ
የአልማ ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ ፡ https://web.facebook.com/profile.php?id=100067437643052
ቴሌግራም ፡-https://t.me/AmharaDevtAssociation
ዮቱዮብ፡-https://www.youtube.com/
ዋትስ አፕ:https://chat.whatsapp.com/H9JxxgVUcdo5NRENaUCSYK
ቲክቶክ:tiktok.com/.devt.assoc
ዌብሳይት: www.ada.org.et
ሺህ ሆነን እንደ አንድ፤ አንድ ሆነን እንደ ሺህ!

የአማራ ልማት ማህበር /አልማ/ ብቁ ወጣት ፕሮግራም በህጻናት ጥበቃና እንክብካቤ ያሰለጠናቸውን 38 ሴት ወጣቶች አሰመረቀ። -------///////------የአማራ ልማት ማህበር /አልማ/ ከጎ...
12/05/2026

የአማራ ልማት ማህበር /አልማ/ ብቁ ወጣት ፕሮግራም በህጻናት ጥበቃና እንክብካቤ ያሰለጠናቸውን 38 ሴት ወጣቶች አሰመረቀ።
-------///////------
የአማራ ልማት ማህበር /አልማ/ ከጎንደር በመምህራን ኮሌጅ ጋር በመቀናጀት በአልማ ብቁ ወጣት ፕሮግራም ለ3 ወራት በህጻናት ጥበቃና እንክብካቤ ላይ ትኩረት በማድረግ ያሰለጠናቸውን 38 ሴት ወጣቶች አሰመርቋል።

በምረቃ መድረኩ ላይ የተገኙት የጎንደር ከተማ ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ ደብሬ የኋላ አልማ በርካታ ሰው ተኮር የሆነ ተግባራትን አያከናወነ መሆኑን ገልፀዋል።

በሴቶችና ህጻናት ላይ መስራት ለሀገር አድገት ትልቅ አበርክቶ ያለው መሆኑን የገለፁት ምክትል ከንቲባዋ እንዲህ አይነቱ ፕሮግራም የህጻናት ማቆያ ማዕከላት ለሁሉም ተቋማት የሚኖራቸውን አስፈላጊነት በግልጽ የሚያሳይ ነው ብለዋል።

የጎንደር ከተማ አልማ ልማት ጽ/ቤት ዳይሬክተር አቶ ይላቅ አለምሰገድ ደግሞ የህጻናት ማቆያ እንክብካቤ ማዕከላትን ማጠናከርና በዘርፉ የሰለጠነ የሰው ኃይል ማፍራት አስፈላጊ መሆኑን አስረድተዋል።

ህጻናት በደህንነት እንዲያድጉ፣ የአእምሮና የአካል እድገታቸው እንዲበረታ እና ማህበራዊ ክህሎታቸው እንዲጎለብት ፣ወላጆች ልጆቻቸው በአስተማማኝ ደህንነት እንዳሉ እንዲሰማቸው፣የቤተሰብ የኑሮ ደረጃን ለማሻሻል ፣ሴቶች በኢኮኖሚና በማህበራዊ ዘርፎች ያላቸውን ተሳትፎ ለማጠናከር ወሳኝ ድርሻ ያለው መሆኑን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል ።

የጎንደር መምህራን ኮሌጅ ዲን አቶ የሻንበል ፀሐይ ደግሞ ስልጠናው አልማ ከዩኒሴፍና ከማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር ከኮሌጁ ጋር በተደረገው የጋራ ስምምነት መሰረት ስልጠናው መሰጠቱን ገልጸዋል ።

ኮሌጂ ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ ለተቋቋሙ ኢንተርፕራይዞች ለጎንደርና አካባቢው ትምህርት ቤቶች አገልግሎት ሊሰጥ የሚችል የህፃናት የውስጥና የውጭ መጫዎቻዎችን በማምረት ላይ መሆኑን ገልፀዋል።

ኮሌጁ በቀጣይም ለ60 ሴት ወጣቶቸ በህጻናት ጥበቃና እንክብካቤ አሰልጥኖ ለማስመረቅ የቅድመ ዝግጅት ስራ እየሰራ መሆኑን አብራርተዋል።

በምረቃ ፕሮግራሙ የጎንደር ከተማ አስተዳደር ስራና ክህሎት መምሪያ ኃላፊ አቶ አበበ ላቀውን ጨምሮ የክልልና የከተማ አስተዳደሩ የስራ ኃላፊዎች በኮሌጁ እየተመረተ ያለውን የህፃናት ማጫዎች የማምረት ሂደት ጎብኝተዋል።መረጃው ጎንደር ከተማ ኮሙኒኬሽን ነው፡፡

አልማ ፡04/09/2018 ዓ.ም
በራስ አቅም የመልማት ምልክት- አልማ
የአልማ ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ ፡ https://web.facebook.com/profile.php?id=100067437643052
ቴሌግራም ፡-https://t.me/AmharaDevtAssociation
ዮቱዮብ፡-https://www.youtube.com/
ዋትስ አፕ:https://chat.whatsapp.com/H9JxxgVUcdo5NRENaUCSYK
ቲክቶክ:tiktok.com/.devt.assoc
ዌብሳይት: www.ada.org.et
ሺህ ሆነን እንደ አንድ፤ አንድ ሆነን እንደ ሺህ!

ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ  የማህበረሰብ አቀፍ ትምህርት ቤት ለመገንባት የመስሪያ ቦታ ተረከበ።-------/////-------ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ በአምስት ወራት የሚጠናቀቅ የማህበረሰብ አቀፍ ትምህርት...
08/05/2026

ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ አቀፍ ትምህርት ቤት ለመገንባት የመስሪያ ቦታ ተረከበ።
-------/////-------
ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ በአምስት ወራት የሚጠናቀቅ የማህበረሰብ አቀፍ ትምህርት ቤት ሊገነባ መሆኑን አስታወቀ።

ዩኒቨርሲቲው የቅድመ መደበኛ እና አንደኛ ደረጃ የማህበረሰብ አቀፍ ትምህርት ቤት ለማስራት የሚያስችለውን ቦታ ዛሬ ከደባርቅ ከተማ አስተዳደር ተረክቧል።

ዩኒቨርሲቲው የትምህርት ቤቱን ግንባታ በቀጣይ አምስት ወራት ለማጠናቀቅ አቅዶ እንደሚሰራ የተገለጸ ሲሆን ግንባታውን በማስተባበር በኩልም አማራ ልማት ማህበር(አልማ) እንደሚሳተፍበት ተመላክቷል።

የደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት አስማማው ዘገዬ (ዶ.ር) የማህበረሰብ ዓቀፍ ትምህርት ቤቱ መገንባት የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ አስተዋጾ ከፍያለ እንደሚሆን ጠቁመዋል።
የጎንደር እና አካባቢው አልማ ልማት ጽህፈት ቤት ዳይሬክተር ደረጀ ዘውዴ ከደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር የትምህርት ቤት ግንባታውን በማስተባበር እና በቀጣይም በሚኖሩ የትምህርት ቁሳቁስ የማሟላት ሂደቶች እንደሚሳተፉ ጠቁመዋል።

አልማ በዞኑ በተለያዩ ወረዳዎች ስድስት ትምህርት ቤቶችን በማስተባበር ገንብቶ ማስረከቡን የገለጹት አቶ ደረጀ በቀጣይ የሚጠናቀቁ ስድስት ትምህርት ቤቶችን ግንባታ እየተከታተለ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

አልማ ከትምህርት ዘርፉ በተጨማሪ በጤና እና በስራ እድል ፈጠራ እየተሳተፈ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

የደባርቅ ከተማ ከንቲባ ጌትነት ጸጋዬ በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው ቅድመ መደበኛ እና አንደኛ ደረጃ ማህበረሰብ ዓቀፍ ትምህርት ቤት መገንባቱ ለአካባቢው ማህበረሰብ ሞዴል የትምህርት ቤት ግንባታ በመሆን የሚያገለግል ነው ብለዋል።

ከተማ አስተዳደሩ ለትምህርት ቤት ግንባታው ቦታ ማመቻቸቱን እና ቶሎ ተጠናቆ ወደ ስራ እንዲገባ ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አመላክተዋል። ዘገባው የአሚኮ ነው።

አልማ ፡30/08/2018 ዓ.ም
በራስ አቅም የመልማት ምልክት- አልማ
የአልማ ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ ፡ https://web.facebook.com/profile.php?id=100067437643052
ቴሌግራም ፡-https://t.me/AmharaDevtAssociation
ዮቱዮብ፡-https://www.youtube.com/
ዋትስ አፕ:https://chat.whatsapp.com/H9JxxgVUcdo5NRENaUCSYK
ቲክቶክ:tiktok.com/.devt.assoc
ዌብሳይት: www.ada.org.et
ሺህ ሆነን እንደ አንድ፤ አንድ ሆነን እንደ ሺህ!

የአማራ ልማት ማህበር በሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደር  የቅድመ-አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ በ90 ቀናት ውስጥ ለማጠናቅ የመሰረት ድንጋይ ተቀመጠ!-------////------የአማራ ልማት...
08/05/2026

የአማራ ልማት ማህበር በሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደር የቅድመ-አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ግንባታ በ90 ቀናት ውስጥ ለማጠናቅ የመሰረት ድንጋይ ተቀመጠ!
-------////------
የአማራ ልማት ማህበር (አልማ) በሳኡዲ አረብያ በጅዳና አካባቢው ከሚኖሩ አባላትና ደጋፊዎች ባሰባሰበው ሃብት፤ በሸዋሮቢት ከተማ ለነገ አገር ተረካቢ ህፃናት የሚያገለግል ደረጃውን የጠበቀ የቅድመ-አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለመገንባት የመሰረት ድንጋይ የማስቀመጥ መርሃ ግብር ተከናውኗል ።

በማስጀመሪያ መርሃ-ግብሩ ላይ የሰሜን ሸዋ ዞን አልማ ልማት ጽ/ቤት ዳይሬክተር አቶ ደረጄ ፍቅሬ፣ የሸዋሮቢት ከተማ ከንቲባ አቶ ዘላለም መኮንን ጨምሮ ሌሎች የከተማዋ ከፍተኛ አመራሮችና የተቋም ሃላፊዎች ተገኝተዋል።

የዞኑ አልማ ልማት ጽ/ቤት ዳይሬክተር አቶ ደረጄ እንዳብራሩት፤ አልማ ባለፉት 34 ዓመታት "በራስ አቅም የራስን ችግር መፍታት" የሚል ራዕይ ሰንቆ በትምህርት፣ በጤና እና በስራ ዕድል ፈጠራ በርካታ ስራዎችን ሰርቷል። የዛሬ ትምህርት ቤት ግንባታ የአልማ አባል እናነደጋፊ በመሆኑ የጅዳ ዲያስፖራዎች በተገኘ ድጋፍ እውን የሆነ መሆኑን ገልጸው፣ ህብረተሰቡ ፕሮጀክቱ እስኪጠናቀቅ ድረስ በእኔነት ስሜት ድጋፍና ክትትል እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል።

"የሰራ ይጨመርለታል!" ያሉት የሸዋሮቢት ከተማ ከንቲባ አቶ ዘላለም መኮንን፤ የግንባታው ጊዜ 90 ቀናት የሚጠናቀቅ ቢሆንም፣ ጥራቱን በጠበቀ መልኩ በቀንና በማታ (24/7) በመስራት ከተቀመጠው ጊዜ ቀድመን አጠናቀን እናስረክባለን ብለዋል።

መንግስት ትምህርት ቤቶችን በማስፋፋት ትውልዱ ካለበት የስነ-ልቦና ጫና በማላቀቅ ሃገርን ወደነበረችበት ከፍታ ለመመለስ እየሰራ መሆኑን የገለጹት ከንቲባው ለዚህም ፕሮጀክት መሳካት ለአልማ አመራሮችንና ለዲያስፖራውን ማህበረሰብ ላደረጉት አስተዋፅኦ በከተማው ነዋሪ ስም አመስግነዋል ፡፡

በመጨረሻም የሸዋሮቢት ከተማ አልማ ጽ/ቤት ስራ አስኪያጅ አቶ ወንዶሰን አሰፋ ፕሮጀክቱ በተያዘለት ጊዜና ጥራት እንዲጠናቀቅ ጽ/ቤታቸው ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅርበት በመስራት ለአገልግሎት እንዲደርስ የበኩላቸውን አስትጽኦ እንደሚያደርጉ ተናግረዋል ።መረጃው ሸዋሮቢት ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት ነው፡፡

አልማ ፡30/08/2018 ዓ.ም
በራስ አቅም የመልማት ምልክት- አልማ
የአልማ ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ ፡ https://web.facebook.com/profile.php?id=100067437643052
ቴሌግራም ፡-https://t.me/AmharaDevtAssociation
ዮቱዮብ፡-https://www.youtube.com/
ዋትስ አፕ:https://chat.whatsapp.com/H9JxxgVUcdo5NRENaUCSYK
ቲክቶክ:tiktok.com/.devt.assoc
ዌብሳይት: www.ada.org.et
ሺህ ሆነን እንደ አንድ፤ አንድ ሆነን እንደ ሺህ!

Address

K 05
Bahir Dar

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amhara Development Association- ADA Head office posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Amhara Development Association- ADA Head office:

Share