21/08/2026
በአማራ ልማት ማህበር የአልማ ብቁ ወጣት ፕሮጀክት ከ1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያለው የህክምና መሳሪያና የቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ
------------------//////---------------
የአማራ ልማት ማህበር የደብረ ብርሃን ከተማ አልማ ልማት ጽህፈት ቤት ከአልማ ብቁ ወጣት ፕሮጀክት በተገኘዉ ፈንድ ለ04፣ለጫጫና ለደብረ ብርሃን ሆስፒታል ከ1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የሆነበት የህክምና መሳሪያ እና የቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ ።
በርክክቡ ወቅት አልማ በትምህርት፣ በጤናና በስራ እድል ፈጠራ ዘርፎች ሰፊ የልማት ተግባራትን እያከናወነ የሚገኝ ማህበር መሆኑን የደብረ ብርሃን ከተማ አልማ ልማት ጽ/ት ቤት ስራ አስኪያጅ አቶ አባተ አውግቸው ተናግረዋል።
ማህበሩ በአጼ ዘርዓ ያዕቆብ እና በጫጫ ክፍለ ከተሞች በትምህርትና ጤና ዘርፍ የሚታዩ ችግሮችን ለማቃለል ሰፊ ጥረት እያደገ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።
የጤና ዘርፉን ከመደገፍ አኳያም እስካሁን ካደረገው በተጨማሪ ዛሬ ለስነ አዕምሮና ስነ ልቦና ህክምና ድጋፍ ለሚፈልጉ ወገኖች ትኩረት በመስጠት ለጫጫ፣ ለ04 ጤና ጣቢያዎች እና ለደብረ ብርሃን ኮምሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከ1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያለው የህክምና መሳሪያ እና ለቢሮ አገልግሎት የሚውሉ የቁሳቁስ ድጋፍ መደረጉን ስራ አስኪያጁ ተናግረዋል ።
የአማራ ልማት ማህበር ከዩኒሴፍ (UNICEF) እና ማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር በአልማ ብቁ ወጣት ፕሮግራም በከተማ አስተዳደሩ ስር ለሚገኙ ጤና ጣቢያዎች እና ለደብረ ብርሃን ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝ ልዩ ልዩ የህክምና ቁሳቁሶችን ፣ፈርኒቸሮች ፣ኮምፒዩተር እና ፕሪንተር ድጋፍ ማድረጉን የደብረ ብርሃን ከተማ ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ በቀለ ገብሬ ገልጸዋል።
የተደረገው ድጋፍ በዋናነት የአዕምሮና እና የስነ ልቦና ህክምና አገልግሎት መስጠት በሚያስችሉ ክፍሎች ላይ የታዩ የቁሳቁስ ክፍተቶችን ለማሟላት ያለመ እንደሆነ ጠቁመው፣የተደረገው ድጋፍ መንግሥት የነበረበትን ክፍተት የሚሞላ መሆኑን አመልክተዋል።
ማህበሩ ማህበረሰቡን በማሳትፍ በትምህርት፣ በጤና እና በሌሎች መሰረተ ልማቶች ላይ አስተዋጽኦው የጎላ መሆኑን ገልጸው በቀጣይም ድጋፉን አጠናክሮ እንዲቀጥል አቶ በቀለ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በሌላ በኩል ድጋፉ በስነ አዕምሮ እና ስነ ልቦና ተጠቂዎች አስፈላጊ ቁሳቁሶችን እጥረት ያቃለለ መሆኑን የደብረ ብርሃን 04 ጤና ጣቢያ ኃላፊ አቶ መኮንን አይተንፍሱ ተናግረዋል።የታካሚዎችን መረጃ እና ፋይሎች ከሌሎች ጋር ሳይደራረቡ ለረጅም ጊዜ በአግባቡ ለመያዝ እንደሚያስችላቸውም ገልጸዋል ።
በተመሳሳይ ጤና ጣቢያው ከፍተኛ ታካሚ ተቀብሎ የሚያስተናግድ በመሆኑ ድጋፉ ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው ያሉት የጫጫ ጤና ጣቢያ ኃላፊ አይረስ እንን ከዚህ በኋላ በተሟላ መሳሪያ እና ግብዓት ደረጃውን የጠበቀ እና ለታካሚዎች ምቹ የህክምና አገልግሎት ለመስጠት እንደሚያስችላቸው አመልክተዋል።መረጃው የሰ/ሽዋ ዞን አልማ ልማት ጽ/ቤት ነው፡፡
#አልማ
#አልማ 15_12_2018_ዓ.ም
በራስ አቅም የመልማት ምልክት- አልማ
የአልማ ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ ፡ https://web.facebook.com/profile.php?id=100067437643052
ቴሌግራም ፡-https://t.me/AmharaDevtAssociation
ዮቱዮብ፡-https://www.youtube.com/
ዋትስ አፕ:https://chat.whatsapp.com/H9JxxgVUcdo5NRENaUCSYK
ቲክቶክ:tiktok.com/.devt.assoc
ዌብሳይት: www.ada.org.et
ሺህ ሆነን እንደ አንድ፤ አንድ ሆነን እንደ ሺህ!