09/09/2017
ሰላም ሰላም እነዴት አለችሁ?
እንደተጠበቀው ባይሆንም ከዚህ ቀደሙ ከነበረው ባልተስተካከለ ልክ አመታዊው የECOSA(2006) የመገናኘት ቀናችንን በውቧ ደብረ ዘይት (በጣም ነው ደስ ያለችኝ) አክብረናል።
በእለቱም ጥልቅ ቤተሰባዊ ወንድማማችንትን ባዘለ መልኩ በሁለት አንኳር ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ትኩረት ሰጥተን የተወያየን ሲሆን እነርንም እንደሚከተለው ቀርበዋል
#1 ECOSA እኛ በምንፈልገው እና በሚጠበቀው ልክ ማደግ አልቻለም!!!
በዚህ አይነት ሁናቴ ከቀጠለ " ህልውናው " አስጊ ደረጃ ላይ ይገኛል ስለሆነም የማህበሩን የወደፊት ትልም ለማስቀጠል በተናጠል እንዲሁም በግሩፕ በመሆን በፋይናንስ እና በሀሳብ ብናጠነክረው ( ድጋፍ ብናደርግ) ለዚህም ሲባል በባህር ዳር እና በአከባቢው የምትገኙ አባላት ነባራዊዉን ሁኔታ በመከታተል ብታሳውቁን።
ECOSA ሳይኖር re union አይታሰብም!!!
#2 በECOSA(2006) አባላት መካከል ርዕይ 2017 ( re union) ከመድረሱ ቀደም (በፊት) የዕርስ በርስ የመረዳዳት እና የመጠያየቅ ባህላችን እንዲጎለብት ጥሪ የቀረበ ሲሆን ለዚህም ይረዳ ዘንድ አመታዊግንኙነቱን በሁለት ከተሞች ላይ በተመሳሳይ ቀን ማክበር (መገናኘት) አዋጭ ሆኖ ተገኝቷል። ለዚህም ይረዳን ዘንድ ሰሜኑን በባህርዳር እና ደቡቡን በ አዲስ አበባ ግሩፕ እንደቀረቤታው በመክፈል በየአመቱ እየተገናኘን ለመወያየት እና ወደ ትዳር ለሚገቡ አለያም ለገቡ በተጨማሪም ለተመራቂ ጓደኞቻችን ደስታችንን በሐዘን ላይ የሚገኙትን በማፅናናት ወንድማዊ ጓደኝነታችንን ለማጎልበት (ለማጠንከር) አስበናል።
ምን ይመስላቹሀል? ሀሳብ እንስጥበት
N.b ትናፍቁኛላችሁ! መልካም አዲስ አመት ( Dj Baba)