የአማራ ፋኖ በባህር ዳር /Amhara Fano Bahirdar

የአማራ ፋኖ በባህር ዳር /Amhara Fano Bahirdar ፋኖነት በሰላሙ ጊዜ አራሽ ፣ቀዳሽነት በጦርነት ጊዜ ደግሞ መ?

የውስጥ ቀጋ ለውጭ አልጋ በአልጋ የሆኑ አመራሮች ፋኖን ማሳደድ ሊያቆሙ ይገባል‼️***የአማራ ፋኖ በባህር ዳር  አኩሪ ጀብድን በጋሸና ግንባር ፈፅሞ የተለመለሰ ፋኖ ጌታቸው ደሴ በግፍ እስር ...
11/01/2023

የውስጥ ቀጋ ለውጭ አልጋ በአልጋ የሆኑ አመራሮች ፋኖን ማሳደድ ሊያቆሙ ይገባል‼️
***

የአማራ ፋኖ በባህር ዳር አኩሪ ጀብድን በጋሸና ግንባር ፈፅሞ የተለመለሰ ፋኖ ጌታቸው ደሴ በግፍ እስር ላይ ነው ።

የአማራ ፋኖ በባሀር ዳር የህውሃት ሀይል የአማራን ርሰት በመውረር ፣ህዝባችንን ለማዋረድ በሶስት ዙር ወረራ ባካሄደበት ወቅት በቀደምት አማራ አባቶቻችን የፋኖነት ታላቅ እሴት ፣ ወኔ እና አልበገር ባይነት በመሰባሰብ የመጣውን ሀይል በመጣበት መንገድ ያናገረ የፋኖ ተቋም ነው ።በዚህ ታላቅ አማራዊ ተጋድሎ ሶስት ጓዶቹ የከበረ መስዕዋትነት የከፈሉ ሲሆን ፤አስራ ሰባት ጀግና አባላቱ ደግሞ ከቀላል እስከ ከባድ ቁስለኛ መሆናቸው የሚታወስ ነው ።

ነገር ግን ይህ ሁሉ ለአማራ ህዝብ የተከፈለ ታላቅ መስዕዋትነት ተረስቶ ፤ትላንት እያለ በእዬ ቀኑ ሲያውጅ የነበረ መንግስታዊ ስርዓት ፤ያለህ ይዘህ ውጣ የአማራ ህዝብ አድን ሲል የነበረ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ኮሽ ባለ ቁጥር የአማራ ፋኖን በማሰር ፣በማሳደድ እንዲሁም በማዋከብ ላይ ይገኛሉ ።የዚህ መንግስታዊ አፈና ሰለባ የሆነው ፋኖ ጌታቸው ደሴ ነው ።

በመሆኑም መንግስታዊ ስርዓቱ ከዚህ አስነዋሪ ተግባሩ እንዲቆጠብ እንዲሁም ጓዳችን ፋኖ ጌታቸው ደሴ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲለቀው እናሳስባለን ።

በመጨረሻም ለመላው የአማራ ፋኖ በባህር ዳር አባላት እና የፋኖ ደጋፊዎች ፋኖ ጌታቸውን ደሴ በዘጠነኛ ፓሊስ ጣቢያ በመገኘት ያለንን አጋርነት ፣አብሮነት እና አንድነት እንዲሁም በፍ/ቤት ቀጠሮው ቀን ማለትም ጥር 9/2015 ዓ.ም የባህር ዳር ከተማ ወረዳ ፍ/ቤት በመገኘት ያለንን ፍፁም አንድነት እንገልፅ ዘንድ የአማራ ፋኖ በባህር ዳር ጥሪውን ያስተላልፋል ።

ፋኖነት የአማራ ህዝብ ዋስትና ነው ።
ፋኖነት ይፋፋም ፤ፋኖነት ይለምልም ‼️

የአማራ ፋኖ በባህር ዳር ጓዶቻችን  በጋሸና ግንባር ታላቅ መስዕዋትነት የከፈሉበትን  አንደኛ አመት በጧፍ ማብራት ታስቧል‼️የአማራ ፋኖ በባህር ዳር ጀግና  አባላት አሸባሪው የህውሀት ሀይል ...
03/12/2022

የአማራ ፋኖ በባህር ዳር ጓዶቻችን በጋሸና ግንባር ታላቅ መስዕዋትነት የከፈሉበትን አንደኛ አመት በጧፍ ማብራት ታስቧል‼️

የአማራ ፋኖ በባህር ዳር ጀግና አባላት አሸባሪው የህውሀት ሀይል የአማራ ህዝብ ለማዋረድ ፣ አንገት ለማስደፋት እና አገራችን ለማፈራረስ አልሞ ጦርነት በመክፈቱ ፤ ይህንን ጦርነት ለመቀልበስ በተደረገ ጦርነት ከፍተኛ ተጋድሎ ያደረገ የአማራ ፋኖ ስብስብ ነው ።

የአማራ ፋኖ በባህር ዳር በጋሸና ግንባር ተሰልፎ ጠላት አይሰበርም ብሎ የተማመነበትን የአርቢት ምሽግ ለመደርመስ ታላቅ መስዋዕትነት ከፍሏል ።በተከፈለው የከበረ መስዕዋትነት 17 ጓዶቻችን ቁስለኛ ሲሆኑ ፤3 ጓዶቻችን የህይወት መስዕዋትነት ከፍለዋል ።

የህይወት መሰዋዕትነትን የከፈሉት የሚከተሉት ናቸው ፦
1).ፋኖ ማንደፍሮ አድማሱ

2).ፋኖ ሙሉቀን አዳነ

3).ፋኖ አሰናቀው ንጋቱ ናቸው ።

በዛሬው ዕለትም የአንደኛ የመስዋዕትነት መታሰቢያውን የአማራ ፋኖ በባህር ዳር አባላት ፣የተሰው ጓዶቻችን ቤተሰቦች በተገኙበት በጧፍ ማብራት ዘክረነዋል ።

የከፋላችሁት ታላቅ መሰዋዕትነት አማራ አንገቱ ቀና አድርጎ እንዲሄድ አድርጋችኃል ።ለተከፈለው መስዕዋትነት ልባዊ ክብር አለን ።

ትግላችን አልተቋጨም ። ትግላችን ይቀጥላል ።የትግላችን መዳረሻ የአማራ ህዝብ ነፃነት ነው ።

አርበኝነት አማራዊ ውርሳችን ፤ፋኖነት ከአባቶቻችን የወረሰነው ታላቁ እሴታችን ነው ‼️

ፋኖ አርበኛ ዘመነ ካሴ ነገ መስከረም 23/2015 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 ሰዐት የባህር ዳር ከተማ ከፍተኛ ፍ/ቤት ይቀርባል ‼️የአማራ ፋኖዎች  በሁሉም አቅጣጫ ለአማራ ህዝብ ብለን በቆሰልን ...
02/10/2022

ፋኖ አርበኛ ዘመነ ካሴ ነገ መስከረም 23/2015 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 ሰዐት የባህር ዳር ከተማ ከፍተኛ ፍ/ቤት ይቀርባል ‼️

የአማራ ፋኖዎች በሁሉም አቅጣጫ ለአማራ ህዝብ ብለን በቆሰልን ፣በደማን እና አንድ ህይወታችን በሰጠን እንደ ጠላት ተቆጥረን እንገደላለን ፣እንሳደዳለን እንዲሁም ለግፍ እስር እንዳረጋለን ።ፋኖ መሸለም ሲገባው ወደ ማረሚያ ይታጎራል ።

በአማራ ህዝባዊ ሐይል(ፋኖ) መሪ ጀግናው ፋኖ አርበኛ ዘመነ ካሴ ላይም የሆነው ይህ ነው ።የተበታተነው የወጣቶች የፋኖ ስልጠና አሰባስቦ በወሎ ግንባር ፦መካነሰላም ፣አቃስታ ወዘተ በመዝመት ጠላቶቻችን ድባቅ ባደረገ ፤እነ ኤፍሬም አጥናፉን የመሰሉ በርካታ ጀግና የአማራ እንቁ ልጆቹን መስዕዋት ሆነው ጠላትን ባሳፈሩ ይህ ሁሉ ተዘንግቶ በአሁኑ ወቅት ወንድማችን በግፍ እስር ላይ ይገኛል ።ኧረ ስንቱ ምን ያልተባለነው ነገር አለ ⁉️
የተባልነውን እና የተፈጠረውን አዲስ ትርክት ፍርዱን ለአማራ ህዝብ ፣ለጊዜ እና ለታሪክ እንተወው ።

በመሆኑም ለመላው የአማራ ፋኖ በባህር ዳር አባላት ፣ለመላው የከተማችን የፋኖ ደጋፊዎችና ተቆርቋሪዎች እንዲሁም ለመላው የባህር ዳር ከተማና አካባቢው ነዋሪዎች በነገው ዕለት በባህር ዳር ከተማ ከፍተኛ ፍ/ቤት በመገኘት ለጀግናው ፋኖ አርበኛ ዘመነ ካሴ ያለንን ታላቅ አክብሮት ፣አድናቆት ፣ አብሮነት እና አጋርነት እንገልፅ ዘንድ የአማራ ፋኖ በባህር ዳር ጥሪውን ያስተላልፋል ።

የትግላችን መዳረሻ የአማራ ነፃነት ነው‼️

የአማራ ህዝብ የቁርጥ ቀን ልጅ የሆነው ፋኖ አሸናፊ አለሙ በራያ ግንባር   የጠላትን  ምሽግ ሰብሮ በክብር ተሰውቷል ።ፋኖ አሸናፊ ለአማራ ህዝብ የከፈልከውን ታላቅ መስዕዋትነት ፣የሰራኸው ታ...
28/09/2022

የአማራ ህዝብ የቁርጥ ቀን ልጅ የሆነው ፋኖ አሸናፊ አለሙ በራያ ግንባር የጠላትን ምሽግ ሰብሮ በክብር ተሰውቷል ።

ፋኖ አሸናፊ ለአማራ ህዝብ የከፈልከውን ታላቅ መስዕዋትነት ፣የሰራኸው ታላቅ ጀብዱ በትውልዱ ሲዘከር ይኖራል ።

የአማራ ፋኖ በባህር ዳር በአሸናፊ አለሙ መስዕዋትነት የተሰማንን ጥልቅ ሃዘን እየገለፅን ፤ለአማራ ህዝብ የተከፈለ ታላቅ መስዕዋትነት ነውና ለከፈልከው ታላቅ መስዕዋትነት ልባዊ ክብር አለን ። የሁሉም አማራ ትግል መዳረሻ የአማራ ነፃነት ነው ።በመሆኑም ህዝባችን ነፃነቱን እስኪጎናፀፍ ፤ህልውናው እስኪረጋገጥ ትግላችን ይቀጥላል ።የምንከፍለው እያንዳንዱ መስዕዋትነት የነፃነታችን በር ከፋች
እንዲሁም ህልውናችን ለማረጋገጥ የምንከፍለው ታላቅ መሰዕዋትነት ነው ።

ዘላለማዊ ክብርና ሞገስ ለአማራ ህዝብ ነፃነት ፥ህልውና ብለው ውድ ህይወታቸውን ለከፈሉ ሁሉም የአማራ ፋኖዎች ።

የትግላችን መዳረሻ የአማራ ነፃነት ነው‼️

አርበኛ ፋኖ ዘመነ ካሴ በተመለከተ ከአማራ ፋኖ በባህር ዳር የተሰጠ የአቋም መግለጫ‼️****የአማራ ህዝብ በትግሉ አበርክቶ ካፈራቸው ዋነኞቹ ውስጥ አንዱ ዘመነ ካሴ ነው። ዘመነ-ነት የትግል ...
27/09/2022

አርበኛ ፋኖ ዘመነ ካሴ በተመለከተ ከአማራ ፋኖ በባህር ዳር የተሰጠ የአቋም መግለጫ‼️
****

የአማራ ህዝብ በትግሉ አበርክቶ ካፈራቸው ዋነኞቹ ውስጥ አንዱ ዘመነ ካሴ ነው። ዘመነ-ነት የትግል ምልክት መሆኑ ለእኛ ለፋኖዎቹ እንዲሁም ለመላው የአማራ ወጣቶች ውሎ ያደረ ሐቅ ነው።በተጨማሪም የማንደራደርበት የትግል መሪያችን ነው ። መንግስት ከአርበኛ ፋኖ ዘመነ ካሴ ጋር የነበረን የእርቅና ሽምግልና ሂደትም ወደ ጎን በመተው የአማራን ስነ -ልቦና የባህል ስሪት በማይመጥን መልኩ በክህደት ሂደት ጀግናችንን ወደ ወኅኒ ቤት መወርወሩን እናምናለን። በመሆኑም ፋኖ አርበኛ ዘመነ ካሴን በተመለከተ የአማራ ፋኖ በባህር ዳር የሚከተሉት አቋሞችን ለማሳወቅ እንወዳለን ፦

1).ፋኖ አርበኛ ዘመነ ካሴን በተመለከተ የነበረውን የሽምግልና እና እርቅ ሂደት ስትመሩ የነበረ የሐገር ሽማግሌዎች፤ የሐይማኖት አባቶችና ፖለቲከኞች እውነታውን ለሕዝባችን በግልፅ እንድታሳውቁ ስንል እንጠይቃለን።

2).መንግስት ፋኖ አርበኛ ዘመነ ካሴ ላይ የፈጠረውን እስራት በአስቸኳይ በማቋረጥ የአማራ ህዝብ ከዋነኛ ጠላቶቹ ጋር የሚያደርገውን ትግል በድል እንዲወጣ ማድረግ አለበት። ጠላትን በስትራቴጂካልም ሆነ ታክቲካል ዉጊያ ማሸነፍ እየተቻለ የአማራን ዋነኞች በማሰር ህዝባችን ማኅበራዊ እረፍት እንዲያጣ የሚያደርጉ ሂደቶችን መንግስት በቶሎ እንዲያቆም እናሳስባለን።

3).ፋኖ አርበኛ ዘመነ ካሴን በተመለከተ የሰፈር አጀንዳን ለማናፈስ የምትሞክሩ አውደልዳዬች ከመሰል መንደሬነት አስተሳሰብ በመውጣት ለትልቅ የአማራ ህዝብ ተጋድሎ እንድትተጉ እየጠየቅን ከመሰል ሂደት ተሳትፎ በማትመለሱ ውታፍ ነቃዬች ለሚወሰዱ እርምጃዎች ኃላፊነቱ ለመውሰድ ትገደዳላቹህ።

4).ፋኖ አርበኛ ዘመነ ካሴ የትግል መምህራችን፣ የፅናት ተምሳሌታችን፣ የአይበገሬነት መንፈሳችን ነው። ከሰፈር የገዘፈ አርማችን፣ ከባህር የሰፋ ዋናችንም ነው።ለእኛ አዲሱ ትውልድ ዘመነ ካሴ የሞትንለት ወልቃይታችን ፣የምን ሞትለት መተከልችን ፣ራያችን እና ደራችን ነው ። በመሆኑም ወንድማችንን እንደ ግለሰብም ሆነ እንደ ሕዝባችን የትግል ተጋድሎ የመጠበቅ ግዴታ አለብን። ስለዚህም መላው የአማራ ፋኖ በባህርዳር አባላት እንዲሁም የፋኖን ትግል ወዳድ አማራ ወጣቶችና ህዝባችን ፋኖ አርበኛ ዘመነ ካሴን በተመለከተ ለምናደርገው ማንኛውም የትግል ጥሪ ዝግጁ እንድትሆኑ እናሳስባለን።

5).ሐገር መስራችና ወጣኒ መንግስት የሆነውን ️የአማራን ህዝብ በሰፈር፣ ሐይማኖትና ጥቅማጥቅም ሰንሰለት ለመከፋፈል የምትሰሩ ሰዎች ላይ ከስራቹህ እንድትታቀቡ እያሳሰብን፣ ዋኖቻችንን በበሬ ወለደ ስም ማጠልሸት በመክሰስ የፖለቲካና ከርስ ትርፍ ለማግኘት የምትታትሩ ሰዎች ላይ ፋኖ የመዥገር ነቃይነት ግዴታውን እንደሚወጣ ለማሳሰብ እንወዳለን።

የትግላችን መዳረሻ የአማራ ነፃነት ነው‼️

በዛሬው ዕለት የክልሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት የቀረበው ፋኖ ጣምያለው ሰንደቅ ነፃ ተብሏል‼️ፋኖ ጣምያለው ሰንደቅ በባህር ዳር ከተማ ሰኔ 20/2014 ዓ.ም በደረሰው ፍንዳታ ፣በሽብር ወንጀል እንዲሁ...
22/09/2022

በዛሬው ዕለት የክልሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት የቀረበው ፋኖ ጣምያለው ሰንደቅ ነፃ ተብሏል‼️

ፋኖ ጣምያለው ሰንደቅ በባህር ዳር ከተማ ሰኔ 20/2014 ዓ.ም በደረሰው ፍንዳታ ፣በሽብር ወንጀል እንዲሁም ህገ - መንግስታዊ ስርዓቱን በሀይል ለመናድ በሚል ወንጀል ተጠርጥሮ ከአዲስ አመት ዋዜማ ጀምሮ በግፍ እስር መቆየቱ ይታወሳል ።

በዛሬው ዕለትም በክልሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት በዋለው ችሎት ፋኖ ጣምያለው ላይ ምንም የተገኘ መረጃ ባለመኖሩ ፣ የሰውና የሰነድ ማስረጃ ስላልተገኘ የጊዜ ቀጠሮው መዝገቡ ተዘግቶ ፍ/ቤቱ በነፃ አሰናብቶታል ።

የትግላችን መዳረሻ የአማራ ነፃነት ነው‼️

ነገ ጠዋት የክልሉ ከፍተኛ  ፍ/ቤት እንገናኝ ‼️የአማራ ፋኖ በባህር ዳር የኮሚቴ አባልና የጋሸና ምሽግ ደርማሹ ጀግናው ፣ኮስታራው እና አስተዋዩ ወንድማችን ፋኖ ጣምያለው ሰንደቅ ነገ ጠዋት ...
21/09/2022

ነገ ጠዋት የክልሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት እንገናኝ ‼️

የአማራ ፋኖ በባህር ዳር የኮሚቴ አባልና የጋሸና ምሽግ ደርማሹ ጀግናው ፣ኮስታራው እና አስተዋዩ ወንድማችን ፋኖ ጣምያለው ሰንደቅ ነገ ጠዋት የክልሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት ይቀርባል ።

በሰኔ 20/2014 ዓ.ም በባህር ዳር ከተማ በደረሰው ፍንዳታ ሰበብ በግፍ ታስረው የነበሩ የአማራ ፋኖ በባህር ዳር አመራሮች በ20 ሺ ብር የዋስተና ገንዘብ ከእስር የወጡ ቢሆንም በበዓል ዋዜማ ጀምሮ ጓዳችንን ፋኖ ጣምያለው ሰንደቅን በግፍ ታስሮ ይገኛል ።የተጠረጠረበት ወንጀል በዚህ የቦንብ ፍንዳታ እንዲሁም ሕጉንና ህገ -መንግስታዊ ስርዓቱን በሀይል ለመናድ የሚል እንደሆነ ተረድተናል ።

በመሆኑም ፋኖ ጣምያለው ሰንደቅ በሃሰት ተወንጅሎ ነገ የክልሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት በጠዋቱ 3:00 ሰዐት ይቀርባል ።ሰለሆነም መላው የአማራ ፋኖ በባህር ዳር አባላት ፣የከተማችንና አካባቢው ንቁ አማራ ወጣቶች እንዲሁም የከተማችን ነዋሪዎች ነገ በክልሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት በመገኘት አጋርነታችንን እናሳይ ዘንድ ጥሪያችን እናስተላልፋለን ።

በማሰር ፥በማፈን የሚቆም የአማራ ትግል የለም‼️

አንድነት ሀይል ነው‼️ሸዋ +ወሎ+ጎጃም+ጎንደር=አንድ አማራ❗️የአማራ ፋኖ አንድነት አመቻች አባላት በዛሬው ዕለት  ከጠባቡ እስር ቤት ወደ ሰፊው ማጎሪያ ወጥተዋል ።የአማራ ፋኖ አንድነት አመ...
15/09/2022

አንድነት ሀይል ነው‼️

ሸዋ +ወሎ+ጎጃም+ጎንደር=አንድ አማራ❗️
የአማራ ፋኖ አንድነት አመቻች አባላት በዛሬው ዕለት ከጠባቡ እስር ቤት ወደ ሰፊው ማጎሪያ ወጥተዋል ።

የአማራ ፋኖ አንድነት አመቻች አባላት ከሰኔ 21/2014 ዓ.ም እሰከ ዛሬ ድረስ በግፍ እስር ቢቆዩም በዛሬው ዕለት ከጠባቡ ማጎሪያ ተለቀዋል ።የፓለቲካ ጫናውን ተቋቁመው ለህሊናቸው ላደሩ የክልሉ ዳኞች ክብርና ምስጋና ይድረሳችሁ ።

በአጠቃላይ ክብርና ምስጋና ለአማራ ፋኖ በባህር ዳር አባላት ፣ንቁ የከተማችን የአማራ ወጣቶች እንዲሁም የባህር ዳር ከተማና አካባቢው ነዋሪዎች በሙሉ ይድረሳችሁ ። ትግላችን ፍሬ አፍርቷል ።
ሸዋ ፣ወሎ ፣ጎጃም እና ጎንደር አንድ አማራ ህዝብ ፤ አንድ አማራ ፋኖ ።

የትግላችን መዳረሻ የአማራ ህዝብ ነፃነት ነው‼️

የአማራ ፋኖ አንድነት አመቻች አባላት የችሎት ውሎ‼️የአማራ ፋኖ አንድነት አመቻች አባላት  ዛሬ በአማራ ክልል ሰበር ሰሚ ችሎት የቀረቡ ሲሆን ጠዋት በነበረው ችሎት “የአማራ ፋኖ አንድነት አ...
14/09/2022

የአማራ ፋኖ አንድነት አመቻች አባላት የችሎት ውሎ‼️

የአማራ ፋኖ አንድነት አመቻች አባላት ዛሬ በአማራ ክልል ሰበር ሰሚ ችሎት የቀረቡ ሲሆን ጠዋት በነበረው ችሎት “የአማራ ፋኖ አንድነት አመቻች ፋኖዎች ወደ ፌደራል ለምን አልሄዱም?” በሚለዉ ጉዳይ ላይ የማረሚያ ቤቱ ተወካዮች የምስክርነት ቃል አዳምጧል። የምስክር ቃላቸውን ካደመጠ በኋላም ለመጨረሻ ብይን ለነገ መስከረም 5/ 2015 ዓ. ም ከቀኑ 8:00 የመጨረሻ ውሳኔ ለመስጠት ቀጠሮ ሰጧል።

በዛሬው ዕለትም በርካታ የአማራ ፋኖ በባህር ዳር አባላት ፣የከተማችን ንቁ አማራ ወጣቶች እንዲሁም የከተማችንና አካባቢው ነዋሪዎች በችሎቱ ተገኝተው ለፋኖ ወንድሞቻችን አጋርነታቸውን አሳይተዋል ።

ነገም በተጠቀሰው ሰዐት በችሎት በመገኘት ለአማራ ፋኖ ያለንን ፍፁም ወገንተኝነት ፣አብሮነት ፣አጋርነት እና አንድነት እንገልፅ ዘንድ ጥሪያችን እናስተላልፋለን ።

የትግላችን መዳረሻ የአማራ ህዝብ ነፃነት ነው‼️

የአማራ ፋኖ አንድነት አመቻች አባላት ነገ  መስከረም 3/2015 ዓ.ም ጠዋት  የክልሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት ይቀርባሉ ።14ቱ የአማራ ፋኖ አንድነት አመቻች አባላት የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሐምሌ...
12/09/2022

የአማራ ፋኖ አንድነት አመቻች አባላት ነገ መስከረም 3/2015 ዓ.ም ጠዋት የክልሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት ይቀርባሉ ።

14ቱ የአማራ ፋኖ አንድነት አመቻች አባላት የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሐምሌ 20/2014 ዓ .ም ከተከሰሱበት የሃሰት ወንጀል እያንዳንዳቸው በ25 ሺ ብር የዋስትና ገንዘብ እንዲወጡ ቢወስንም ከተያዙበት ቀን ከሰኔ 21/2014 ዓ.ም እስከ አሁን ድረስ በግፍ እስር ላይ ይገኛሉ ።

የግፍ እስረኞቹ ለክልሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት አካል ነፃ የማውጣት አቤቱታ አቅርብው ጉዳያቸው እየታየ መሆኑ የሚታወስ ነው ።ስለሆነም በነገው ዕለት መሰከረም 3/2015 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 ሰዐት ጀምሮ ጉዳያቸው በክልሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት ይታያል ።

በመሆኑም መላው የአማራ ፋኖ በባህር ዳር አባላት ፣የከተማችን ብርቱ የአማራ ወጣቶች እንዲሁም የከተማችንና አካባቢው ነዋሪዎች በነገው ዕለት እንደተለመደው በክልሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመገኘት ለፋኖ ወንድሞቻችን አማራዊ አንድነትን ፣አጋርነትን እና ህብረታችንን እናሳይ ዘንድ ጥሪያችን እናስተላልፋለን ።

የትግላችን መዳረሻ የአማራ ህዝብ ነፃነት ነው‼️

14ቱ የአማራ ፋኖ አንድነት አመቻች አባላት ለነገ ከሰዐት ተቀጠሩ‼️የአማራ ፋኖ አንድነት አመቻች አባላት ከሰኔ 21/2014 ዓ.ም ጀምሮ   በግፍ እስር በባህር ዳር ሰባታሚት ማረሚያ ቤት ይ...
08/09/2022

14ቱ የአማራ ፋኖ አንድነት አመቻች አባላት ለነገ ከሰዐት ተቀጠሩ‼️

የአማራ ፋኖ አንድነት አመቻች አባላት ከሰኔ 21/2014 ዓ.ም ጀምሮ በግፍ እስር በባህር ዳር ሰባታሚት ማረሚያ ቤት ይገኛሉ ።

የክልሉ ጠቅላይ ፍ/ቤት ሐምሌ 20/2014 ዓ.ም በዋለው ችሎት እያንዳንዳቸው በ25 ሺ ብር ዋስትና አስይዘው እንዲወጡ ቢወሰነም ፤የፌደራሉ ፍ/ቤት እኔ እፈልጋቸዋል በሚል ከአርባ (40) ቀናት በላይ በግፍ ታሰረው ይገኛሉ ።በዚህም ምክንያት አካል ነፃ የማድረግ አቤቱታ ለባህር ዳር ከፍተኛ ፍ/ቤት በዛሬው ዕለት ማለትም ጷግሜ 3/2014 ዓ.ም አቅርበው ጉዳያቸው ታይቷል ።

ከፍተኛ ፍ/ቤቱ ጉዳዩን ለሚመለከተው አካል ልኮ መልስ ለመሰጠት ነገ ማለትም ጷግሜ 4/2014 ዓ.ም ከሰዐት በኃላ ተቀጥረዋል ።

በመሆኑም በዛሬው ዕለት እንደተደረገው ፍፁም አንድነት ፣አብሮነት እና አጋርነት በነገው ዕለትም መላው የአማራ ፋኖ በባህር ዳር አባላት ፣የከተማችን ንቁ አማራ ወጣቶች እንዲሁም የከተማችንና አካባቢው ነዋሪዎች ከሰዐት በኃላ በክልሉ ፍ/ቤት በመገኘት ለፋኖዎች አጋርነታችሁን ትገልፁ ዘንድ ጥሪያችን እናስተላልፋለን ።

ፋኖነት የአማራ ህዝብ መዳኛ መንገድ ነው‼️

14ቱ የአማራ ፋኖ አንድነት አመቻች አባላት የአካል ነፃ የማውጣት አቤቱታ አቀረቡ  ‼️       (ጷግሜ 3 :2014 ዓ.ም ፍ /ቤት ይቀርባሉ )እንደሚታወቀው አስራ አራቱ (14) ከአራቱም ...
06/09/2022

14ቱ የአማራ ፋኖ አንድነት አመቻች አባላት የአካል ነፃ የማውጣት አቤቱታ አቀረቡ ‼️
(ጷግሜ 3 :2014 ዓ.ም ፍ /ቤት ይቀርባሉ )

እንደሚታወቀው አስራ አራቱ (14) ከአራቱም የአማራ ዋና ዋና ግዛቶች የተሰባሰቡ የአማራ ፋኖ አንድነት አመቻች አባላት በሰኔ 20/2014 ዓ .ም በባህርዳር ከተማ ለምክክር በተገኙበት በህግ ተይዘው ጉዳያቸውም በባህርዳር ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሲከታተሉ ቆይተው ሐምሌ 22/2014 ዓም እያንዳንዳቸው በ25ሽ ብር ዋስትና ፍርድቤቱ ቢለቃቸውም አስካሁን ማለትም ከ40 ቀናት በላይ ከህግ አግባብ ውጭ በእስር ላይ ይገኛሉ ።

ስለሆነም አካልን ነፃ የማውጣት አቤቱታ ለባህርዳር ከፍተኛ ፍርድ ቤት አቅርበው ሐሙስ ጷግሜ 3/2014 ዓ.ም ከጥዋቱ 3:00 ሰዓት ቀጠሮ ያላቸው ስለሆነ የፍርድ ቤቱን የችሎት ውሎ መከታተል የምትፈልጉ ሁሉ በቦታው ተገኝታችሁ ወገናዊ አጋርነታችሁን እና ደጋፋችሁን እንድታሳዩ በማለት ከሰባታሚት ማረሚያ ቤት ጥሪ አቅርበዋል ።

በመሆኑም በባህር ዳር ከተማ የምትገኙ የአማራ ፋኖ በባህር ዳር አባላት ፣ንቁ የከተማችን ወጣቶች እንዲሁም የከተማችንና አካባቢዋ ነዋሪዎች በተጠቀሰው ዕለት እና ሰዐት በክልሉ ጠቅላይ ፍ/ቤት በመገኘት ለወንድሞቻችን አጋርነታችንን እንገልፅ ዘንድ በትህትና ጥሪያችን እናስተላልፋለን ።

ፋኖነት የአማራ ህዝብ መዳኛ መንገድ ነው‼️

Address

Bahirdar
Bahir Dar

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የአማራ ፋኖ በባህር ዳር /Amhara Fano Bahirdar posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share