Bahirdar city prison Administration.

Bahirdar city prison Administration. Bahirdar

ስፖርት  ============+ ዓመታዊ  የህግ ታራሚዎች  የስፖርት ውድድር ተጠናቀቀ።በባህር ዳር ዩኒበርስቲ  ስፖርት አካዳሚ እና በባህር ዳር  ከተማ አስተዳደር ማረ/ቤት መመሪያ  በጋራ አ...
13/07/2023

ስፖርት ============+
ዓመታዊ የህግ ታራሚዎች የስፖርት ውድድር ተጠናቀቀ።

በባህር ዳር ዩኒበርስቲ ስፖርት አካዳሚ እና በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ማረ/ቤት መመሪያ በጋራ አዘጋጅነት ከአንድ ወር በላይ ሲካሔድ የቆየው የህግ ታራሚዎች መዝናኛ ስፖርት በደመቀ ሁኔታ በእግር ኳስ፣በመረብ ኳስ እና በገመድ ጉተታ ፍፃሜውን አግኝቷል።

የዓሳ ሃብት ልማት ፕሮጀክት በማረ/ቤት፡፡፡፡፡፡፡፡፡በአብክመ ዓሳ ሃብት ልማት ኤጀንሲ እና በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ማረ/ቤት መምሪያ በጋራ ትብብር  በ300 ሜትር ካሬ ላይ ያረፈው የዓ...
30/06/2023

የዓሳ ሃብት ልማት ፕሮጀክት በማረ/ቤት፡፡፡፡፡፡፡፡፡

በአብክመ ዓሳ ሃብት ልማት ኤጀንሲ እና በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ማረ/ቤት መምሪያ በጋራ ትብብር በ300 ሜትር ካሬ ላይ ያረፈው የዓሳ ማርቢያ ፕሮጀክት ግንባታው ተጠናቋል።

ውሃ የመሙላት ሂደቱም ተጠናቆ ፣አከባቢውን የማስዋብ ሥራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ።

23/10/2015 ዓ/ም

የህግ ታራሚዎች  ዓመታዊ  የእርስ በርስ መዝናኛ የስፖርት ውድድር ሦስተኛ ሳምንት  የ7ኛ ቀን ጨዋታ ዛሬም ቀጥሎ ውሏል።ባህር ዳር መጋቢት 25/2015 ዓ/ም በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ማ...
03/04/2023

የህግ ታራሚዎች ዓመታዊ የእርስ በርስ መዝናኛ የስፖርት ውድድር ሦስተኛ ሳምንት የ7ኛ ቀን ጨዋታ ዛሬም ቀጥሎ ውሏል።

ባህር ዳር መጋቢት 25/2015 ዓ/ም በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ማረ/ቤት መምሪያ እና በባህር ዳር ዩኒቨርስቲ ስፖርት አካዳሚ በጋራ አዘጋጅነት እየተካሔደ ያለው የህግ ታራሚዎች ዓመታዊ የእርስ በርስ መዝናኛ የስፖርት ውድድር ሦስተኛ ሳምንት ፣ሰባተኛ ቀን ጨዋታ ዛሬም ቀጥሎ ውሏል።

በዛሬው መርሃ ግብር ጨዋታ ፣ የመረብ ኳስ፣ የእግር ኳስ እና የገመድ ጉተታ ውድድሮች ተካሔደዋል።

መረብ ኳስ ዞን ሦስት, ዞን አንድን, 2 ለ 0 አሸንፏል።

እግር ኳስ ዞን አምስት, ዞን አራትን 5 ለ 4 በፔናሊት ሲያሸንፍ፣ የገመድ ጉተታ ውድድር ዞን ሁለት, ዞን አራትን 2 ለ 0 አሸናፊ በመሆን የእለቱ መርሃ ግብር ውድድር በሠላም ተጠናቋል።

ለመረጃው ህዝብ ግንኙነት።

ለፌዲራል ማሪሚያ ፖሊስ በድጋሜ ተራዝሞ የወጣ የቅጥር ማስታወቂያ:-የፌዲራል ማረ/ቤቶች ኮሚሽን በኢፊዴሪ ማረሚያ ፖሊስ ማሰልጠኛ ተቋም በአለልቱ በ2015 በጀት ዓመት 35ኛ ኮርስ መሠረታዊ የ...
03/04/2023

ለፌዲራል ማሪሚያ ፖሊስ በድጋሜ ተራዝሞ የወጣ የቅጥር ማስታወቂያ:-

የፌዲራል ማረ/ቤቶች ኮሚሽን በኢፊዴሪ ማረሚያ ፖሊስ ማሰልጠኛ ተቋም በአለልቱ በ2015 በጀት ዓመት 35ኛ ኮርስ መሠረታዊ የማረሚያ ፖሊስ አሰልጥኖ ወደ ሥራ ማስገባት ይፈልጋል።

ሥለሆነም በማስታወቂያው ላይ የተቀመጠውን መስፈርት የምታሟሉ ሥራ ፈላጊዎች በተጠቀሰው የጊዜ ሴላዳ እንድትመዘገቡ ኮሚሽኑ ያሳስባል።

፨ የመመዝገቢያ ቀን ከ15/07/2015--02/08/2015 ዓ/ም ዘወትር በሥራ ሠዓት፣

፨ የመመዝገቢያ ቦታ ባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ማረ/ቤት መምሪያ ሰባታሚት፣

ማሳሰቢያ:- ተመዝጋቢዎች የቀበሌና የፖሊስ ደብዳቤ፣የትምህርት ማስረጃ ኦርጅናል ፎቶ ኮፒ እና የታደስ መታወቂያ መያዝ ይጠበቅባቸዋል።

ለበለጠ መረጃ:- 0583203062 ይደውሉ።

ለፌዲራል  ማረሚያ ፖሊስ የቅጥር ማስታወቂያ።የፌዲራል ማረ/ቤቶች ኮሚሽን በኢፌድሪ ማረሚያ ፖሊስ ማሰልጠኛ ተቋም አለልቱ በ2015 ዓ/ም በጀት 35ኛ ኮርስ መሠረታዊ የማረሚያ ፖሊስ አሰልጥኖ ...
30/03/2023

ለፌዲራል ማረሚያ ፖሊስ የቅጥር ማስታወቂያ።

የፌዲራል ማረ/ቤቶች ኮሚሽን በኢፌድሪ ማረሚያ ፖሊስ ማሰልጠኛ ተቋም አለልቱ በ2015 ዓ/ም በጀት 35ኛ ኮርስ መሠረታዊ የማረሚያ ፖሊስ አሰልጥኖ ወደ ሥራ ለማሰማራት ይፈልጋል። ሰለሆነም የተገለፀውን መስፈርት የምታሟሉ በማስታወቂያው በተቀመጠው የጊዜ ሠሌዳ እንደትመዘገቡ ይጋብዛል።

የምዝገባ ጊዜ ከ15/07/2015 እስከ 25/07/2015 ዓ/ም ዘወትር በሥራ ሠዓት።

የምዝገባ ቦታ ባህር ዳር ከተማ አስ/ማረ/ቤት መምሪያ ሰባታሚት።

፨ የቀበሌና የፖሊስ ድጋፍ ደብዳቤ ፣የትምህርት ኦርጅናል ፎቶ ኮፒ እና የታደሰ መታወቂያ መያዝ ይጠበቅባቸዋል።

ለሥራ ፈላጊው መረጃው እንዲደርስ መረጃውን ያጋሩ/ሼር በማድርግ ይተባበሩ።

ለበለጠ መረጃ 0583203062 ይደውሉ።

የህግ ታራሚዎች አመታዊ የእርስ በርስ መዝናኛ ስፖርት ሁለተኛ ሳምነት ፣አምስተኛ ቀን ጨዋታ ዛሬም ቀጥሎ ውሏል።ባህር ዳር መጋቢት 20/2015 ዓ/ም በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ማረ/ቤት መ...
29/03/2023

የህግ ታራሚዎች አመታዊ የእርስ በርስ መዝናኛ ስፖርት ሁለተኛ ሳምነት ፣አምስተኛ ቀን ጨዋታ ዛሬም ቀጥሎ ውሏል።

ባህር ዳር መጋቢት 20/2015 ዓ/ም በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ማረ/ቤት መምሪያ እና በባህር ዳር ዩኒቨርስቲ ስፖርት አካዳሚ በጋራ አዘጋጅነት
እየተካሔደ ያለው የህግ ታራሚዎች አመታዊ የመዝናኛ ስፖርት ውድድር ሁለተኛ ሳምንት ፣አምስተኛ ቀን ጨዋታ ዛሬም ቀጥሎ ውሏል።

በዛሬው መርሃ ግብር የመረብ ኳስ፣የእግር ኳስ እና የገመድ ጉተታ መርሃ ግብሮች ተከናውነዋል።

መረብ ኳስ የፖሊስ አባላት ዞን አምስትን 2 ለ0 አሸንፈዋል።

እግር ኳስ ዞን አራት, ዞን ሶስትን 6 ለ 3 ሲያሸንፉ ፣የገመድ ጉተታ ዞን ሁለት ዞን ሶስትን በፎርፌ 2 ለባዶ አሸንፈዋል።

ለመረጃው ህዝብ ግንኙነት።

የህግ ታራሚዎች ዓመታዊ  የእርስ በርስ የስፖርት ውድድር ዛሬም ለሁለተኛ ሳምንት ቀጥሎ ውሏል።ባህር ዳር መጋቢት 18/2015 ዓ/ም  በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ማረ/ቤት መምሪያ እና በባህ...
27/03/2023

የህግ ታራሚዎች ዓመታዊ የእርስ በርስ የስፖርት ውድድር ዛሬም ለሁለተኛ ሳምንት ቀጥሎ ውሏል።

ባህር ዳር መጋቢት 18/2015 ዓ/ም በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ማረ/ቤት መምሪያ እና በባህር ዳር ዩኒቨርስቲ ስፖርት አካዳሚ በጋራ አዘጋጅነት እየተካሔደ ያለው የህግ ታራሚዎች ዓመታዊ መዝናኛ የስፖርት ውድድር ዛሬም ቀጥሎ ውሏል።

በዛሬው መርሃ ግብር የመረብ ኳስ፣ የእግር ኳስ እና የገመድ ጉተታ መርሃ ግብሮች ተከናውነዋል።

በመረብ ኳስ፣ዞንአምስት ዞን ሦስትን 2 ለ0 አሸንፏል።

የገመድ ጉተታ ዞን አንድ ዞን አራትን 2 ለ 0 አሸነፊ ሲሆኑ የእግር ኳስ ዞን ሦስት ከፖሊስ አባላት አንድ አቻ ተለያይተዋል።

በሁሉምር የውድድር መርሃ ግብርች በመልካም ሥነ ምግባር በስፖርታዊ ጨዋነት ተጠናቋል።

ለመረጃው ህዝብ ግንኙነት።

ከባህር ዳር ዩኒቨርስቲ  ቴክኖሎጂ ኢንስቲቲዊት የመጡ ዳይሬክተሮች  እና ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን የጋዜጠኞች ቡድን  በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ማረ/ቤት መምሪያ በመገኘት የህግ ታራሚዎችን...
24/03/2023

ከባህር ዳር ዩኒቨርስቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲቲዊት የመጡ ዳይሬክተሮች እና ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን የጋዜጠኞች ቡድን በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ማረ/ቤት መምሪያ በመገኘት የህግ ታራሚዎችን የሙያ ሥልጠና አይነቶች እና ለሥልጠናው የሚጠቀሙባቸውን ማሽኖች እና ግብዓቶችን በጋራ ጉብኝት አድርገዋል።
ጎብኝ ቡድኑ ይህም ቅድመ ጉብኝት ይሆናል ሲሉ ገልፀዋል። ለሙያ ሥልጠናው የሚያስፈልጉ ግብዓቶችንም ከሚመለከተው አካል ጋር በመነጋገር ድጋፍ ለማድረግ እንሞክራለን ያሉ ሲሆን በቀጣይ በጋራ የሚንሰራቸው ሥራዎች ይኖሩናል ብለዋል።

በጉብኝቱ ላይ የህግ ታራሚዎች የማረም ማነፅ ቡድን መሪ አቶ ግርማ ጥሩ ነህ እና የማረ/ቤቱ የጥበቃና መረጃ ደህንነት ቡድን መሪ የሆኑት ምክትል ክማንደር ረቂቅ መላክ ተገኝተዋል።

ለመረጃው ህዝብ ግንኙነት።

የህግ  ታራሚዎች ዓመታዊ የስፖርት ውድድር ዛሬም ለሦስተኛ  ቀን ቀጥሎ ውሏል።ባህር ዳር መጋቢት  15/2015 ዓ/ም  በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ማረ/ቤት መምሪያ እና በባህር ዳር ዩኒቨር...
24/03/2023

የህግ ታራሚዎች ዓመታዊ የስፖርት ውድድር ዛሬም ለሦስተኛ ቀን ቀጥሎ ውሏል።

ባህር ዳር መጋቢት 15/2015 ዓ/ም በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ማረ/ቤት መምሪያ እና በባህር ዳር ዩኒቨርስቲ ስፖርት አካዳሚ በጋራ አዘጋጅነት እየተከናወነ ያለው የህግ ታራሚዎች ዓመታዊ የስፖርት ውድድር ዛሬም ለሶስተኛ ቀን ሰሲካሔድ ውሏል።

በዛሬው መርሃ ግብርም የመረብ ኳስ፣የእግር ኳስ እና የገመድ ጉተታ መርሃ ግብሮች በሠላም ሲካሔዱ ውለዋል።

በሁሉም የጨዋታ ወድድሮች ላይ ከፍተኛ ስፖርታዊ ፉክክር የታየበት ሆኖ በሠላም ተጠናቋል።

ለመረጃው ህዝብ ግንኙነት።

22/03/2023
የህግ ታራሚዎች  ዓመታዊ የስፖርት ፌስቲባል  የሁለተኛ ቀን ዙር ዛሬም ቀጥሏል።ባህር ዳር መጋቢት 13/2015 ዓ//ም  በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ማረ/ቤት መምሪያ እና በባህር ዳር ዩኒቨ...
22/03/2023

የህግ ታራሚዎች ዓመታዊ የስፖርት ፌስቲባል የሁለተኛ ቀን ዙር ዛሬም ቀጥሏል።

ባህር ዳር መጋቢት 13/2015 ዓ//ም በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ማረ/ቤት መምሪያ እና በባህር ዳር ዩኒቨርስቲ ስፖርርት አካዳሚ በጋራ አዘጋጅነት እየተካሔደ ያለው የህግ ታራሚዎች ዓመታዊ የስፖርት ፌስቲቫል ዛሬም ለሁለተኛ ቀን ተጠናክሮ ቀጥሏል።

በዛሬው መርሃ ግብር መረብ ኳስ ፣እግር ኳስ እና የገመድ ጉተታ መርሃ ግብሮች እየተከናወኑ ይገኛሉ።

ለመረጃው ህዝብ ግንኙነት።

በማረ /ቤቱ የህግ ታራሚዎች ዓመታዊ የስፖርት ፌስቲቫል ውድድር መካሔድ ጀምሯል።ባህር ዳር መጋቢት 11/2015 ዓ/ም በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ማረ/ቤት መምሪያ እና በባህር ዳር ዩኒቨርስ...
20/03/2023

በማረ /ቤቱ የህግ ታራሚዎች ዓመታዊ የስፖርት ፌስቲቫል ውድድር መካሔድ ጀምሯል።

ባህር ዳር መጋቢት 11/2015 ዓ/ም በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ማረ/ቤት መምሪያ እና በባህር ዳር ዩኒቨርስቲ ስፖርት አካዳሚ በጋራ ትብር በየዓመቱ የሚካሔደው የህግ ታራሚዎች ስፖርታዊ ፌስቲቫል ውድድር ዛሬ በማረ/ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ መካሔድ ጀምሯል።

በዛሬው መክፈችያ መርሃ ግብር የመረብ ኳስ፣የእግር ኳስ እና የገመድ ጉተታ ውድድሮች ተካሔድዋል።

በመክፈችያው መርሃ ግብር በተደረገው የመረብ ኳስ ጨዋታ ከባህር ዳር ዩኒቨርስቲ ከቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ለወዳጀነት ተጋብዞ የተጫወተው ቡድን በህግ ታራሚዎች በድን 2 ለ1 ተሸንፏል።

በስፖርት ፌስቲቫሉ በርካታ የባህር ዳር ዩኒቨርስቲ ማህበረሰብና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታድመዋል።

የፌስቲቫሉን ውድድር የማረ/ቤቱ ሃላፊ ኮማንደር አብርሃም ተስፋ በመክፈችያ ንግግር አስጀምረውታል።

ለመረጃው ህዝብ ግንኙነት።

Address

Bahirdar City Administration Prison
Bahir Dar
PR717290

Telephone

+251994520994

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Bahirdar city prison Administration. posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share