09/01/2024
በ97 ቢሊየን ብር ወጪ 61 የአስፓልት መንገድ ፕሮጀክቶች እየተሠሩ ነው
በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች የሚከናወኑ የመንገድ ሥራ ፕሮጀክቶችን አፈጻጸም የተመለከተ ግምገማ እና ውይይት የክልሉ መንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች በተገኙበት በባሕር ዳር ከተማ እየተካሄደ ነው።
ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደን ጨምሮ የአማራ ክልል ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች እና የኢትዮጵያ መንገዶች አሥተዳደር አመራሮች የውይይቱ ተሳታፊዎች ናቸው።
• ባለስልጣኑ የጎንጂ-ቆለላን ጨምሮ አራት የመንገድ ፕሮጀክቶችን ውል ተፈራረመ፡፡
• “በክልሉ ከ4ሺህ ኪሎ ሜትር በላይ የመንገድ ጥገና ለማካሄድ ጥረት እየተደረገ ነው”…
• የተጀመሩ የመንገድ ፕሮጀክቶች ተጠናቅቀው ለአገልግሎት ክፍት እንዲሆኑ ትኩረት ሠጥቶ…
• "በ2015 በጀት ዓመት ከ2 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ 541 ፕሮጀክቶች…
የኢትዮጵያ መንገዶች አሥተዳደር በአማራ ክልል በአጠቃላይ 61 የአስፓልት መንገድ ፕሮጀክቶችን እየሠራ እንደሚገኝ ተገልጿል። የመንገዶቹ አጠቃላይ ድምር ርዝማኔ 3 ሺህ 658 ኪሎ ሜትር ነው።
የመንገድ ግንባታዎቹ በ97 ቢሊዮን ብር ወጪ የሚገነቡ ስለመሆናቸው የኢትዮጵያ መንገዶች አሥተዳደር ገልጿል።
በአዲስ ከሚሠሩ መንገዶች በተጨማሪ 3 ሺህ 664 ኪሎ ሜትር ነባር መንገዶችም እየተጠገኑ መኾኑ ተጠቁሟል። ከ2 ቢሊዮን 166 ሚሊዮን 529 ሺህ በላይ ብር ለመንገዶች ጥገና ተመድቦ እየተሠራ ስለመሆኑም ተነግሯል።
ውይይቱ በክልሉ የሚከናወኑ የመንገድ ፕሮጀክቶችን በመደገፍ ወደ ጠንካራ አፈጻጸም ለማስገባት እና የሕዝቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ያለመ ስለመሆኑ ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ ተናግረዋል።
(አሚኮ)