Sidama Development Association-SDA

Sidama Development Association-SDA Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Sidama Development Association-SDA, Community Service, Bahil-Adarash sub-city by the Hawassa post office, Awassa.

Sidama Development Association (SDA) is an independent, non-political, non-religious, not-for-profit, non-governmental member-based organization established in July 1993 Registered and licensed by FDRE Civil Society Organizations Authority.

JSI ኢትዮጵያ ከሲዳማ ልማት ማህበር ጋር በመቀናጅት እያከናወነ ለሚገኛቸው የጤና ፕሮጀክት ከጤና ጣቢያ ወደ ጤና ኬላ ግብዓት ለማድረስ እና ድጋፋዊ ክትትል ለማድረግ የሚረዱ ሁለት ሞተር ሳይ...
16/05/2026

JSI ኢትዮጵያ ከሲዳማ ልማት ማህበር ጋር በመቀናጅት እያከናወነ ለሚገኛቸው የጤና ፕሮጀክት ከጤና ጣቢያ ወደ ጤና ኬላ ግብዓት ለማድረስ እና ድጋፋዊ ክትትል ለማድረግ የሚረዱ ሁለት ሞተር ሳይክሎችን ለክልሉ ጤና ቢሮ አስረከበ::
***""""""""""""""""******
የሲዳማ ልማት ማህበር ኮሚኒኬሽን
ግንቦት 8/2018 ሀዋሳ

ድጋፉ የተደረገው በወንዶገነት ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ሥር ለሚገኙ ሁለት ጤና አጠባበቅ ጣቢያዎች (አሩማ እና ባቦ ጮሮሮ ) በጤና አገልግሎት አሰጣጥ ማሻሻል ፕሮጀክት (strengthen service delivery project (SSD) ነው።

በርክክቡ ወቅት የሲዳማ ብ/ክ/መንግሥት ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ በላይነህ በቀለ እና የJSI የሲዳማ ክልል IPHCSD እና SSD አስተባባሪ ወ/ሮ ምንትዋብ ዘነበ፣ የሲዳማ ልማት ማህበር ም/ስራስካጅ አቶ ያለዉ ተከስተ እንዲሁም የወረዳው ጤና ጽ/ቤት የማኔጅመነት አባላት እና የሁለቱም ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

በርክብክቡ ወቅት የሲዳማ ብ/ክ/መንግሥት ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ በላይነህ በቀለ ባስተላለፉት መልዕክት JSI ከሲዳማ ልማት ማህበር ጋር በመቀናጅት በክልሉ በስድስት ወረዳዎች ላይ የእናቶችን፤ የህጻናትን እና የጨቅላ ህጻናትን ሞትና ህመም ለመቀነስ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እየራ ከመሆኑም በላይ የግብዓት መቆራረጥን ለማስለጥ በሚደረገውን ጥረት ለመደገፍ ሁለት የሞተር ሳይክሎች ድጋፍ በጣም አስፈላጊ መሆናቸዉን ገልጽዉ፣ ግብዐትን ከጤና ጣብያ ወደ ጤና ኬላ ግብዕት ከማድረስ በተጨማሪ ከጤና ኬላ ወደ ክትባት ጣብያዎቻችን እና የዉሎ ገብ ስራዎችን ለማሳለጥ ከፍተኛ አሰተዋዖ እንደሚኖራቸዉ በመግለጽ በአግባቡና በከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲሰራ መመርያ ሰተዋል፡፡
የJSI የክልሉ ኘሮግራም አስተባባሪ ወ/ሮ ምንትዋብ ዘነበ በበኩላቸዉ JSI በክልሉ ዉስጥ ብዙ ተግባራትን እየስራ መሆኑን ገልጸዉ በተለይም የእናቶችን፤ የህጻናትን እና የጨቅላ ህጻናትን ሞትና ህመም ለመቀነስ፤ በጤና ኬላ አእና በማህበረስብ ውስጥ አግልግሎቱን ተድራሽ ልማደረግ ከፍተኛ አሰተዋጾ እንዳለዉ ገልጸዋል፡፡ በተጨማርም የልማት ማህበሩ ም/ሥራ አሰፈፃሚ አቶ ያለዉ ተከስተ የልማት ማህበሩ ከJSI ጋር ለመተግበር እንዲያመች አንድ በክልል ደረጃ የፕሮጅከቶች አሰተባባሪ እና አምስት ወረዳ ኦፊሰሮችን በመቅጠር ስራዉን እየሰራ ሲሆን የዛሬዉ ድጋፍ ግባትን ለማሳለጥ ከJSI የተገኘ ተጨማር ድጋፍ መሆኑን በመግለፅ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደረጉ መሰል ተግባራትን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡

!
!

~Follow us on~
🌎website:https://sida.org.et/
🌎 telegram:https://t.me/+l9A1rzxwsCgzMTQ0
🌎 YouTube:https://www.youtube.com/
🌎 TikTok:-https://www.tiktok.com/?_t=8n5NdDvxjvh&_r=10

የትውውቅ፣ የፕሮጀክት ማስጀመሪያ እና ለዲጅታል የግብርና መረጃ ማሳለጫ የሚያገለግል 31 የዘመናዊ ስልኮች ከአመታዊ የኢንተርኔትና የመልዕክት ጥቅል ጋር  የማስራጨት እንዲሁም የግንዛቤ ማስጨበ...
13/05/2026

የትውውቅ፣ የፕሮጀክት ማስጀመሪያ እና ለዲጅታል የግብርና መረጃ ማሳለጫ የሚያገለግል 31 የዘመናዊ ስልኮች ከአመታዊ የኢንተርኔትና የመልዕክት ጥቅል ጋር የማስራጨት እንዲሁም የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ-ግብር ተካሄደ::
**********""""""""""""""**********
የሲዳማ ልማት ማህበር ኮሚኒኬሽን
ግንቦት 5/2018 ይርጋአለም

የሲዳማ ልማት ማህበር ከሲ/ብ/ክ/መንግሥት ግብርና ቢሮ ISVCD ፕሮጀክት ጋር የእስትራቴጅክ አጋርነት ሥምምነት መነሻ በማድረግ በልማት ማህበሩ በተቋቋመው AgriCONNECT Hub ሥር የበለፀገውን AgriDiko ዌብሳይት ለተጠቃሚው ህብረተሰብ ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግ እና ለሚመለከታቸው አካላት ግንዛቤ ለመፍጠርና ፕሮጀክቱን ለማስተዋወቅ ያለመ መርሃ-ግብር ነው።

በመድረኩ ተገኝትው መልዕክት በማስተላለፍ ስልጠናውን ያስጀመሩት የልማት ማህበሩ ም/ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ያለው ተከስተ በመልዕክታቸው ልማት ማህበሩ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ በግብርናው ዘርፉ በርካታ ሥራዎችን እየሠራ መቆየቱን ገልፀው የዛሬው መርሃ-ግብር ወቅቱ የዲጅታላይዜሽን መሆኑን በመረዳት በግብርናው መስክ የተሰማሩ አካላት ወቅታዊ የግብርና ገበያ መረጃን ስትክክለኛ ምንጮች እንዲያገኙ በማስቻል በዘርፉ ከመረጃ እጥረት የተነሳ የሚያጋጥሙ ዘርፉ ብዙ ችግሮችን ለመቅረፍ የሚያስል ሥርዓት በመዘርጋት የገበያ መረጃ ሰብሳቢዎችን በመቅጠርና በማስልጣን እንዲሁም መረጃ ለመሰብሰብ የሚረዳ Smart Phone በመስጠት በ10 ወረዳዎች የሥራ ስምሪት ተሰቷል::
በዛሬው እለት ሁሉም የሚመለከተው አካል በተገኘበት 2ዐ ለሚሆኑ መሰረታዊ የህብረት ሥራ ማህበራት የመረጃ ግብይቶች እንዲመግቡ የሚያስችላቸውን Smart Phone በልማት ማህበሩ የሚበረከትላቸው ሲሆን ለወደፊት በቅንጅት ለመስራት የሚያችልም ነው ብለዋል::
ከሲብ/ክ/መንግሥት እርሻና ተፈ/ሀ/ል/ቢሮ ከአካታችና ቀጣይ የግብርና እሴት ሰንሰለት ልማት /ISVCD/ ፕሮጀክት ማኔጀር አቶ ምትኬ ሙሉጌታ ለተሳታፊዎች በአካታችና ቀጣይ የግብርና እሴት ሰንሰለት ልማት /Inclusive and Sustainable Value chain Development/ ፕሮጀክት እና በግብርና ገበያ መረጃ ላይ ሰፊ ግንዛቤ የፈጠሩ ሲሆን የግብርናውን ዘርፍ ለማዘመን በሚደረገው ጥረት ላይ ግብርናን ከተለመደው አምርቶ ገበያ ከሚፈለግበት አስቀድሞ ወስኖ እና ሸጦ ወደማምረት በዚህም አርሶአደሮችም ሆኑ የእሴት ሰንሰለት ተዋናዮች ሁሉ በተገቢው ተጠቃሚ ሊሆኑ ስለሚችሉበት እና በቅንጅት መስራት በሚችሉበት ሁኔታ ላይ ግንዛቤ አስጨብጠዋል::

የሲዳማ ልማት ማህበሩ የዕቅድ ክትትል ዲፓርትመንት ኃላፊ አቶ ግሩም ሹኔቴ ልማት ማህበሩ እያከናወነ ስለሚገኘው አጠቃላይ እንቅስቃሴ እና ከመርሃ- ግብሩ ተሳታፊዎች አጠቃላይ የፕሮጀክቱ አላማ እና የሚጠበቁ ውጤቶች ላይ ትኩረት ያደረገ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሰጥተዋል።

የልማት ማህበሩ የIG Department ኃላፊ በሌላ በኩል በሲዳማ ልማት ማህበር በተቋቋመው AgriCONNECT Hub ሥር የበለፀገውን AgriDiko ዌብሳይት ላይ ግብአት ማስገባት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ስልጠና የሰጡ ሲሆን ድህረ ገፁ ዘመኑን የዋጀና የግብርና መረጃ ሥርዓትን የሚያዘምን እንደሆነ ገልፀው የሥርዓቱን ተደራሸነት ለማስፋት ከተጀመሩ ሥራዎች ውስጥ አንዱ የሆነ እንቅስቃሴ መሆኑን ገልፀዋል።

በመጨረሻም የውይይት ከተሳታፊዎች ሀሳብ፤ አስተያየት እና ጥያቄዎች ተነስተው ከመድረኩ ምላሽ በተሰጠ በኋላ ለመሰረታዊ ህብረት ሥራ ማህበራት እና ለመረጃ ስብሳቢ ኦፊሰሮች smart phone With Annual internate packege በመስጠት መርሃ-ግብሩ ተጠናቋል::

!
!


~Follow us on~
🌎website:https://sida.org.et/
🌎 telegram:https://t.me/+l9A1rzxwsCgzMTQ0
🌎 YouTube:https://www.youtube.com/
🌎 TikTok:-https://www.tiktok.com/?_t=8n5NdDvxjvh&_r=10

በጤናው ዘርፍ እየተተገበረ የሚገኘውን ፕሮጀክት አፈጻጸም ግምገማ የክልሉ ጤና ቢሮ እና ገንዘብ ቢሮ በተገኙበት ተካሂዷል። የሲዳማ ልማት ማህበር ኮሚኒኬሽንግንቦት 4/2018 ዓ.ም ሀዋሳ ፕሮጀ...
12/05/2026

በጤናው ዘርፍ እየተተገበረ የሚገኘውን ፕሮጀክት አፈጻጸም ግምገማ የክልሉ ጤና ቢሮ እና ገንዘብ ቢሮ በተገኙበት ተካሂዷል።

የሲዳማ ልማት ማህበር ኮሚኒኬሽን
ግንቦት 4/2018 ዓ.ም ሀዋሳ

ፕሮጀክቱ በዋናነት የሲዳማ ልማት ማህበር JSI ከተባለ መንግስታዊ ካልሆነ ድርጅት ጋር በመተባበር በስድስት ወረዳዎች በሁለት የተለያዩ ፕሮጀክቶች ማለትም የመጀመሪያ ደረጃ ጤና አገልግሎት ማሻሻያ (Improve primary health care service delivery project, IPHCSD) እና የጤና አገልግሎት አሰጣጥን ማጎልበት (strengthen service delivery, SSD) ላይ የሰራ የቆየ ሲሆን የልማት ማህበሩ የሁለቱም ፕሮጀክቶች የክልል አስተባባሪ አቶ ተረፈ ሙሉጌታ በፕሮጀክቱ በሲዳማ ክልል ባለፉት ሶስት አመታትና ከዚያ በላይ የተከናወኑ ጠንካራ አፈፃፀሞችን በማጣቀስ እስካለፈው አመት 2025 ድረስ የተከናዎኑ ሥራዎችን በዝርዝር አቅርበዋል፡፡

በመድረኩ የሲዳማ ብ/ክ/መንግሥት ጤና ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ በላይነህ በቀለ፣ የቢሮው ማኔጅመንት አባላት እና ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት እንዲሁም ከክልሉ ገንዘብ ቢሮ የሲቪል ማህበረሰብ ደርጅቶች ዴስክ ኃላፊ አቶ ሳሙአል ተካ ብሎም የልማት ማህበሩ ማኔጅመንት አባላት እና የሁሉም ወረዳ የፕሮጀክት ኦፊሰሮች ተገኝተዋል፡፡
የግምገማ መድረኩን በእንኳን ደህና መጣችሁ መልከዕክት ያስጀመሩት የልማት ማህበሩ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ወይንሸት መንገሻ በመልዕክታቸው ልማት ማህበሩ በአምስት ቴማቲክ አቅጣጫዎች እያከናወናቸው ከሚገኙ ሥራዎች ውስጥ አንዱ የጤናው ዘርፍ ሲሆን JSI ከጌትስ ፋውንዴሽን ጋር በሀገር አቀፍ ደረጃ በገባው የፕሮጀክት ስምምነት መነሻነት በሲዳማ ክልል በIPHCSD ፕሮጀክት በበንሳ ወረዳ ተጀምሮ የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ በመቻሉ SSD ፕሮጀክት ተጨምሮ በሁለቱም ፕሮጀክቶች በስድስት ወረዳዎች ውስጥ የሚታይ ለውጥ ማምጣት የተቻለ ሲሆን የተመዘገበውን ውጤት ተከትሎ C-RMNCH የተባለ ሶስተኛ ፕሮጀክት በተለዩ ወረዳዎች ለመጀመር ዝግጅቱ ተጠናቆ ስምምነት መፈራረም ብቻ ቀርቶናል ብለው የዛሬው የግምገማ መድረክ የሥራው ባለቤቶች ባሉበት ማድረግ ያስፈለገበት ምክንያት የታዩ ጠንካራ አፈፃፀሞችን በማስቀጠል ክፍተቶችን በመለየት ለወደፊት በተጠናከረ መልኩ ለማስቀጠል ነው ብለዋል፡፡

በመጨረሻም የውይይት መድረኩን የሲዳማ ብ/ክ/መንግሥት ጤና ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ በላይነህ በቀለ እና የልማት ማህበሩ ዋና ሥራ አስፈፃሚ እየመሩ ከተሳታፊዎች ሀሳብ፤ አስተያየት እና ጥያቄዎች ተነስተው ከመድረኩ ምላሽና ቀጣይ አቅጣጫ በማስቀመጥ የግምገማ መድረኩ ተጠናቋል፡፡
!
!


~Follow us on~
🌎website:https://sida.org.et/
🌎 telegram:https://t.me/+l9A1rzxwsCgzMTQ0
🌎 YouTube:https://www.youtube.com/
🌎 TikTok:-https://www.tiktok.com/?_t=8n5NdDvxjvh&_r=10

11/05/2026

Check out SDA’s video.

08/05/2026
ለዲጂታል የግብርና ገበያ መረጃ ስብሳቢ ሠራተኞች ስልጣና ተሰጠ::              ***********""""""""""""""""************የሲዳማ ልማት ማህበር  ኮሚኒኬሽን ሚያዚያ...
28/04/2026

ለዲጂታል የግብርና ገበያ መረጃ ስብሳቢ ሠራተኞች ስልጣና ተሰጠ::
***********""""""""""""""""************
የሲዳማ ልማት ማህበር ኮሚኒኬሽን ሚያዚያ 20/2018 ዓ.ም ሀዋሳ

በሲዳማ ልማት ማህበር በተቋቋመው AgriCONNECT Hub ሥር የበለፀገውን AgriDiko ዌብሳይት ማሳለጥ ለማሳቻል ከሲብ/ክ/መንግሥት ግብርና ቢሮ ከISVCD ፕሮጀክት ጋር የእስትራቴጅክ አጋርነት ሥምምነት መደረጉ ይታወሳል።

በመድረኩ መልዕክት በማስተላለፍ ስልጠናውን ያስጀመሩት የልማት ማህበሩ ም/ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ያለው ተከስተ በመልዕክታቸው በዛሬው እለት መሰጠት የጀመረው ሥልጠና የዚሁ ስምምነት አካል መሆኑን ገልፀው ሰልጣኞች ከስልጠናው በኋላ ወደ መጡበት ወረዳ ተመልሰው ሥራቸው በሚሰሩበት ጊዜ የሚሰበስቡት መረጃ ለማህበረሰባችን ትልቅ ሚና ያለው መሆኑን በመረዳት ትክክለኛ መረጃ ከትክክለኛ ምንጭ በመሰብሰብ የሚጠበቅብንን ሚና ልንወጣ ይገባል ብለው ሥራቸሁን በሚገባ ተረድታችሁ መስራት የሚያስችላችሁን ስልጠና ለመስጠት ታሰቦ የተዘጋጀ በመሆኑ በንቃት መከታተል አለባችሁ ብለዋል።

ከሲብ/ክ/መንግሥት እርሻና ተፈ/ሀ/ል/ቢሮ ከአካታችና ቀጣይ የግብርና እሴት ሰንሰለት ልማት /ISVCD/ ፕሮጀክት ማኔጀር አቶ ምትኬ ሙሉጌታ ለሰልጣኞች በአካታችና ቀጣይ የግብርና እሴት ሰንሰለት ልማት /Inclusive and Sustainable Value chain Development/ ፕሮጀክት እና በግብርና ገበያ መረጃ ላይ ሰፊ ስልጠና የሰጡ ሲሆን ለአፊሴሮቹ በታሪክ አጋጣሚ የግብርናውን ዘርፍ ለማዘመን በሚደረገው ጥረት ላይ ግብርናን ከተለመደው አምርቶ ገበያ ከሚፈለግበት አስቀድሞ ወስኖ እና ሸጦ ወደማምረት በዚህም አርሶአደሮችም ሆኑ የእሴት ሰንሰለት ተዋናዮች ሁሉ በተገቢው ተጠቃሚ ሊሆኑ ስለሚችሉበት ሁኔታ ላይ ግንዛቤ አስጨብጠዋል::

በተጨማሪም ከኢትዮጵያ ምግብና እርሻ ድርጅት/FAO -Ethiopia/የሲዳማ እና ደቡብ ኢትዮጵያ ክልሎች የISVCD ፕሮጀክት ቴክኒካል አማካሪ አቶ ኪዳኔ ገ/ፃዲቅ በስልጠናው ተገኝተው ልማት ማህበሩ በአጭር ጊዜ ውስጥ ፕሮጀክቱን ተባባራዊ ለማድረግ የሄደበት ርቀት አሰደናቂ በመሆኑን በመግለጽ ፕሮጀክቱን በተመለስተ አጭር ገለፃ ካደረጉ በኋላ ይህን የሥራ ዕድል እንደቀላል እንዳታዩት በማለት ልምዳቸውን በማጋራት ሠራተኞቹን አበረታተዋል::

የዕቅድ ክትትል ዲፓርትመንት ኃላፊ አቶ ግሩም ሹኔቴ ልማት ማህበሩ እያከናወነ ስለሚገኘው አጠቃላይ እንቅስቃሴ እና ከሰጣኞች አጠቃላይ የፕሮጀክቱ አላማ እና የሚጠበቁ ውጤቶች ላይ ትኩረት ያደረገ ስልጠና ሰጥተዋል።

የIG Department ኃላፊ አቶ አመኑ አርጎ በሌላ በኩል በልማት ማህበሩ በተቋቋመው AgriCONNECT Hub ሥር የበለፀገውን AgriDiko ዌብሳይት ላይ ግብአት ማስገባት በሚቻልበት ሁጌታ ላይ ስልጠና የሰጡ ሲሆን ድህረ ገፁ ዘመኑን የዋጀና የግብርና መረጃ ሥርዓትን የሚያዘምን እንደሆነ ገልፀው የሥርዓቱን ተደራሸነት ለማስፋት ከተጀመሩ ሥራዎች ውስጥ አንዱ የሆነ እንቅስቃሴ መሆኑን ገልፀዋል።

በመጨረሻም አቶ ሳምባቶ ካያሞ ሠራተኞቹ መረጃውን በሚሰበስቡበት፤ በሚተነትኑበት እና ሪፖርት በሚያደርጉት ወቅት ስለሚጠቀሙባቸው ቱሎች ስፋ ያለ ስልጠና ሰጥተዋል::

!
!


~Follow us on~
🌎website:https://sida.org.et/
🌎 telegram:https://t.me/+l9A1rzxwsCgzMTQ0
🌎 YouTube:https://www.youtube.com/
🌎 TikTok:-https://www.tiktok.com/?_t=8n5NdDvxjvh&_r=1

የሲዳማ ልማት ማህበር በጤናው ዘርፍ በስድስት  ወረዳዎች  እየተገበረ የሚገውን ፕሮጀክት አፈጻጸም ግምገማ ተደረገ። የሲዳማ ልማት ማህበር ኮሚኒኬሽንሚያዝያ 17/2018 ዓ.ም ሀዋሳፕሮጀክቱ በ...
25/04/2026

የሲዳማ ልማት ማህበር በጤናው ዘርፍ በስድስት ወረዳዎች እየተገበረ የሚገውን ፕሮጀክት አፈጻጸም ግምገማ ተደረገ።

የሲዳማ ልማት ማህበር ኮሚኒኬሽን
ሚያዝያ 17/2018 ዓ.ም ሀዋሳ

ፕሮጀክቱ በዋናነት የሲዳማ ልማት ማህበር JSI ከተባለ መንግስታዊ ካልሆነ ድርጅት ጋር በመተባበር እየተገበረ የሚገኘው የጤና ፕሮጀክ, (Improve primary health care service delivery project, IPHCSD) ወይም የመጀመሪያ ደረጃ አገልግሎት ማሻሻያ ፕሮጅክት ፤ የጤና አገልግሎት አሰጣጥን ማጎልበት (strengthen service delivery, SSD) ላይ እየሰራ የቆየ ሲሆን በመድረኩ የሁሉም ወረዳ የሥራ አፈፃፀም ሪፖርት በቀረበበት ወቅት የተከናወኑ አፈፃፀሞች በጥንካሬ እና በክፍተት በመለየት ጠንካራ አፈፃፀም የታየባቸው ጉዳዮችን በማስፋት ክፍተቶችን ደግሞ በማረም በቀጣይ ይበልጥ ውጤታማ መሆን በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ጠንካራ እና ሰፋ ያለ ውይይት የተደረገ ከመሆኑም በላይ ምርጥ ተሞክሮዎች ቀርበው የልምድ ልውውጥ ተደርጎበታል።

የልማት ማህበሩ ም/ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ያለው ተከስተ የሥራ አፈፃፀም ግምገማውን ባስጀመሩበት ወቅት ልማት ማህበሩ Improve primary health care service delivery (IPHCSD) እና የአገልግሎት አቅርቦትን ማጠናከር (SSD) በፕሮጀክቶች ትግበራ በአመቱ ውስጥ የተከናወኑ ሥራዎችን በየሩብ አመቱ በአካል ክትትል እያደረገ እና ሳምንታዊ እንዲሁ ወርሃዊ የቨርቿል ስብሰባዎችን በማድረግ ጠንካራ አፈፃፀም እንዲኖርና ህብረተሰቡ ተጠቃሚ እንዲሆን ማድረግ የተቻለበት ነው ብለዋል፡፡
በተጨማርም የፕሮጀክቱን የፋይናንስ አፈፃፀም፣ በተመለከተ የሲዳማ ልማት ማህበር ፋይናስና አስተዳደር ዲፓርትመንት ኃላፊ አቶ መሳሪያ ዲንጋማ በዝርዝር ቀርቦ ዉይይት ተደርጎል፡፡

በመድረኩ የልማት ማህበሩ ማኔጅመንት ፣ የJSI የሲዳማ ክልል አስተባባሪ ወ/ሮ ምንትዋብ ዘነበ እንዲሁም የሁሉም ወረዳ የፕሮጀክት ኦፊሰሮ የተገኙ ሲሆን ወ/ሮ ምንትዋብ በበኩላቸው የፕሮጀክቱን አፈፃፀም በቅርበት ክትትል እየተደረገ በአመቱ ጥሩ አፈፃፀም ማስመዝገብ ተችሏል ብለው ከተሰበሰቡ መረጃዎች በመነሳት ሊታረሙ የሚገባቸው ነጠቦችን አስተው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡

በመጨረሻም በሁለቱም ፕሮጀክቶች በተለዩ ጉዳዮች ላይ የቡድን ሥራ በመስራት ቀጣይ አቅጣጫዎችን በመስጠት የግምገማ መድረኩ ተጠናቋል።

!
!


~Follow us on~
🌎website:https://sida.org.et/
🌎 telegram:https://t.me/+l9A1rzxwsCgzMTQ0
🌎 YouTube:https://www.youtube.com/
🌎 TikTok:-https://www.tiktok.com/?_t=8n5NdDvxjvh&_r=1

ክርስቲያን በጎ አድራጎት እና ልማት ማህበራት ህብረት ደቡብ ክልላዊ ማስተባበሪያ በሲዳማ ልማት ማህበር አመቻችነት  ለ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ መሳካት የሲቪል ማህበረሰብ ደርጅቶች ሚና በሚል ርዕስ...
21/04/2026

ክርስቲያን በጎ አድራጎት እና ልማት ማህበራት ህብረት ደቡብ ክልላዊ ማስተባበሪያ በሲዳማ ልማት ማህበር አመቻችነት ለ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ መሳካት የሲቪል ማህበረሰብ ደርጅቶች ሚና በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ሰልጠና ተሰጠ፡፡
**********""""""""""""************
የሲዳማ ልማት ማህበር ኮሚኒኬሽን
ሚያዝያ 13/2018 ዓ.ም ሀዋሳ

ስልጠናው ለህብረቱ አባል የሲቪል ማህብረሰብ ድርጅቶች የተሰጠ ሲሆን በስልጠናው ላይ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የሲዳማ ብሆራዊ ክልላዊ መንግስት ፋይናንስ ቢሮ የሲቪል ማህበረሰብ ደርጅቶች ዴስክ ኃላፊ አቶ ሳሙአል ተካ፣ የሲቪል ማህበርሰብ ድርጅቶች በክልሉ የተለያዩ የልማትና በጎ ተግባራት ሥራዎች ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከቱ እንድሚገኙ ገልፀው፣ ሀገራዊ ምርጫው ሰላማዊ ታዓማኒነት ያለዉ እንዲሆን ለዜጎች ግንዛቤ በመፍጠር በማንቃት ረግድ የሚጠበቅባቸው ሚና ከፍተኛ መሆኑን መንግስት እንድሚያምን አውቀዉ ተሳትፎ ሊያደርጉ ይገባል ብለዋል።
የክርስቲያን በጎ አድራጎት እና ልማት ማህበራት ህብረት (CCRDA) የቅንጅትና አጋርነት ዲፓርትመንት ኃላፊ ወ/ሮ ራሔል ሕለውተወርቅ አክልዉም የሲቪል ማህበረሰብ ደርጅቶች፣ ምርጫ የዲሞክራሲ መሰረት የሚጥል መሳሪያ በመሆኑ ሰላማዊ ፤ ታአማንነት ያለዉ እንዲሆን ሚናቸዉ ከፍተኛ በመሆኑ መራጭ ዜጎችን በማስተማር ፤ በማንቃት፤ በታዛዊነት ሂደት ሚናቸው የላቀ በመሆኑ በአዋጁ የተፈቀደላቸዉ ገደብ አውቀዉ ሰላማዊ ምርጫ እንዲካሄድ ለማስቻልና የበኩላቸውን እንዲወጡ ታስቦ የተዘጋጀ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መሆኑን ገልጸዋል።

በመጨረሻም የስልጠናው ተሳታፊዎች ሲቪል ማህበረሰብ ደርጅቶች ሚናቸውን በሚገባ እንዲያውቁና ለ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ሰፊ ግንዛቤ ያገኙበት መሆኑን ገልጸዋል።

!
!


~Follow us on~
🌎website:https://sida.org.et/
🌎 telegram:https://t.me/+l9A1rzxwsCgzMTQ0
🌎 YouTube:https://www.youtube.com/
🌎 TikTok:-https://www.tiktok.com/?_t=8n5NdDvxjvh&_r=1

Address

Bahil-Adarash Sub-city By The Hawassa Post Office
Awassa

Opening Hours

Monday 08:00 - 17:00
Tuesday 08:00 - 17:00
Wednesday 08:00 - 17:00
Thursday 08:00 - 17:00
Friday 08:00 - 17:00

Telephone

+251916586048

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Sidama Development Association-SDA posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Sidama Development Association-SDA:

Share