16/05/2026
JSI ኢትዮጵያ ከሲዳማ ልማት ማህበር ጋር በመቀናጅት እያከናወነ ለሚገኛቸው የጤና ፕሮጀክት ከጤና ጣቢያ ወደ ጤና ኬላ ግብዓት ለማድረስ እና ድጋፋዊ ክትትል ለማድረግ የሚረዱ ሁለት ሞተር ሳይክሎችን ለክልሉ ጤና ቢሮ አስረከበ::
***""""""""""""""""******
የሲዳማ ልማት ማህበር ኮሚኒኬሽን
ግንቦት 8/2018 ሀዋሳ
ድጋፉ የተደረገው በወንዶገነት ወረዳ ጤና ጽ/ቤት ሥር ለሚገኙ ሁለት ጤና አጠባበቅ ጣቢያዎች (አሩማ እና ባቦ ጮሮሮ ) በጤና አገልግሎት አሰጣጥ ማሻሻል ፕሮጀክት (strengthen service delivery project (SSD) ነው።
በርክክቡ ወቅት የሲዳማ ብ/ክ/መንግሥት ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ በላይነህ በቀለ እና የJSI የሲዳማ ክልል IPHCSD እና SSD አስተባባሪ ወ/ሮ ምንትዋብ ዘነበ፣ የሲዳማ ልማት ማህበር ም/ስራስካጅ አቶ ያለዉ ተከስተ እንዲሁም የወረዳው ጤና ጽ/ቤት የማኔጅመነት አባላት እና የሁለቱም ጤና አጠባበቅ ጣቢያ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
በርክብክቡ ወቅት የሲዳማ ብ/ክ/መንግሥት ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ በላይነህ በቀለ ባስተላለፉት መልዕክት JSI ከሲዳማ ልማት ማህበር ጋር በመቀናጅት በክልሉ በስድስት ወረዳዎች ላይ የእናቶችን፤ የህጻናትን እና የጨቅላ ህጻናትን ሞትና ህመም ለመቀነስ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እየራ ከመሆኑም በላይ የግብዓት መቆራረጥን ለማስለጥ በሚደረገውን ጥረት ለመደገፍ ሁለት የሞተር ሳይክሎች ድጋፍ በጣም አስፈላጊ መሆናቸዉን ገልጽዉ፣ ግብዐትን ከጤና ጣብያ ወደ ጤና ኬላ ግብዕት ከማድረስ በተጨማሪ ከጤና ኬላ ወደ ክትባት ጣብያዎቻችን እና የዉሎ ገብ ስራዎችን ለማሳለጥ ከፍተኛ አሰተዋዖ እንደሚኖራቸዉ በመግለጽ በአግባቡና በከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲሰራ መመርያ ሰተዋል፡፡
የJSI የክልሉ ኘሮግራም አስተባባሪ ወ/ሮ ምንትዋብ ዘነበ በበኩላቸዉ JSI በክልሉ ዉስጥ ብዙ ተግባራትን እየስራ መሆኑን ገልጸዉ በተለይም የእናቶችን፤ የህጻናትን እና የጨቅላ ህጻናትን ሞትና ህመም ለመቀነስ፤ በጤና ኬላ አእና በማህበረስብ ውስጥ አግልግሎቱን ተድራሽ ልማደረግ ከፍተኛ አሰተዋጾ እንዳለዉ ገልጸዋል፡፡ በተጨማርም የልማት ማህበሩ ም/ሥራ አሰፈፃሚ አቶ ያለዉ ተከስተ የልማት ማህበሩ ከJSI ጋር ለመተግበር እንዲያመች አንድ በክልል ደረጃ የፕሮጅከቶች አሰተባባሪ እና አምስት ወረዳ ኦፊሰሮችን በመቅጠር ስራዉን እየሰራ ሲሆን የዛሬዉ ድጋፍ ግባትን ለማሳለጥ ከJSI የተገኘ ተጨማር ድጋፍ መሆኑን በመግለፅ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደረጉ መሰል ተግባራትን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡
!
!
~Follow us on~
🌎website:https://sida.org.et/
🌎 telegram:https://t.me/+l9A1rzxwsCgzMTQ0
🌎 YouTube:https://www.youtube.com/
🌎 TikTok:-https://www.tiktok.com/?_t=8n5NdDvxjvh&_r=10