09/01/2024
የጨረታ ማስታወቂያ
የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስና /ኢኮ/ልማት መምሪያ
የሀዋሳ ከተማ አስ/ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ በ2016 በጀት ዓመት በታቀደው መሠረት በከተማ ውስጥ የሚሠሩ ሥራዎች መካከል አንዱ የቄራ አገልግሎት ለሚያሰራው የከብት በረት የግንብና የእርድ ክፍል ጥገና ሥራ ግዥ በተዘጋጀው ዲዛይን መሠረት በዘርፉ ሕጋዊ ፈቃድ ካላቸው ተቋራጮች መካከል በጨረታ አወዳድሮ ማሠራት ይፈልጋል፡፡
በዚህ መሠረት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተቋራጮች መወዳደር ይችላሉ፡፡
1. በኮንስትራክሽን ዘርፍ ደረጃ GC-6/ BC-6 እና ከዚያ በላይ ያላቸው፡፡
2. በሥራ መስኩ ህጋዊ የታደሰ ንግድ ፍቃድ ፣ የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉና የ2016 ዓ.ም የዘመኑን ግብር መከፈላቸውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ ፣
3. ተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ተመዝጋቢ የሆኑ፤
4. የቅራቢነት ምዝገባ ምስክር ወረቀት ማቅረብ አለባቸው፡፡
5. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ሲፒኦ (cpo) ወይም Bid Bond በባንክ የተመሰከረውን 40,000 (አርባ ሺህ ብር/ ከጨረታ ሰነድ ጋር አያይዞ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
6. የጨረታ ሰነዱን ከሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ፋይ/ኢኮ/ልማት መምሪያ ቢሮ ቁጥር 10 ( አስር) በመቅረብ ይህ ጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ21 /ሃያ አንድ/ ተከታታይ ቀናት ውስጥ ብር 500 አምስት መቶ ከፍላችሁ ሰነድ በመውሰድ ዋጋ ሞልቶ ማቅረብ አለበት፡፡
7. የጨረታ ሰነዱ በሰም ለየብቻቸው በታሸገ ኤንቬሎፕ አንድ ኦሪጂናል እና ሁለት ኮፒ (ቴክኒካል እና ፋይናንሻል) በመያዝ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተከታታይ ቀናት ፋይ/ ኢኮ/ልማ/ መምሪያ ቢሮ ቁጥር 10 (ግዢ ኬዝ ቲም ) ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
8. ጨረታው በ22ኛው ቀን ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ታሽጎ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኮሎቻቸው በተገኙበትም ሆነ ባልተገኙበት ከጠዋቱ 3፡30 ሠዓት በቢሮ ቁጥር 10 ይከፈታል፡፡ ይህ ቀን በበዓላት ቅዳሜ ወይም እሁድ ከሆነ ቀጥሎ ባለው የሥራ ቀን በተመሣሣይ ሰዓት የሚታሸግና የሚከፈትበት ቀን ይሆናል፡፡ የበዓል ቀን ከሆነ ደግሞ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ጨረታው ይከፈታል፡፡
9. ማንኛውም ተጫራች በሲዳማ ክልል እና ሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ውስጥ ተመሳሳይ ሥራ በእጁ ላይ ካለና የሥራው አፈጻጸም 70% ካልደረሰ በጨረታ መወዳደር አይችልም፡፡ ሥራው 70% እና በላይ የደረሰ ከሆነ ከሚመለከተው የመንግስት አካል ማረጋገጫ ደብዳቤ ማቅረብ የሚችሉ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
10. በጨረታ አከፋፈት ስነ-ስርዓት የተነበበው ዋጋ እና በአርትሜቲከ ቼክ በሚደረግበት ጊዜ በሁለቱ መካከል ከ2% (ከሁለት ፐርሰንት) በላይ ሆነ በታች ልዩነት ካለ ተጫራቹ በቀጥታ ከጨረታ ውጪ ይደረጋል።
11. ለጨረታ ያስገቡት ዋጋ ከቀረበ የመሐንዲስ ዋጋ ጥናት ጋር ሲነፃፀር ወደ ላይ ከአሥራ አምስት ፐርሠንት (15%) በላይ ከሆነ በቀጥታ ከጨረታ ውጪ ይደረጋል፡፡
12. ለጨረታ ያስገቡት ዋጋ ከቀረበ የመሐንዲስ ዋጋ ጥናት ጋር ሲነፃፀር ወደ ታች ከአሥራ አምስት ፐርሠንት (15%) በታች ከሆነ ለእያንዳንዱ ሥራ ዝርዝር ተጨባጭ የወቅቱ ገበያ የዋጋ ትንተና (Direct Unite cost Analysis sheet) ማቅረብ የሚችል እና ለዚህም መ/ቤቱ የጠየቀውን የውል ማስከበሪያ ዋስትና ገንዘብ ወይም መያዣ ገንዘብ መጠን ማቅረብ የሚችል መሆን ይኖርበታል፡፡
13. መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ [ 046-220-99-63/046-212-13-34
የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስና/ኢኮ/ል/መምሪያ ሀዋሳ