Gamo development association Geressie branch /ጋሞ ልማት ማህበር ገረሴ ቅርንጫፍ

  • Home
  • Ethiopia
  • Arba Minch'
  • Gamo development association Geressie branch /ጋሞ ልማት ማህበር ገረሴ ቅርንጫፍ

Gamo development association Geressie branch /ጋሞ ልማት ማህበር ገረሴ ቅርንጫፍ Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Gamo development association Geressie branch /ጋሞ ልማት ማህበር ገረሴ ቅርንጫፍ, Non-Governmental Organization (NGO), Arba Minch'.

Gamo Development Association (GaDA), is an indigenous, not-for- profit, non-religious and development oriented non-governmental organization.The organization has 3 levels of management; namely, the General Assembly/ the supreme organ of the organization,

👉በጋሞ ልማት ማህበር ገረሴ ቅርንጫፍ የ2018 ዓ.ም የአርሶ አደር አባላት መዋጮ ለመሰብሰብ የንቅናቄ መድረክ ከገረሴ ከገረሴ ከተማ አስተዳደር  ጋር በመሆን ተካሄደ (ጥቅምት 5/2018 ዓ....
16/10/2025

👉በጋሞ ልማት ማህበር ገረሴ ቅርንጫፍ የ2018 ዓ.ም የአርሶ አደር አባላት መዋጮ ለመሰብሰብ የንቅናቄ መድረክ ከገረሴ ከገረሴ ከተማ አስተዳደር ጋር በመሆን ተካሄደ (ጥቅምት 5/2018 ዓ.ም ገረሴ)

👉በዛሬው ዕለት ማለት በቀን 5/2/2018 ዓ.ም የጋሞ ልማት ማህበር ገረሴ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የ2018 ዓ.ም የአርሶ አደር አባላት መዋጮ ለመሰብሰብ የንቅናቄ መድረክ አካሂዷል። መድረኩ የተካሄደው ከገረሴ ከተማ አስተዳደር የገቢዎች ጽ/ቤት ጋር በመተባበር ሲሆን የገቢዎች ጽ/ቤትም የ2018 የመሬት ግብር በሚሰበስብበት እግረ መንገድ የልማት ማህበሩ መዋጮ እንዲሰበሰብ ለማድረግ ነው።

👉 የጋሞ ልማት ማህበር የገረሴ ቅርጫፍ ሥራ አስኪያጁ አቶ ሳሲዮስ ሻርቶ በመድረኩ እንዳስታወቁት ከ2 ሽህ 95 አባል አርሶ አደሮች የ2018 ዓ.ም መዋጮ 104,750 ብር (አንድ መቶ አራት ሺህ ሰባት መቶ ሃምሳ ) ብር ለማሰባሰብ ማቀዱን አስታውቋል። በእግረ መንገዱም ለተጀመረው ለገረሴ መካከለኛ ደረጃ ግንባታ 2ዙር ድጋፍ ከአንድ ግብር ከፋይ 100 ብር ከጠቅላላው ከ2,095 አርሶ አደር 209,500 (ሁለት መቶ ዘጠኝ ሺህ አምስት መቶ) ብር ለመሰብሰብ መታቀዱንም ገልፀዋል።

👉መድረኩን የመሩት የገረሴ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ኤርሚያስ ጋሞ ልማት ማህበር ጉዳይ ማለት የማንነታችን ጉዳይ በመሆኑና እኛ ለእኛው የሚንሰራ የእኛው ማህበር በመሆኑ ሁሉም አርሶ አደር ጊዜ ሳይሰጥ የአባልነቱን መዋጮ መክፈል፣ የሞዴል ት/ቤት ግንባታ ድጋፉንም ሳያንጠባጥብ መክፈል እንዳለበትና ይህም እስከ ጥቅምት 30/2018 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ ብቻ መጠናቀቅ እንዳለበት አበክረው ገልፀዋል።

👉የጋሞ ልማት ማህበር ገረሴ ቅርንጫፍ ስለ ትብብሩ የገረሴ ከተማ አስተዳደርን እያመሰገነ አርሶ አደር አባላቱ በተባለው ጊዜ ውስጥ ብቻ መዋጮውን በማጠናቀቅ የልማት አጋርነታቸውን እንዲገልፁ ጥሪ ያስተላልፋል።

ቅድሚያ ለጋራ ልማት!

👉በጋሞ ልማት ማህበር ገረሴ ቅርንጫፍ የ2018 ዓ.ም የአርሶ አደር አባላት መዋጮ ለመሰብሰብ የንቅናቄ መድረክ ከገረሴ ዙሪያ ወረዳ ጋር በመተባበር ተካሄደ (ጥቅምት 4/2018 ዓ.ም ገረሴ)👉...
14/10/2025

👉በጋሞ ልማት ማህበር ገረሴ ቅርንጫፍ የ2018 ዓ.ም የአርሶ አደር አባላት መዋጮ ለመሰብሰብ የንቅናቄ መድረክ ከገረሴ ዙሪያ ወረዳ ጋር በመተባበር ተካሄደ (ጥቅምት 4/2018 ዓ.ም ገረሴ)

👉በዛሬው ዕለት ማለት በቀን 4/2/2018 ዓ.ም የጋሞ ልማት ማህበር ገረሴ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የ2018 ዓ.ም የአርሶ አደር አባላት መዋጮ ለመሰብሰብ የንቅናቄ መድረክ አካሂዷል። መድረኩ የተካሄደው ከገረሴ ዙሪያ ወረዳ የገቢዎች ጽ/ቤት ጋር በመተባበር ሲሆን የገቢዎች ጽ/ቤትም የ2018 የመሬት ግብር በሚሰበስብበት እግረ መንገድ የልማት ማህበሩ መዋጮ እንዲሰበሰብ ለማድረግ ነው።

👉 የጋሞ ልማት ማህበር የገረሴ ቅርጫፍ ሥራ አስኪያጁ አቶ ሳሲዮስ ሻርቶ በመድረኩ እንዳስታወቁት ከ19 ሽህ 830 አባል አርሶ አደሮች የ2018 ዓ.ም መዋጮ 991,500 ብር (ዘጠኝ መቶ ዘጠና አንድ ሺህ አምስት መቶ ) ብር ለማሰባሰብ ማቀዱን አስታውቋል። በእግረ መንገዱም ለተጀመረው ለገረሴ መካከለኛ ደረጃ ግንባታ 2ዙር ድጋፍ ከአንድ ግብር ከፋይ 100 ብር ከጠቅላላው ከ19,830 አርሶ አደር 1,983,000 (አንድ ሚሊዬን ዘጠኝ መቶ ሰማኒያ ሦስት ሺህ) ብር ለመሰብሰብ መታቀዱንም ገልፀዋል።

👉መድረኩን የመሩት የገረሴ ዙሪያ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊና የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ኢዮብ ኢያሱ ጋሞ ልማት ማህበር ከእኛ ወስዶ ለእኛ የሚሰራ የእኛው ማህበር በመሆኑ ሁሉም አርሶ አደር ጊዜ ሳይሰጥ የአባልነቱን መዋጮ መክፈል፣ የሞዴል ት/ቤት ግንባታ ድጋፉንም ሳያንጠባጥብ መክፈል እንዳለበትና ይህም እስከ ጥቅምት 30/2018 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ ብቻ መጠናቀቅ እንዳለበት አበክረው ገልፀዋል።

👉የጋሞ ልማት ማህበር ገረሴ ቅርንጫፍ ስለ ትብብሩ የገረሴ ዙሪያ ወረዳን እያመሰገነ አርሶ አደር አባላቱ በተባለው ጊዜ ውስጥ ብቻ መዋጮውን በማጠናቀቅ የልማት አጋርነታቸውን እንዲገልፁ ጥሪ ያስተላልፋል።

ቅድሚያ ለጋራ ልማት!

👉በጋሞ ልማት ማህበር ገረሴ ቅርንጫፍ ድጋፍ በ2017 ዓ.ም   ከተማሩት ተማሪዎች እስከ አሁን ባለው መረጃ  #17 ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት አምጥተዋል (መስከረም 06/2018 ዓ....
16/09/2025

👉በጋሞ ልማት ማህበር ገረሴ ቅርንጫፍ ድጋፍ በ2017 ዓ.ም ከተማሩት ተማሪዎች እስከ አሁን ባለው መረጃ #17 ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት አምጥተዋል (መስከረም 06/2018 ዓ.ም ገረሴ)

👉በ2017 ዓ.ም በትምህርት ዘመን በጋሞ ልማት ማህበር ገረሴ ቅርንጫፍ ድጋፍ በስፔሻል ክፍል ትምህርታቸውን ከተከታተሉት እስከ አሁን ባለው መረጃ 17 ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያመጡ ሲሆን ከነዚህም #14ቱ ከገረሴ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት #2ቱ ከዘርጉላ 2ኛ ደረጃ ት/ቤትና #1 ደግሞ ከጎቦ ባኬ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ነው።

👉የጋሞ ልማት ማህበር ገረሴ ቅርንጫፍ ለተማሪዎቹ፣ ለቤተሰቦቻቸውና ለት/ቤቶቻቸው መልዕክቱን ያስተላልፋል!🙏🙏🙏

ቅድሚያ ለጋራ ልማት!

👉በጋሞ ልማት ማህበር ገረሴ ቅርንጫፍ ድጋፍ በስፔሻል ክፍል ከተማሩ ተማሪዎች ለጊዜው በደረሰን መረጃ ከ14 የሚበልጡ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት አምጥተዋል (መስከረም 5/01/2018...
15/09/2025

👉በጋሞ ልማት ማህበር ገረሴ ቅርንጫፍ ድጋፍ በስፔሻል ክፍል ከተማሩ ተማሪዎች ለጊዜው በደረሰን መረጃ ከ14 የሚበልጡ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት አምጥተዋል (መስከረም 5/01/2018 ዓ.ም ገረሴ)

👉በ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በጋሞ ልማት ማህበር ገረሴ ቅርንጫፍ ድጋፍ በገረሴ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት በስፔሻል ክፍል ትምህርታቸውን ሲከታተሉ ከነበሩት ተማሪዎች ለጊዜው በደረሰን መረጃ ወደ 14 ተማሪዎች የዩኒርሲቲ መግቢያ ውጤት አምጥተዋል። ሆኖም ይህ በገረሴ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ብቻ ፎርም የሞሉ ተማሪዎች ብቻ ውጤት ሲሆን በገጠር ቀበሌያት በሚገኙ በሌሎች 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ፎርም ሞልተው የስፔሻል ክፍል ትምህርታቸውን ግን እዚሁ የተከታተሉት ውጤት ታይቶ ሲጠናቀቅ ከዚህ በላይ መሆን እንደምችል የገረሴ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ር/መምህር ወፋሎ ወልቃ ገልፀዋል።

ቅድሚያ ለጋራ ልማት!

👉የገረሴ ከተማ አስተዳደር "ጳጉሜን ለትውልድ" ዘመቻ ቃል የገባውን 15,000 (አሥራ አምስት ሺህ ብር) ገቢ አደረገ።(ጳጉሜ 3,13,2017 ዓ. ገረሴ)👉የገረሴ ከተማ  አአስተዳዳር"ጳጉሜን...
08/09/2025

👉የገረሴ ከተማ አስተዳደር "ጳጉሜን ለትውልድ" ዘመቻ ቃል የገባውን 15,000 (አሥራ አምስት ሺህ ብር) ገቢ አደረገ።
(ጳጉሜ 3,13,2017 ዓ. ገረሴ)

👉የገረሴ ከተማ አአስተዳዳር"ጳጉሜን ለትውልድ" በሚል መሪ ቃል በኢኮኖሚ ችግር ውስጥ ላሉ ተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ ለማድረግ ለሚካሄደው የሀብት አሰባሰብ ዘመቻ ባለፈው ቃል የገባውን 15,000 (አስራ አምስት ሺህ ብር) ገቢ አድርጓል። ከልብ እናመሰግናለን🙏🙏🙏

👉ሌሎቻችሁ "ጳጉሜን ለትውልድ" በሚል መሪ ቃል ለኢኮኖሚ ችግር ለተጋለጡ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁሳ ድጋፍ ለማድረግ በሚካሄደው በሀብት አሰባሰብ ዘመቻ ድጋፋችሁን በ1000106672408 ገቢ በማድረግ እንድትተባበሩ እንገልፃለን።

ቅድሚያ ለጋራ ልማት!

👉የጋሞ ልማት ማህበር ገረሴ ቅርንጫፍ " " በሚል መሪ ቃል በኢኮኖሚ ችግር ውስጥ ላሉ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ለማድረግ የሚካሄደውን የሀብት አሰባሰብ ዘመቻ ማስጀመርያን ምክንያት ...
02/09/2025

👉የጋሞ ልማት ማህበር ገረሴ ቅርንጫፍ " " በሚል መሪ ቃል በኢኮኖሚ ችግር ውስጥ ላሉ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ለማድረግ የሚካሄደውን የሀብት አሰባሰብ ዘመቻ ማስጀመርያን ምክንያት በማድረግ ለገረሴ ዙሪያ ወረዳ #የምስጋና ሰርተፊኬት(ፕሬም) አበረከተ።

(ነሐሴ 27/2017 ዓ.ም ገረሴ)

👉የጋሞ ልማት ማህበር ገረሴ ቅርንጫፍ ከበጎ ተግባራት አንዱና ዋነኛ የሆነውን "ጳጉሜን ለትውልድ" በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ያለውን ንቅናቄ ምክንያት በማድረግ "የአርባ አርባ ሁለት ደረጃ" (አርባ ምንጭ፣ አርባ ሁለቱ ደሬዎች እና 40*42= 1680 ደረጃዎችን) ከአርባ ምንጮች ጋር የሚያገናኝ ፕሮጀክት የሚያሳይ ካርታ ያለበትን ሰርተፊኬት(ፕሬም) ለገረሴ ዙሪያ ወረዳው አበረከተ ።

👉የጋሞ ልማት ማህበር የገረሴ ቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጅ አቶ የገረሴ ዙሪያ ወረዳ እስከ አሁን ላደረጉት አስተዋፅኦ በማመስገን ሰርተፊኬቱን ያበረከቱ ሲሆን የገረሴ ዙሪያ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር በበኩላቸው ሁሌም ከልማት ማህበሩ ጋር ተያይዘን እንሰራለን በማለት "ጳጉሜን ለትውልድ" ዘመቻ 1,500 ብር ድጋፍ አድርገው ሌሎችም ድጋፍ እንድያደርጉ ጥሪ አስተላልፈዋል።

👉የመደገፍ አቅም ያላችሁ ሁሉ በኢኮኖሚ ችግር ውስጥ ላሉ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ በዓይነትም ሆነ በገንዘብ ድጋፍ እንድታደርጉ እየገለፅን "ጳጉሜን ለትውድ" የሀብት የማሰባሰብ ዘመቻ በይፋ የተጀመረ መሆኑን በድጋሚ እናበስራለን፡፡ በገንዘብ ድጋፍ የሚታደርጉ በጋሞ ልማት ማህበር በገረሴ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አካውንት ቁጥር 1000106672408 ላይ ገቢ ማድረግ የሚትችሉ መሆኑን ጭምር እንገልጻለን፡፡

(ዘገባው የጋሞ ልማት ማህበር የገረሴ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ነው)

"ቅድሚያ ለጋራ ልማት"!

👉የገረሴ ዙሪያ ወረዳ ረዳት የመንግሥት ተጠሪና ፖሌትካና የህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ    1,000  ብር በመክፈል "ጳጉሜን ለትልድ ዘመቻን" ተቀላቀሉ።👉የገረሴ ዙሪያ ወረዳ ረዳት የመ...
02/09/2025

👉የገረሴ ዙሪያ ወረዳ ረዳት የመንግሥት ተጠሪና ፖሌትካና የህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ 1,000 ብር በመክፈል "ጳጉሜን ለትልድ ዘመቻን" ተቀላቀሉ።

👉የገረሴ ዙሪያ ወረዳ ረዳት የመንግሥት ተጠሪና ፖሌትካና የህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ለጋሞ ልማት ማህበር ገረሴ ቅርንጫፍ 1,000 ብር በመክፈል "ጳጉሜን ለትውልድ" ዘመቻ ተቀላቅለዋል። ከልብ እናመሰግናለን🙏🙏🙏

👉ሌሎቻችሁ "ጳጉሜን ለትውልድ" በሚል መሪ ቃል ለኢኮኖሚ ችግር ለተጋለጡ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁሳ ድጋፍ ለማድረግ በሚካሄደው በሀብት አሰባሰብ ዘመቻ ድጋፋችሁን በ1000106672408 ገቢ በማድረግ እንድትተባበሩ እንገልፃለን።

ቅድሚያ ለጋራ ልማት!

👉የገረሴ ዙሪያ ወረዳ ም/አስተዳዳሪና የት/ቤቶች ጽ/ቤት ኃላፊ  አቶ  ,000  ብር በመክፈል "ጳጉሜን ለትልድ ዘመቻን" ተቀላቀሉ።👉የገረሴ ዙሪያ ወረዳ ም/አስተዳዳሪና የት/ቤቶች ጽ/ቤት ኃ...
02/09/2025

👉የገረሴ ዙሪያ ወረዳ ም/አስተዳዳሪና የት/ቤቶች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ,000 ብር በመክፈል "ጳጉሜን ለትልድ ዘመቻን" ተቀላቀሉ።

👉የገረሴ ዙሪያ ወረዳ ም/አስተዳዳሪና የት/ቤቶች ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ለጋሞ ልማት ማህበር ገረሴ ቅርንጫፍ 1,000 ብር በመክፈል "ጳጉሜን ለትውልድ" ዘመቻ ተቀላቅለዋል። ከልብ እናመሰግናለን🙏🙏🙏

👉ሌሎቻችሁ "ጳጉሜን ለትውልድ" በሚል መሪ ቃል ለኢኮኖሚ ችግር ለተጋለጡ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁሳ ድጋፍ ለማድረግ በሚካሄደው በሀብት አሰባሰብ ዘመቻ ድጋፋችሁን በ1000106672408 ገቢ በማድረግ እንድትተባበሩ እንገልፃለን።

ቅድሚያ ለጋራ ልማት!

👉የገረሴ ዙሪያ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊና የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ    1,000  ብር በመክፈል "ጳጉሜን ለትልድ ዘመቻን" ተቀላቀሉ።👉የገረሴ ዙሪያ ወረዳ ብልፅግና ጽ/ቤት ኃላ...
02/09/2025

👉የገረሴ ዙሪያ ወረዳ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊና የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ 1,000 ብር በመክፈል "ጳጉሜን ለትልድ ዘመቻን" ተቀላቀሉ።

👉የገረሴ ዙሪያ ወረዳ ብልፅግና ጽ/ቤት ኃላፊና የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ ለጋሞ ልማት ማህበር ገረሴ ቅርንጫፍ 1,000 ብር በመክፈል "ጳጉሜን ለትውልድ" ዘመቻ ተቀላቅለዋል። ከልብ እናመሰግናለን🙏🙏🙏

👉ሌሎቻችሁ "ጳጉሜን ለትውልድ" በሚል መሪ ቃል ለኢኮኖሚ ችግር ለተጋለጡ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁሳ ድጋፍ ለማድረግ በሚካሄደው በሀብት አሰባሰብ ዘመቻ ድጋፋችሁን በ1000106672408 ገቢ በማድረግ እንድትተባበሩ እንገልፃለን።

ቅድሚያ ለጋራ ልማት!

👉የገረሴ ዙሪያ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ  ዶ/ር   1,500  ብር በመክፈል "ጳጉሜን ለትልድ ዘመቻን" ተቀላቀሉ።👉የገረሴ ዙሪያ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር   ለጋሞ ልማት ማህበር ገረሴ ቅርን...
02/09/2025

👉የገረሴ ዙሪያ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር 1,500 ብር በመክፈል "ጳጉሜን ለትልድ ዘመቻን" ተቀላቀሉ።

👉የገረሴ ዙሪያ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር ለጋሞ ልማት ማህበር ገረሴ ቅርንጫፍ 1,500 ብር በመክፈል "ጳጉሜን ለትውልድ" ዘመቻ ተቀላቅለዋል። ከልብ እናመሰግናለን🙏🙏🙏

👉ሌሎቻችሁ "ጳጉሜን ለትውልድ" በሚል መሪ ቃል ለኢኮኖሚ ችግር ለተጋለጡ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁሳ ድጋፍ ለማድረግ በሚካሄደው በሀብት አሰባሰብ ዘመቻ ድጋፋችሁን በ1000106672408 ገቢ በማድረግ እንድትተባበሩ እንገልፃለን።

ቅድሚያ ለጋራ ልማት!

👉የጋሞ ዞን ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ   2,200 ብር በመክፈል "ጳጉሜን ለትልድ ዘመቻን" ተቀላቀሉ።👉የጋሞ ዞን ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ   ለጋሞ ልማት ማህበር ገረሴ ቅርንጫፍ 2,200...
02/09/2025

👉የጋሞ ዞን ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ 2,200 ብር በመክፈል "ጳጉሜን ለትልድ ዘመቻን" ተቀላቀሉ።

👉የጋሞ ዞን ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ አቶ ለጋሞ ልማት ማህበር ገረሴ ቅርንጫፍ 2,200 ብር በመክፈል "ጳጉሜን ለትውልድ" ዘመቻ ተቀላቅለዋል። ከልብ እናመሰግናለን🙏🙏🙏

👉ሌሎቻችሁ "ጳጉሜን ለትውልድ" በሚል መሪ ቃል ለኢኮኖሚ ችግር ለተጋለጡ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁሳ ድጋፍ ለማድረግ በሚካሄደው በሀብት አሰባሰብ ዘመቻ ድጋፋችሁን በ1000106672408 ገቢ በማድረግ እንድትተባበሩ እንገልፃለን።

ቅድሚያ ለጋራ ልማት!

የጋሞ ልማት ማህበር ገረሴ ቅርንጫፍ "ጳጉሜን ለትውልድ" ምክንያት በማድረግ  ለገረሴ ከተማ አስተዳደር የምስጋና ሰርተፊኬት(ፕሬም) አበረከተ።(ነሐሴ 26/2017 ዓ.ም ገረሴ) የጋሞ ልማት ማ...
01/09/2025

የጋሞ ልማት ማህበር ገረሴ ቅርንጫፍ "ጳጉሜን ለትውልድ" ምክንያት በማድረግ ለገረሴ ከተማ አስተዳደር የምስጋና ሰርተፊኬት(ፕሬም) አበረከተ።

(ነሐሴ 26/2017 ዓ.ም ገረሴ)

የጋሞ ልማት ማህበር ገረሴ ቅርንጫፍ ከበጎ ተግባራት አንዱና ዋነኛ የሆነውን "ጳጉሜን ለትውልድ" በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ያለውን ንቅናቄ ምክንያት በማድረግ "የአርባ አርባ ሁለት ደረጃ" (አርባ ምንጭ፣ አርባ ሁለቱ ደሬዎች እና 40*42= 1680 ደረጃዎችን) ከአርባ ምንጮች ጋር የሚያገናኝ ፕሮጀክት የሚያሳይ ካርታ ያለበትን ሰርተፊኬት(ፕሬም) ለከተማ አስተዳደሩ ዛሬ ጠዋት አበረከተ ።
የጋሞ ልማት ማህበር የገረሴ ቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጅ አቶ ሳሲዮስ ሻርቶ የከተማ አስተዳደርሩ እስከ አሁን ላደረጉት አስተዋፅኦ በማመስገን ሰርተፊኬቱን ያበረከቱ ሲሆን የገረሴ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ኤርሚያስ እሼተ በበኩላቸው ሁሌም ከልማት ማህበሩ ጋር ተያይዘን እንሰራለን በማለት "ጳጉሜን ለትውልድ" ዘመቻ 15,000 (አሥራ አምስት ሺህ) ብር ድጋፍ ለማድረግ ቃል ገብቷል።

ለሎቻችሁም በኢኮኖሚ ችግር ውስጥ ላሉ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ በዓይነትም ሆነ በገንዘብ ድጋፍ እንድታደርጉ "ጳጉሜ ለበረከት" የሀብት የማሰባሰብ ሥራ በይፋ የተጀመረ በመሆኑ የተቻለውን ሁሉ እንድታደርጉ በፍቅር እናሳስባለን፡፡ በገንዘብ ድጋፍ የሚታደርጉ በጋሞ ልማት ማህበር በገረሴ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አካውንት ቁጥር 1000106672408 ላይ ገቢ ማድረግ የሚትችሉ መሆኑን ጭምር እንገልጻለን፡፡

(ዘገባው የጋሞ ልማት ማህበር የገረሴ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ነው)

"ቅድሚያ ለጋራ ልማት"!

Address

Arba Minch'

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gamo development association Geressie branch /ጋሞ ልማት ማህበር ገረሴ ቅርንጫፍ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Gamo development association Geressie branch /ጋሞ ልማት ማህበር ገረሴ ቅርንጫፍ:

Share