20/02/2026
ሰዉኛ የበጎ አድራጎት ማህበር ከ30 በላይ ለሚሆኑ ለአቅመ ደካሞች የረመዳን ጾምን ምክንያት በማድረግ የማድ ማጋራት መርሐግብር አካሄደ፡፡
የካቲት 13/2018ዓ.ም
ሰዉኛ የበጎ አድራጎት ማህበር ከ30 በላይ ለአቅመ ደካሞች የረመዳን ጾምን ምክንያት በማድረግ የቦቆላ፣ክክ እና ዘይት ድጋፍ አድርጓል፡፡
በድጋፉ ወቅት የሚቶ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ከድር መሀመድ ፣ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አብዲ ዋበላ፣ምክትል አስተዳደር እና የፋይናንስ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ነጃ ቆርቻ ፣ የወረዳዉ አመራሮች እና የሰዉኛ በጎ አድራጎት ማህበር
አስተባባሪዎች ተገኝተዋል ።
የረመዳን ወር የመተዛዘን፣ የመረዳዳት እና የደስታ ወር ነው። ሰዉኛ የበጎ አድራጎት ማህበር ይህንን ታላቅ ወር ምክንያት በማድረግ፣ አቅመ ደካሞች በሰላም እና በደስታ እንዲጾሙ ለማስቻል ሲያከናውን የቆየውን የአስቤዛ ማሰባሰብ እና ማሰራጨት መርሃ-ግብር በስኬት አጠናቋል።
ባለፉት ቀናት ባደረግነው ከፍተኛ ጥረት፦ እጅግ ችግረኛ ለሆኑ ምስኪን ወገኖቻችን መድረስ ተችሏል። የተከፋፈለው አስቤዛ፦ በቆሎ፣ ዘይት እና የሾርባ ክክ መሰረታዊ የምግብ ቁሳቁሶችን ያካተተ ነው።ዛሬ እነዚህ ወገኖቻችን የረመዳን ወር ሲገባ "ምን አፍጥሬ አነጋለሁ?" የሚለው ጭንቀታቸው ተወግዶ በፊታቸው ላይ የታየው ፈገግታ የሁላችንም ኩራት ነው። ይህ ትልቅ ስኬት ያለ እናንተ የልግስና እጅ ፈጽሞ የማይታሰብ ነበር።
ምስጋና ለእናንተ!
በሀገር ዉስጥ እና ከሀገር ዉጪ ሆናቹ በገንዘባችሁ፣ በጉልበታችሁ፣ በሃሳባችሁ እንዲሁም ይህ ጥሪ ለብዙዎች እንዲደርስ በማድረግ አብራችሁን ለቆማችሁ ውድ ደጋፊዎቻችን በሙሉ ልባዊ ምስጋናችንን እናቀርባለን። ፈጣሪ በረከቱን በቤታችሁ ያፍስሰው!
የሰዉኛ የበጎ አድራጎት ማህበር ጉዞ ይቀጥላል። ወደፊትም ከጎናችን በመሆን የበጎነት አሻራችሁን እንድታሳርፉ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
በጋራ በመሆን የሰዎችን ህይወት መለወጥ እንችላለን!
ሰዉኛ የበጎ አድራጎት ማህበር
ሰዉኛ በጎ:- 1000406998529
ስልክ:- +251928714254
+251939841090
+251919572573