Wolla -Shasha students pages

Wolla -Shasha students  pages Teenagers community college

13/06/2025

በ2 ሚሊዮን ዶላር ዕድሜን ለማርዘም የሚደረግ ሙከራ
*******

የሰው ልጅ ዕድሜ ቢበዛ መቶ ነው፤ አብዛኛው ሰው 80ና 90ዎቹ ዕድሜ ላይ ደርሼ እንዳማረብኝ ይህችን ዓለም ብሰናበት ብሎም ይመኛል።

ከዚህ በተቃራኒው ደግም አንዳንዶች እርጅናን ከገታን ረጅም ዓመታትን ልንኖር እንችላለን በሚል የተለያዩ ሙከራዎችን ሲያደርጉ ቆይተዋል።

ምንም እንኳን እስካሁን የተሳካ ሙከራ ባይኖርም ይህንን ማሳካት እችላለሁ ብሎ የተነሳ አንድ ባለሃብት አለ።

ብራየን ጆንሰን ይባላል። ትውልድ እና እድገቱ በአሜሪካ ዩታህ ግዛት ነው። እርጅናን ማዘግየትና ህመሞችን መቀነስ እንዲሁም ከማርጀት ይልቅ ወደ ወጣትነት መሸጋገር ይቻላል ይላል።

ብራየን የሰው ልጅ አፈጣጠር ልክ እንደ ኮምፒዩተር ሶፍትዌር መሻሻል የሚችል ነው ብሎ ያምናል።

''ብሉፕሪንት'' የተሰኘ ፕሮጀክትም በመንደፍ ‘የአላረጅም ፣ አልሞትም’ መንገዱን ተያይዞታል።

ሁሌም በየቀኑ የተለያዩ ቫይታሚኖችን ይውጣል፤ አመጋገቡንም እጅግ በጥንቃቄ የተሞላ ሲሆን፤ ስፖርትም ይሰራል። በተጨማሪም ለተወሰኑ ሰዓታት ብቻ ነው የሚተኛው።

ከፍተኛ የሕክምና ክትትልም በማድረግም የሰውነቱ እያንዳንዷን ጤንነት ለማወቅ ጥረት ያደርጋል።

የ47 ዓመቱ ሚሊየነር ብራየን ይህም አልበቃ ብሎት በየቀኑ ከአንድ መቶ በላይ የተለያዩ የመድኃኒት እንክብሎችን እየወሰደ ነው።

ሃይፐርባሪክ ኦክሲጅን በተሰኘ ቴራፒ አማካኝነት ዝግ በሆነና ግፊት ባለበት ከባቢ ውስጥ የተጣራ ኦክሲጅን አየር ወደሰውነቱ እያስገባ የተጎዱ ህዋሳቶቹ እንዲሻሻሉ በማድረግ እርጅናን ለመከላከል እየጣረ ነው።

ለ90 ቀናት በየቀኑ ለ1 ሰዓት ተኩል ያህል በዚህ አይነት ሕክምና አፉ ላይ የኦክሲጅን አየር ማስገቢያ አድርጎ ያሳልፋል።

ብራየን ህልሙን ለማሳካት በዓመት 2 ሚሊዮን ዶላር ያወጣል ፤ ይህንን ሁሉ እያደረገ ቢሆንም የግል ሕይወቱ ግን ችግሮች የበዙበት ነው። ከትዳሩ ተፋቷል ፣ ሐይማኖቱንም ትቷል።

ለ5 ዓመታት ይህንን ሙከራ ያደረገው ብራየን ግን ወደወጣትነቴ እየተመለስኩ ነው ይላል።

ዘላለም የመኖር ፍላጎት የብራየን ብቻ አደለም፤ የብዙ ሰዎች ፍላጎት ነዉ።

የብራየን ሕይወት አንድ ጥያቄን እንድናነሳ ይጋብዘናል፤ ሕይወት አጭር መሆኗን አምነን እንቀበል ወይስ ዕድሜያችንን ለማርዘም እንታገል? እርስዎስ በዚህ ጉዳይ ላይ ምን ይላሉ?

በቢታንያ ሲሳይ

#እድሜ #እርጅና

13/06/2025
ጣናነሽ-2 ጀልባ ሞጆ ከተማ ደረሰች*************** ጀልባዋ ሞጆ ስትደርስ የከተማው ነዋሪ እንዲሁም የፌዴራል እና የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች ደማቅ አቀባበል አድርገውላታል። ጣናነሽ-...
11/06/2025

ጣናነሽ-2 ጀልባ ሞጆ ከተማ ደረሰች
***************

ጀልባዋ ሞጆ ስትደርስ የከተማው ነዋሪ እንዲሁም የፌዴራል እና የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች ደማቅ አቀባበል አድርገውላታል።

ጣናነሽ-2 ግንቦት 7 ቀን ወደ ኢትዮጵያ ከገባች ጀምሮ ላለፈው አንድ ወር ገደማ በአፋር ክልል የተለያዩ ከተሞችን እያቆራረጠች ጉዞ ስታደርግ ቆይታለች።

ጀልባዋ በግዝፈቷም በአይነቷም ለየት ያለች ስትሆን፤ ለኢትዮጵያም ከጀልባነት በላይ ብዙ ተምሳሌታዊ ትርጉም አላት።

በአሰግድ ሲሳይ

-2 #ጣናነሽ-2

26/05/2025

ሳይንቲስቶች በበረዶ የተሸፈነች አዲስ ፕላኔት አገኙ
********

ሳይንቲስቶች ከፕሉቶ ርቃ የምትገኝ አዲስ ፕላኔት አግኝተዋል።

አዲሷ ፕላኔት ከፀሐይ እጅግ ርቃ ስለምትገኝ በበረዶ ግግር የተሸፈነች መሆኗን የሥነ ፈለክ ተመራማሪዎች ገልጸዋል።

ይህ ግኝት የሕዋ ካርታና አፈጣጠርን በአዲስ መልክ ለመቃኘት የሚያስችል መሆኑ እየተጠቆመ ይገኛል።

አነስተኛ ፕላኔቷ በጊዜያዊነት "2017 OF201" ተብላ መሰየሟን ዓለም አቀፉ የአስትሮኖሚካል ሕብረት የአነስተኛ ፕላኔቶች ማዕከል አስታውቋል።

አዲሷ ፕላኔት ፀሐይን አንድ ጊዜ ለመዞር 25 ሺህ የምድር ዓመታትን እንደሚወስባት የግኝት ቡድኑን የመሩት ሲሃዎ ቼንግ አስታውቀዋል።

ለንፅፅር ያህል ሲያቀርቡትም ፕሉቶ በፀሐይ ዙሪያ አንድ ጊዜ ለመዞር 248 የምድር ዓመታትን እንደሚፈጅባት ገልጸው፤ አዲሷ አነስተኛ ፕላኔት ግን ከፕሉቶም እጅግ ርቃ ስለምትገኝ በፀሐይ ምህዋር የምታደርገው ጉዞ የተራዘመ መሆኑን አንስተዋል።

እጅግ ዘመናዊ የሆነ ቴሌስኮፕን በመጠቀም የተገኘችው አነስተኛዋ ፕላኔት ለተጨማሪ ምርምሮች በር ከፋች መሆኗን ናሳ አስታውቋል።
#ፕላኔቶች

27/02/2025

የሞባይል ሥልኮች የማብቂያ ዘመን እየመጣ ይሆን?
+++++++++++++

የካቲት 16/2017 (ጋዜጣ+)፡- ዛሬ ላይ ስንቶቻችን ነን የሞባይል ስልኮች የምንጠቀመው? እንደ ድንገት የሞባይል ስልካችንን ከቤት ረስተን ስንወጣ አልያም ሲጠፋብን የሚሰማን ስሜት ምንድነው?

በዓለማችን ከሰባት ቢሊየን በላይ የሞባይል ስልኮች በአገልግሎት ላይ እንደሚገኙ መረጃዎች ያሳያሉ።

ይህም በአማካይ እያንዳንዱ ሰው የሞባይል ስልክ ተጠቃሚ እንደሆነ ያሳያል። የሞባይል ቴክኖሎጂ ተግባራዊ ከሆነ ሶስት አስርት ዓመታት ተቆጥረዋል።

በዚህ ጊዜ ውስጥ ታዲያ ይህ ቴክኖሎጂ ዓለምን ከማዳረስ አልፎ የሰውን ልጅ አዕምሮ እስከመቆጣጠር ለመድረስ ብዙ ጊዜ አልፈጀበትም። ዛሬ ላይ ሞባይል ስልክ ትልቁ የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ ዋነኛ አካል ሆኗል።

በአሁኑ ወቅት ብዙዎቻችን ያለሞባይል መዋልና ማደር የማይቻል እስኪመስለን ድረስ በተጽዕኖው ስር ወድቀናል። ከምንሰራቸው ስራዎች ውስጥም ብዙ ነገሮች ከስልክ ጋር ተገናኝተዋል።

በስማርት ስልኮቻችን በዓለም ላይ የሚከናወኑ ሁነቶችን እንከታተላለን። ከዚያም አልፎ መረጃ እናሰራጨበታለን። ገንዘባችንን ማንቀሳቀስ እንችላለን። በአጠቃላይ ዘርፈብዙ ጠቀሜታ ሥራዎችን ለማከናወን እንጠቀምበታለን።

ይሁንና ይህ ወርቃማ የሞባይል ስልኮች ዘመን መጨረሻው እየተቃረበ መሆኑን የሜታው ፈጣሪና ባለቤት እየነገረን ነው።

ማርክ ዙከምበርግ እንደሚለው ለዓመታት የተገለገልንባቸው ስልኮች ቆይታ ዕድሜ አጭር ነው።

በዲጂታሉ ዓለም ቀጣዩ የስማርት ስልኮች ወራሽ ለመሆን ስማርት መነጽሮች ከወዲሁ ዝግጅታቸውን አጠናቅቀዋል።

ዙከምበርግ እንሚለው ሽግግሩ ተጀምሯል።

በቅርቡ ከቴክ ጋዜጠኛ ክሊዮ አብራም ጋር ባደረገው ቃለ ምልልስ፣ መጪው ጊዜ ይበልጥ መሳጭ፣ ተፈጥሯዊ እና ማህበራዊ መስተጋብርን እጅግ ያቀለለ ነው።

ቴክኖሎጂው ከእጅ ስክሪኖች ወደ ተለባሽ ቴክኖሎጂ የሚሸጋገር እንደሚሆንም አብራርቷል።

“በኮምፒውተር ውስጥ ያለው አዝማሚያ በይበልጥ በሁሉም ቦታ የሚገኝ፣ የበለጠ ተፈጥሯዊ እና የበለጠ ማህበራዊ መሆን ነው። በዙሪያህ ካሉ ሰዎች ጋር ያለችግር መገናኘት ትፈልጋለህ እና ይህ ምናልባት ከስልኮች በኋላ ቀጣዩ ትልቅ ቴክኖሎጂ ስማርት መነጽር ሊሆን ይችላል ብዬ አስባለሁ ”ሲል ዙከርበርግ ተናግሯል።
+++++++++++++++++++

#ኢትዮጵያ
#ዙከምበርግ #ሞባይል

26/02/2025

በረራ ላይ እያለ በሸረሪት ተነድፎ አውሮፕላን በድንገት ያሳረፈው አብራሪ
********************************************
በየካቲት 2022 ደግሞ ማሌዥያ ውስጥ ከዋና ከተማዋ ኳላ ላምፑር ወደ ሳባህ የሀገር ውስጥ በረራ በሚያደርግ አውሮፕላን ላይ ዘንዶ ተገኝቶ ብዙዎችን አሰገርሞ ነበር።
ዛሬ ደግሞ እያበረረ በነበረበት ወቅት ታራንቱላ በተለባለች መርዛማ ሸረሪት የተነደፈው አብራሪ አውሮፕላኑን በድንገት ለማሳረፍ ተገዷል።
አብራሪው የተነደፈው ከጀርመን ወደ ስፔን እያበረረ በነበረበት ወቅት መሆኑን ዘ ጋርዲያን ጋዜጣ ዘግቧል።
እንደጋዜጣው ዘገባ በሸረሪት የተነደፈው አብራሪ ጸረ-መርዝ መድሃኒት እስከሚሰጠው ድረስ የኢቤሪያ አውሮፕላን በረራ ዘግይቶ ነበር ተብሏል።
ይህ የአየር ላይ ድራማዊ ክስተት የተፈጠረው የኢቤሪያ ኤ320 አውሮፕላን ከጀርመን ዱሰልዶርፍ ተነስቶ ወደ ስፔኗ ማድሪድ ከተማ እየበረረ በነበረበት ወቀት መሆኑን ጋዜጣዉ ጠቅሷል።
ሸረሪቷ አውሮፕላኑ በዚህ ሳምንት መጀመሪያ በሞሮኮ ካዛብላንካ ባረፈበት ወቅት ገብታ ሊሆን እንደሚችል ይገመታል። አውሮፕላኑ በሰፔን ዋና ከተማ ካረፈ በኋላ እስከሚጸዳ ሶስት ሰአት በመዘግየቱ ወደ ጋሊሺያኗ ከተማ ቪጎ የሚሄዱ ተጓዦች እንዲጠብቁ ተደርገዋል።
አብራራው እብጠት የሚያስከትሉ በሽታዎችን ለማከም የሚውለውና ከከባድ አለርጅክ ጋር የተያያዙ እብጠቶችንና ሌሎች ምልክቶችን ለመቀነስ በስፋት ጥቅም ላይ የሚውለው ኡርባሶን ወይም በሳይንሳዊ ስያሜው ሜታይልፕሬዲኒሶሎን የተባለ መድሃኒት ተሰጥቶታል።
ኢቤሪያ አብራሪው ደህና መሆኑንና በጤናው ላይ የከፋ ጉዳት እንደማያስከትልበት ቢገልጽም ማድሪድ በደረሰበት ወቅት የህክምና እርዳታ መፈለጉ ወይም አለመፈለጉ ግልጽ አይደለም።
ሸረሪት የወጣችበት አውሮፕላን ከካዛብላንካ ተነስቶ ስፔን ለመድረስ ብራሰልዝ፣ ዙሪክና ቶሎዜን ጨምሮ በከተሞች አርፏል። የጋሊያሽያን ጋዜጣ ላ ቮዝ ዲ ጋላሽያ እንደዘገበው ምንም እንኳን አውሮፕላኑ አርብ ሌሊት ቪጎ ከማረፉ በፊት ቢጸዳም የተወሰኑ መንገደኞች ሸረሪት ፈርተው መቀመጫቸውንና መተላፋያውን በተደጋጋሚ ሲፈትሹ ተስተውለዋል።
የማሌዥያ አየርመንድ ባወጣው መግለጫ "እንዲህ አይነት ክስተት የፈጠር እድሉ በጣም ጠባብ ነው" የሚል ምላሽ ሰጥቶ ነበር።
Via- አልዓይን

26/02/2025

የነባሩ ፓስፖርት መጠቀሚያ ጊዜ ሲጠናቀቅ አዲሱን ፓስፖርት ያለ ክፍያ ማግኘት ይቻላል ተባለ

(ባላገሩ ቴሌቪዥን፣ የካቲት 19 ቀን 2017 ዓ.ም )

ነባሩ ፓስፖርት አሁንም ጥቅም ላይ እንደሚውል እና የመጠቀሚያ ጊዜው ሲያበቃ አዲሱን ፓስፖርት ያለ ምንም ክፍያ ማግኘት እንደሚቻል ተገለጸ፡፡

በዘርፉ የመጨረሻ ቴክኖሎጂን የተጠቀመው ኢ-ፓስፖርት በውስጡ የያዘው ቺፕ ተመሳስሎ የመሠራት ዕድሉን እንደሚቀንስ የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት ገልጸዋል፡፡

ይህም ለሀገር ደኅንነት እና ለድንበር ቁጥጥር የጎላ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት የጠቀሱት ዳይሬክተሯ፣ በሀገር አቀፍ ደረጃ አዲስ ፓስፖርት የማግኘት ፍላጎት ከፍ ማለቱንም አስታውቀዋል፡፡
በክልሎች 10 እና በአዲስ አበባ 4 ቅርንጫፎችን በመክፈት ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት መታቀዱን መግለጻቸው ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።

14/03/2023

በሥር ፍርድ ቤት ያልተነሰ ክርክር በይግባኝ ሰሚ ፍ/ቤት
የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 74፣ 328(2) እና 182(2) ላይ የተሰጠው ትርጉም
======================
ተከሳሽ በራሱ ቸልተኝነት በታችኛው ፍርድ ቤት መከራከሪያ ሊያደርጋቸው የሚገቡ ነጥቦችን በስር ፍርድ ቤት ባላነሳበት ሁኔታ ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት በራሱ አነሳሽነት አንስቶ ውሣኔ መስጠት የማይችል ስለመሆኑ የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 328(2) እና 182(2) ቅጽ 6 በመ/ቁ. 25026 የተሰጠው ውሳኔ ሰጥቷል።

የመጀመሪያውን ደረጃ ያለበቂ ምክንያት ክሱ በሚሰማት ጊዜ ሳይቀርብ ቀርቶ መከራከሪያውን ባለማቅረቡና የፍትሐብሄር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 74 በሚደነግገው የጊዜ ገደብ ውስጥ ማለትም በሰላሳ ቀን ውስጥ ወደ ክርክሩ እንዲገባ ጥያቄ ባለማቅረቡ ጉዳዩ በሌለበት ታይቶ ተወስኗል፡፡ ተጠሪ ወደ ከፍተኛ ፍ/ቤት ወደ ክርክሩ እንድገባ ያልፈቀደልኝ በአግባቡ አይደለም በማለት ለይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት ይግባኝ አላቀረበም፡፡ ይግባኝ ባይ የፍርድ ቤቱ መጥሪያ ደርሶት ቀርቦ ባልተከራከረበት ሁኔታ፣ በሌለበት ታይቶ በተሰጠው ውሣኔ ላይ ቢያቀርበው ይግባኝ በሥር ቀርቦ በመከላከያነት ሊያቀርባቸው የሚችለውን ሁሉንም የመከራከሪያ ነጥቦች በማንሣት የይግባኝ ቅሬታው መሰረት ማድረግ እንደማይችል ከፍትሐብሄር ሕግ ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 328 ንዑስ አንቀፅ 2 ድንጋጌ ለመረዳት ይችላል፡፡ ምክንያቱም እንኳንስ የፍርድ ቤት መጥሪያ ደርሶት የቀረበበትን ክስ ማስረጃ ለማስተባበል በሕጉ መሰረት ባለመቅረቡ ጉዳዩ በሌለበት ታይቶ የተወሰነበት ተከራካሪ ጉዳዩ እሱ ባለበት ታይቶና ክሱ ወይም የመከላከያ መልሱና ማስረጃው ተሰምቶ የተወሰነበት ወገን በይግባኝ ደረጃ በሥር ፍርድ ቤት ያላነሳውን አዲስ መከራከሪያ ማቅረብ እንደማይችል የፍትሐብሄር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 328 ንዑስ አንቀፅ 2 ይደነግጋል፡፡ በመሆኑም በሌለበት ውሣኔ የተሰጠበት ተከራካሪ በሥር ቀርቦ መከላከያ ሊያደርጋቸው የሚገባውን የመከራከሪያ ነጥቦች በይግባኝ ቅሬታው የመከራከሪያ ነጥብ አድርጎ ለማንሳት ከላይ የተጠቀሰው የሕግ ድንጋጌ የማይፈቅድ ሲሆን ተከራካሪው እንኳን ቢያነሳው ይግባኙን የሚያየው ፍርድ ቤት ውድቅ ሊያደርገው ይገባል፡፡
በሌለበት ውሣኔ የተሰጠበት ሰው በሌለበት በተሰጠው ውሳኔ ላይ ሊያነሳቸው የሚገባው የይግባኝ ቅሬታ ነጥቦችና የይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤትም ተቀብሎ ሊመረምራቸው የሚችላቸው መከራከሪያዎች እጅግ በጣም ውስን ናቸው፡፡ ይኽውም በክርክሩ ገብቶ የመከላከያ መልስና ማስረጃውን ባያቀርብም በከሳሽ በኩል የቀረበው ክስ ማስረጃ እሱን በሕግ አግባብ ኃላፊ የማያደርግ ሆኖ እያለ ፍርድ ቤቱ፣ የከሳሽን ክስና ማስረጃ ሲመዝን በፈጸመው የጎላ ስህተት ምክንያት ፍትሃዊ ያልሆነ ውሣኔ የተወሰነበት መሆኑን የሚያረጋግጡና ማንም ተከራካሪ ወገን ባያነሳቸውም ፍርድ ቤቱ በራሱ አነሳሽነት ሊያነሳቸው የሚገቡ መሰረታዊ የሕግ ጉዳዮች በማለፍ ውሳኔ መሰጠቱን የሚያመላክቱ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡ አንድ ተከራካሪ ክስና ማስረጃ ደርሶት በራሱ ቸልተኝነት ምክንያት ለሥር ፍርድ ቤት በመከራከሪያነት አላቀረባቸውም፡፡ በክርክሩ ሂደት ባለመቅረባቸውም ጉዳዩ በሌለበት ተሰምቶና ተመርምሮ ሲወሰን እነዚህን ተከራካሪ በሌለበት አይቶ በሰጠው ውሳኔ ላይ የተፈጸመ የሕግ ወይም የፍሬ ጉዳይ ስህተት በሌለበት ሁኔታ ፍርድ ቤቱ በራሱ ሊያነሳቸው የማይፈቀድለትን የተጠሪን መከራከሪያዎች ለምን ራሱ አነሳው የሚል ይዘት ያለው መሰረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት ነው፡፡
ሁለተኛው ደረጃ በተመለከተ፣ በሕግ በልዩ ሁኔታ ካልተደነገገ በስተቀር ፣ በይግባኝ የሚደረገው ክርክር በሥር ፍርድ ቤት የተነሳና የታየ ጉዳይ የሚመለከት እንደሆነና፣ ይግባኝ ሰሚው ፍ/ቤት የሥር ፍርድ ቤት ክርክሩን በሚመራበት ማስረጃ በሚቀበልበት ወይም በሚመዝንብት እና ውሣኔ በሚሰጥበት ወቅት የፈጸማቸውን የሕግና የፍሬ ጉዳይ ስህተቶች ለማረምእንደሆነ ግልጽ ነው ፡፡ በዚህ ሂደት ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት በሥር ፍርድ ቤት ያልታየና ያልተያዙ ጭብጦች መርምሮ እንደሚወስን የፍትሐብሄር ሕግ ቁጥር 182 ንዑስ አንቀፅ 2 ይደነግጋል፡፡ ሆኖም ለይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት በዚህ ድንጋጌ የተሰጠው ስልጣን ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት ተከራካሪዎች በሥር ፍ/ቤት በመከላከያነት ሊያነሷቸው የሚችሏቸው ነገር ግን ያላነሷቸውን የመከራከሪያ ነጥቦች በራሱ አነሳሽነት በማንሳት ውሣኔ የመስጠትን ሁኔታ የሚጨምር አይደለም፡፡ በሕጉ የተቀመጡትን ሁኔታዎች በማክበር ቀርቦ በመከላከያ መልሱ ሊያነሳቸው የሚገቡ የመከራከሪያ ነጥቦች በራሱ ቸልተኝነት ምክንያት ባለማቅረቡ ፣ ጉዳዩ በሌለበት ታይቶ ውሳኔ ሲሰጥ መከላከያ ሊያደርጋቸው የሚገባቸውን ነጥቦች በሥር ፍርድ ቤት ቀርቦ ባልተከራከረበትና ባላነሳበት ሁኔታ ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት በይግባኝ ተቀብሎና በራሱ አነሳሽነት አንስቶ መሻሩ የፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 328 ንዑስ አንቀፅ 2 እና ከፍትሐብሔር ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 182 ንዑስ አንቀፅ 2 ድንጋጌዎች መንፈስና ዓላማ ጋር የማይጣጣም እና መሰረታዊ የሕግ ስህተት ያለበት ነው።

Address

West
Adiya

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Wolla -Shasha students pages posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Wolla -Shasha students pages:

Share