SOZO TUBE

SOZO TUBE ቅድስና ለእግዚአብሔር!!

"እግዚአብሔር ጭንቀታችን ይገባዋል"ሌሊቱ 9፡00 ሰዓት ሆኗል፣ እኔ ግን አሁንም ነቅቻለሁ። አእምሮዬ መሮጡን አላቆመም—ያልተከፈሉ ሂሳቦች፣ እየሳሱ ያሉ ጓደኝነቶች፣ ነገ ምን ሊያመጣ ይችላል ...
28/02/2025

"እግዚአብሔር ጭንቀታችን ይገባዋል"

ሌሊቱ 9፡00 ሰዓት ሆኗል፣ እኔ ግን አሁንም ነቅቻለሁ። አእምሮዬ መሮጡን አላቆመም—ያልተከፈሉ ሂሳቦች፣ እየሳሱ ያሉ ጓደኝነቶች፣ ነገ ምን ሊያመጣ ይችላል የሚለው ፍርሃት። በዚህ ጭንቀት እየሰመጥኩ፣ የማልታይና የተረሳሁ ሆኖ ተሰማኝ።

ይህን ሀሳብ ከመሸሽ ስልኬን ከፍቼ፣ ትኩረቴን ለመቀየር በከንቱ ማሸብለል ጀመርኩ. . . በድንገት አንድ ጥቅስ አየሁ፡-
📖 "እርሱ ስለ እናንተ ያስባልና፣ የሚያስጨንቃችሁን ሁሉ በእርሱ ላይ ጣሉ።" (1 ጴጥሮስ 5:7) . . ደረቴ እየደለቀ ቃላቱን ተመለከትኩ። "እግዚአብሔር ሆይ… በእርግጥ ታስብልኛለህ?" በሹክሹክታ ጠየቅሁ።
ከዚያም እናቴ አንድ ጊዜ የነገረችኝን ነገር አስታወስኩ፡-
"በጭንቀት እየሰመጥክ እንደሆነ ሲሰማህ፣ አትያዘው። ለኢየሱስ ስጠው። እሱ ሊሸከምልህ በቂ ጥንካሬ አለው።"
. . እንባዎች አይኖቼን ሞሉ። በጥልቅ ተንፍሼ ስልኬን ዘግቼ እጄን በልቤ ላይ አደረግሁ። "እግዚአብሔር ሆይ፣ ዛሬ ፍርሃቴን ሁሉ ላንተ እሰጣለሁ። አንተ እንደምታስብልኝ አምናለሁ።"
በዚያ ቅጽበት፣ አንድ ነገር ሲቀየር ተሰማኝ። ችግሮቼ አልተወገዱም፣ ነገር ግን ለመጀመሪያ ጊዜ ብቻዬን አልሸከምኳቸውም። ያ ሁሉንም ነገር ለወጠው።

ቁልፍ ነጥቦች፡-
• እግዚአብሔር ጭንቀታችንን ያያል – በችግሮቻችን ውስጥ ብቻችን አይደለንም።
• ጭንቀቶቻችንን ለእርሱ እንስጥ – እነሱን ለመሸከም በቂ ጥንካሬ አለው። (1 ጴጥሮስ 5:7)
• መታመን ሰላምን ያመጣል – ችግሮቻችን ወዲያውኑ ላይጠፉ ይችላሉ፣ ነገር ግን የእግዚአብሔር መገኘት ሁሉንም ነገር ይለውጣል።

🔄 https://t.me/sozo_purity
🔄 https://shorturl.at/6uJKY

ለምን ሁልጊዜ በኃጢአት እወድቃለሁ? የኃጢአት እና የሱስ ዑደቶችን መስበርመንፈሳዊ ህይወታችሁን ስታስቡ የኋሊት እየተጓዛችሁ እንዳለ የተሰማችሁ ጊዜ አለ? ከኃጢአት ለመላቀቅ ትሞክራላችሁ፣ ነገ...
27/02/2025

ለምን ሁልጊዜ በኃጢአት እወድቃለሁ?
የኃጢአት እና የሱስ ዑደቶችን መስበር

መንፈሳዊ ህይወታችሁን ስታስቡ የኋሊት እየተጓዛችሁ እንዳለ የተሰማችሁ ጊዜ አለ?
ከኃጢአት ለመላቀቅ ትሞክራላችሁ፣ ነገር ግን... BooM! ወዲያውኑ ወደጀመራችሁበት ትመለሳላችሁ። 😔 ብቻችሁን አይደላችሁም። ይህ ብዙዎቻችን የምንጋፈጠው ጦርነት ነው።

እውነቱን ስናወራ ሁሌታው የሚያበሳጭ፣ ተስፋ የሚያስቆርጥ፣ እና አንዳንድ ጊዜ እምነታችንን እንድንጠራጠር የሚያደርግ ነው። ግን እውነቱ ይህ ነው፡ እግዚአብሔር በሽንፈት ዑደት ውስጥ እንድንኖር አይፈልግም። በነጻነት እንድንመላለስ ይፈልጋል! ✨

ታዲያ ለምን መውደቃችንን እንቀጥላለን?
እዚህ ዑደት ላይ እንድንቆይ ምክንያት ሊሆኑ የሚችሉ ነገሮች አሉ፡

- ያልተሟሉ ፍላጎቶች፡ ምናልባት በተሳሳተ ቦታዎች ላይ የህይወትን ትርጉም እየፈለግን ሊሆን ይችላል። (ለምሳሌ፡ በማህበራዊ ሚዲያ ውስጥ የመወደዳችንን ማረጋገጫ. . .)

የምናምናቸው ውሸቶች፡ ጠላት ድርጊታችንን የሚያጸድቁ ውሸቶችን ያሾካሽካል። (ለምሳሌ፡ "ይህ አንድ ጊዜ አይጎዳም፣" "ሌላው ሁሉ እያደረገው ነው።")

ያልተፈወሱ ቁስሎች፡ ያለፉት ህመሞች ጤናማ ወዳልሆኑ የመፈወሻ ዘዴዎች ተጋላጭ ሊያደርጉን ይችላሉ።
ተጠያቂነት ማጣት፡ ድጋፍ በሚያስፈልገን ጊዜ ጦርነቶችን ብቻችንን ለመዋጋት እንሞክራለን።
ቀስቃሾችን ችላ ማለት፡ ወደ ስህተት የሚመሩንን ሁኔታዎች አንለይም ወይም አንርቅም።

ግን የምስራች!! የእግዚአብሔር ጸጋ ከማንኛውም ኃጢአት የበለጠ ኃይለኛ ነው!

📖 የመጽሐፍ ቅዱስ እውነቶች፡

1 ዮሐንስ 1:9፡ "ኃጢአታችንን ብንናዘዝ ኃጢአታችንን ይቅር ሊለን ከዓመፃም ሁሉ ሊያነጻን የታመነና ጻድቅ ነው።"
ሮሜ 6:14፡ "ከጸጋ በታች እንጂ ከህግ በታች ስላልሆናችሁ ኃጢአት አይገዛችሁምና።" "

አወይ ፈተናዬ ቅዳሜ አመሻሽ ላይ ነው ድብርቴ ከሌላው ቀን ይልቅ እጅጉን ልቋል:: ከጊቢያችን ውስጥ ከዋናው መኖርያ ራቅ ብላ በምትገኘው ክፍሌ ከቴሌቪዥናችን ፊትለፊት ሪሞተር ጨብጬ ከስጋዬ ጋ...
07/11/2024

አወይ ፈተናዬ

ቅዳሜ አመሻሽ ላይ ነው ድብርቴ ከሌላው ቀን ይልቅ እጅጉን ልቋል:: ከጊቢያችን ውስጥ ከዋናው መኖርያ ራቅ ብላ በምትገኘው ክፍሌ ከቴሌቪዥናችን ፊትለፊት ሪሞተር ጨብጬ ከስጋዬ ጋር እየታገልኩ ነው:: ብቻዬን ስሆን እንዲህ አይነት ፈተና ብዙ ጊዜ ይገጥመኛል::ለእኔ ይህ አዲስ አይደለም ብዙ ጊዜ ተሸንፌበታለሁ አምላኬንም አሳዝኜበታለሁ::በዚህ ችግሬ ምክንያት ውሎዬ እና አዳሬ በሰው የታጀበ እንዲሆን ጥብቅ መሻቴ ነው:: በእጄ ከፍርሀቴ የተነሳ የሙጥኝ ብዬ የያዝኩት የቴሌቪዥን መቆጣጠርያ ሪሞት አንደበት ኖሮት ቢናገር የእኔን ጉድ ከማንም በላይ ያወራችሁ ነበር:: ብዙ የሚስጢር ኮዶችን እንዳስገባሁባት ከእኔ እና ከሪሞተሯ በስተቀር ማንም የሚያውቅ የለም:: ብዙ ስጋዊ ነገሬን የሚያነሳሱ የተሌቪዥን ቻናሎችን ሞልቼበታለሁ:: ታድያ ዛሬ ቤት ማንም ስለሌለ ይህን ቻናል ከፍቼ ልመልከት አልመልከት በሚል እሰጣ ገባ ውስጥ እያለሁ ከመቅፀብት ጣቶቼ ከቁጥጥሬ ውጭ በመሆን የሪሞተሩን ቁልፎች ተጫኑ:: ወዲያው በስክሪኑ ላይ በብዥታ ምስል ፊታቸው ተሸፍኖ ልቅ የሆነ ወሲብ የሚፈፅሙ ጥንዶችን ተመለከትኩ :: ምስላቸውን መመልከት ስጀምር አንዳች ነገር ሊሰርቅ እንዳቀደ ሰው ግራ እና ቀኜን ዞር ዞር ብዬ አየሁ:: ረዘም ላለ ሰዐት መመልከት እንድችል ግን ግዴታ ወጣ ብዬ የክፍሌን ዙርያ ማየት እና ሰው እንደሌለ ማረጋገጥ አለብኝ:: ዛሬ ቤት ማንም ባይኖርም የዘውትር ቅድመ ሁኔታዬ ስለሆነ አረጋግጬ በእግሬ ጣት ቀስስ ብዬ ወደ መቀመጫዬ ተመለስኩ::ቪዲዮውን መመልከት ስጀምር ድንገት ሰውነቴ በክፋት ሲወረር ተሰማኝ:: በሰመመን የክፋትን አለም አሰስኩ::
ይህ ለእኔ ትልቅ ፈተና ነበር::ሰውነቴ በሙሉ አይን አውጥቶ የእርቃነ ስጋቸውን ምስል እየቀረፀ አዕምሮዬ ውስጥ ሲያከማች ይታወቀኛል:: ግማሹ እኔነቴ የማደርገውን ነገር ቢቃወም ግን የማቆሙን ሐይል አጣው:: ከብዙ ደቂቃዎች በኋላ ጨርሼ ከክፍሌ ወጣሁ::በዚች ጥቂት ደቂቃ ውስጥ ግን ብዙ ምስሎችን በጭንቅላቴ ስዬ ነበር።ይህ ምስል ምስል እለት እለት ብዙ ፈተና ያመጣብኝ ነበር።የዛሬው ድርጊቴ የመጀመርያዬ አይደለም። ብዙ ጊዜ ብቻዬን ስሆን ማከናወን የሚቀናኝ ይህ ነው።ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም ስቀላቀል ብዙ ነፃነት ተሰማኝ የሁል ጊዜ ተግባሬ ይህን የወሲብ ፊልም ማየትና ራሴን በራሴ ማርካት(masterbation) ሆነ። በዚህ ተግባሬም በጣም ብዙ ፀፀት እሸምት ነበር።
ብዙ ጊዜ ይህን ተግባሬን ለመተው ሞከርኩ ነገር ግን ለምን እንደሆነ አላውቅም ከሳምንት በኋላ ተመልሼ እዛው እገኛለሁ።የእኔ ትልቁ ችግር ፖርኖ ማየት ብቻ ሳይሆን በቪዲዮው ላይ ያሉ አክተሮች አለባበስ አሳሳቅ እና የእያንዳንዷ እንቅስቃሴ ምስል ቀንቀን ት/ቤት ውስጥ የማያቸውን ሴቶች ያለማቋረጥ በመጥፎ እይታ እንድመለከታቸው ማድረጉ ጭምር ነው።አጭር ቀሚስ የለበሰች ሰውነቷን ጥብቅ አድርጎ የሚይዝ ልብስ የለበሰች ሴት ለእኔ እርቃኗን ሆና ነው የምትታየኝ።አይኖቼ ልብሷን አውልቀው መላ አካላቷን ፍንትው አድርገው ውስጤ ያስቀምጣሉ።እነዚህን እህቶች እያሰብኩ ደግሞ ማታ መጥፎ አለም ውስጥ እገባለሁ።
ፀፀት እና እራሴን መጥላት የሁልጊዜ ተግባሬ ነበር።
"ጌታ ሆይ እርዳኝ።"
"ይቅር በለኝ።"
ሁል ጊዜ እላለሁ ነገር ግን ተመልሼ እራሴን እዛው አገኛለሁ።ምክንያቱ ደግሞ ፅኑ የውሳኔ ሰው አለመሆኔ ነበር።

እንደ ዮሴፍ እንድሆን እርዳኝ!!

መፅሐፍ ቅዱስ አንብቤ አላውቅም ነበር።አንድ ቀን ታድያ በምን አይነት አጋጣሚ እንደሆነ ባላውቅም [እውነት ለመናገር ካለሁበት ስቃይ ለመላቀቅ ስል ነው] ከዘፍጥረት ጀምሮ ማንበብ ጀመርኩ።ታድያ በጥልቀት እያጠናው ባልሔድም ስለ ሰው ልጅ ክፋት እና ስለ እግዜአብሔር ምህረት አስተውያለሁ። እንደ ዮሴፍ አይነቱን ታሪክ ማንበቡ አቋሜን ማስተካከል እንዳለብኝ እረድቶኛል። ሴይጣን ደግሶ እና ሁሉንም ነገር አመቻችቶ አቅርቦለት ዮሴፍ እምቢ ብሎ መሸሹ እንደ እኔ አይነቱ ከሰይጣን ጋር አብሮ የመቀበርያውን ጉድጓድ የሚቆፍር ምንኛ ሞኝ እንደሆንን አሳየኝ።
እለት እለት ይህን የዮሴፍን ሽሽት ማሰላሰል ትልቅ ብርታት ሆኖኝ ከነበርኩበት ስቃይ ተላቅቄ አለሁ። ከምንም በላይ ከዚህ አይነት ስቃይ ሊያላቅቅ የሚችል የእግዜአብሔር ፀጋ ብቻ ነው።

ክብር ለክርስቶስ ይሁን!!
⬇️ ይቀላቀሉን ⬇️
https://t.me/joinchat/AAAAAEQpgnjWczaPdu0FwA
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖
🚻🚻 t.me/sozo_purity

Address

Addis Ababa

Telephone

+251974860210

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when SOZO TUBE posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to SOZO TUBE:

Share