27/03/2026
የ10ኛ የኢትዮጵያ እጅ ኳስ ፕርሚየር ሊግ ሁለተኛ ዙር ጨዋታ በሀዋሳ ከተማ ተጀመረ።
የጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ
“ሀዋሳ ተሞሽራለች ከፍተኛ ደስታ ልገልፅላቹ እወዳለው ለመላው ኢትዮጵያ ህዝብ ሀዋሳ ተሞሽራለች ቅዳሜና እሁድ ምን ታደርጋለች ኑ እያለች ስለሆነ በአዲስ አበባ በተለያዩ የሀገራችን ክፍላት ያላቹ ሰዎች የሀዋሳን ብርሀን የህዝቡን ፍቅር ታሪካዊ ማንነቱን ቅዳሜና እሁድ እየመጣቹ እንድትጋሩ ከሀዋሳ ግብዣ አቀርብላችሆለው "
ግብዣ ባስተላለፉ ማግስት በከተማዋ ክቡር ከንቲባ ጥራቱ በየነ እና ባልደረቦቻቸው ኑ ምቹ እናደርጋለን በማለት የረጅም አመት የእጅ ኳስ ቤተሰብ ጥያቄ የሆነው የውድድር ቦታ ሳምንት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ሰርተው ዝግጁ አድርገው የሀገሪቱ ከፍተኛ ውድድርን በማስተናገድ በድምቀት ተጀምሯል።
በሀዋሳ የተገኙት የ10 ክለባት ልዑካንም እውነትም ሀዋሳ ተሞሽራለች በማለት የጠቅላይ ሚኒስትሩን ቃል አረጋግጠዋል።
የስፖርት መሠረታዊ የእድገት ምንጭ የማዘውተሪያ ቦታ ዝግጅት ነውና ሀዋሳ የጥሩ ተሞክሮ መሪነቷን አሳይታለች።
ይህም ስኬት ጠንካራ የነበረውን የሀዋሳ ከተማ እጅ ኳስ ክለብ ወደ ውድድር በመመለስ ሙሉ ስኬት እንደሚያሳዩን አንጠራጠርም።
በሎጊታ እጅ ኳስ ሜዳ በመካሄድ ላይ ያለው የፕሪሚየር ሊግ ውድድር መጋቢት 18/2018 የተጀመረ ሲሆን ውድድር እስከ መጋቢት 26/2018 እንደሚቆይ እየገለፅን በዛሬው ዕለት በተካሄደ የመክፈቻ ውድድር በ12ኛ ሳምንት ጨዋታ ውጤት በሚከተለው መልኩ ተጠናቋል፡-
4:40 ሰዓት - መቻል 54 Vs 27 ከምባታ ዱራሜ
5:40 ሰዓት - ኦሜድላ 28 Vs 34 ቂርቆስ ክፍለ ከተማ
ቀጣይ ፕሮግራም ቅዳሜ እረፍት በማድረግ እሁድ መጋቢት 20/2018 ሦስት ጨዋታዎች ሎጊታ ሜዳ ይካሄዳል።
እኛም እንደ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለዋሳዎች መጥተናል በሜዳ በመገኘት ስፖርቱን እንድትከታተሉ ጋብዘናል።
የኢትዮጵያ እጅ ኳስዐፌዴሬሽን