EvaSUE

EvaSUE EvaSUE is a fellowship of Students and Graduates who are dedicated to follow and witness Jesus Christ as Lord and Savior.

Evangelical Students' and Graduates' Union of Ethiopia is a ministry that serves University and College Evangelical Christian Student Fellowships.

ቃል ቅምሻ ፫ምነው እስራኤልን የሚያድን ከጽዮን በወጣ!እግዚአብሔር የሕዝቡን ምርኮ በሚመልስበት ጊዜ፣ያዕቆብ ደስ ይበለው፤ እስራኤልም ሐሤት ያድርግ።መዝሙር 14፥7እስራኤልን የሚያድን የሚመጣው...
30/05/2026

ቃል ቅምሻ ፫

ምነው እስራኤልን የሚያድን ከጽዮን በወጣ!
እግዚአብሔር የሕዝቡን ምርኮ በሚመልስበት ጊዜ፣
ያዕቆብ ደስ ይበለው፤ እስራኤልም ሐሤት ያድርግ።
መዝሙር 14፥7

እስራኤልን የሚያድን የሚመጣው ከጽዮን ነው ። ጽዮን የአዳኙ መገኛ ነው ። ለጽዮን ከተሰጡ ትርጉሞች ሁሉ በዚህ ክፍል የተገለጸው "ጽዮን " የእግዚአብሔርን ሰማያዊ መንግሥት ይገልጻል ።

እስራኤላዊያንን የሚያድን መምጫውም ሰማያዊ ከሆነው መንግሥቱ የሚመጣው እግዚአብሔር ነው ። ዛሬም ማዳኑ ለእስራኤል ብቻ ሳይሆን በምድር ላሉ የሰው ልጆች ሁሉ በክርስቶስ ኢየሱስ በኩል በመስቀሉ ታይቷል ። እግዚአብሔር ወልድ ጌታችን ኢየሱስ ፍጹም መለኮት ሲሆን ነገር ግን የባርያን መልክ በመያዝ ፤ ፍጹም ሰው ሆኖ ለመስቀል ሞት እንኳን በመታዘዝ ለሰው ልጆች የማዳን ሥራውን ገልጧል ። መልአኩም ለዮሴፍ በሕልም ተገልጦ ሕዝቡን ከኃጢአታቸው ያድናቸዋልና ስሙን "ኢየሱስ "ብለህ ትጠራዋለህ ። "ማለቱ ምነኛ ድንቅ ብስራት ሆኖት ይሆን ?!

ምነው ሕዝቡን የሚያድን ከጽዮን በመጣ "በሚያስበል የኃጢአት ባርነት ተገዝተን ለኖርን ድኩማን የአዳኙ መገለጥ ምነኛስ ደስ ሚያስኝ ዜና ይኾን! በርግጥ ከዚህ የሚልቅ ደስታ የለም ። ዘማሪው እስራኤልን የሚያድን መስፍን የፈለገው ከጽዮን እንጂ ከሌላ ሥፍራ አልነበረምና እኛም የሚያድነውን መስፍን ከጽዮን ከላይ ከሰማይ እንሻ ።

በሌላ መዝሙር ላይ "ዐይኖቼን ወደ ተራሮች አነሣሁ ፣ ረዳቴ ከወዴት ይምጣ ፤ ረዳቴ ሰማይና ምድርን ከፈጠረ ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው ። "እንዳለ ዐይናችንን ሊከልልለን ከሚችለው ተራራ ይልቅ የሁለ ፈጣሪና ጌታ የሆነው አምላካችን እግዚአብሔር ላይ እናድርግ ። ረድኤት ማዳን ያለው ከርሱ ዘንድ ነውና ። የማዳን ሥራውን በተግባር ሲገልጥ የሕዝቡን ምርኮ መመለስ መገለጫው ነው ።

የሕዝቡ ምርኮ መመለስ የተነፈገውን ነጻነትና መብት መልሶ መጎናጸፉ ነው ። ምክንያቱም የባርነት መገለጫው ነጻነትና መብትን መነፈግ ነው ። የሚያድነው ንጉሥ ሲመጣ ፤ ከባርነት ዋጅቶ ነጻነትና መብትን ለሕዝቡ ይሰጣል ። ይህም በክርስቶስ ለሚያምን ሁሉ ሆኗል ደግሞም ይሆናል ።

የእስራኤል ልጆች በእውነተኛ ደስታ የሚመሉትና ሐሤት ሚያደርጉት ፤ ማዳን ከጽዮን ሲመጣ ፣ ምርኮንም ከጽዮን የሚመጣው እግዚአብሔር ሲመልስላቸው ነው ። እውነተኛ ሐሤትና ደስታ የእግዚአብሔር ሕዝብ የሚያገኘው በእግዚአብሔር እና ከእግዚአብሔር በሚሆን ነገር ነው ።

እግዚአብሔርን እና ከእግዚአብሔር ዘንድ የሆነውን በመሻት እንድንኖር ጸጋው ይብዛልን !!

✍️ጌታሁን አያኖ

በራልንእግዜሩ ጋር ንክኪ ያለው ሰው አቤት መታደሉ። ከክንፉ ጥላ ስር ተሸሽጎ በጥበቃው ልቡ አርፎ ይኖራል። ከመረጃ ባለፈ በተጨባጭ ሁኔታ በሒወቱ እውን ለሆነለት አምላክ ፈቃዱን አስገዝቶ ይኖ...
23/05/2026

በራልን

እግዜሩ ጋር ንክኪ ያለው ሰው አቤት መታደሉ። ከክንፉ ጥላ ስር ተሸሽጎ በጥበቃው ልቡ አርፎ ይኖራል። ከመረጃ ባለፈ በተጨባጭ ሁኔታ በሒወቱ እውን ለሆነለት አምላክ ፈቃዱን አስገዝቶ ይኖራል። እግዚአብሔር ራሱን ካልገለጠልን በስተቀር በራሳችን ጥረት ልንደርስበት አንችልም ፤ በሰው ቀመር እና ስሌት አይገኝም ፤ በሰው የአዕምሮ ልህቀት ታስሶ አይደረስበትም። ታዲያ ይህ ረቂቅ እና ምጡቅ አምላክ ራሱን ለሰው ልጆች መግለጥ በጎ ፈቃዱ ሆኖ በልጁ በክርስቶስ በኩል መልኩን፣ ባህሪውን እና ማንነቱን አሳየን። እግዚአብሔር ተገለጠልን በራልን። እርሱን ማወቅ የዘላለም ህይወት ነው። ከእርሱ ጋር ተጣብቆ መኖር የህይወት ትርጉም ነው። ከእርሱ ጋር መወዳጀት የእረፍት አለም ነው። እርሱን ማመን ልብን የሚያረጋ መልህቅ ነው። ታዲያ እግዜሩን ከመረጃ ባለፈ በህይወታችን እውን ይሆንልን ዘንድ ይበራልን ዘንድ የግድ ያስፈልጋል። እንዲበራልን ይበልጡን እንድናውቀው እና እንድንረዳው ደግሞ ወደእርሱ ቀርበን ልንለምነው በፀሎት እንማፀነው ዘንድ ይገባል፤ እንዲሁ በአዕምሮ የምናውቃቸውን የእግዚአብሔር ቃል እውነቶች መተግበር ይገባናል ። ከትላንቱ ዛሬ ፤ ከዛሬ ደግሞ ነገ እግዚአብሔርን በማወቅ ህይወት እንዲሁም በእውነተኛ መረዳት እና ግንዛቤ እያወቅነው እንኖር ዘንድ ፀጋ ይብዛልን

✍ ካሌብ ካሳሁን

ቃል ጸሎትእንደ ዐይንህ ብሌን ጠብቀኝ፤በክንፎችህም ጥላ ሰውረኝ፤መዝሙር 17፥8አቤቱ ጠብቀኝ ! ትድግናህ የሚያሻኝ ድኩም ፣ ጠብቆትህ የሚያስፈልገኝ ፣ ለአውሬ ለሌባ ተጋላጫ የሆንኹ በግ ፣ ከ...
16/05/2026

ቃል ጸሎት

እንደ ዐይንህ ብሌን ጠብቀኝ፤
በክንፎችህም ጥላ ሰውረኝ፤
መዝሙር 17፥8

አቤቱ ጠብቀኝ ! ትድግናህ የሚያሻኝ ድኩም ፣ ጠብቆትህ የሚያስፈልገኝ ፣ ለአውሬ ለሌባ ተጋላጫ የሆንኹ በግ ፣ ከለላህ የሚያኖረኝ ልል ፣ ማዳናህ ሚፈውሰኝ ሕማም ፣ እጅህ የሚመራኝ ተጓዝ ፣ ቃልህ የሚያጸናኝ ወላዋይ ነኝና እንደ ዐይንህ ብሌን ጠብቀኝ ።

የዐይንን ብሌን ከራስ በታች ከሌላው የሰውነት ክፍል ሁሉ ከፍ አድርገህ ፥ በማበጀት ከብዙ ጥፋት እንዲጠበቅ እንዳደረግህ ፤ ከዚህ ዓለም ክፋት እና ነውር በላይ በጽድቅህ ከፍታ እግሮቼን እንድታጸና እማጸንሃለሁ ። የዐይንን ብሌን በተከለለ ሥፍራ እንዳኖርከው አቤቱ ባርያህንም በእቅፍህ እንድታኖረኝ አሻለሁ ።

ንስር ጫጩቶቿን በክንፎቿ ሰውራ ከውጩ ብርድ ሙቀትን እንደምትቸር ፣ ከፀሓዩም ከልላ ጥላ እንድምትሆነው ፣ ከዝናብ ከውርጭ ሸሽጋ በጉያዋ እንደምታሳርፍ አቤቱ ልጅህ ነኝና ከዚህ ዓለም ዐመጽ እና ነውር እንዲሁም ክፋት ሁሉ በክንፎችህ ሰውረኝ ።

አምላክ ሆይ፤ ስለምትመልስልኝ ስምህን በመጥራት ልመናዬን አቅርቤያለሁና ስማኝ ። በእረኝነትህ እስከፍጻሜው አኑረኝ ፣ ለዘላለሙ አሜን !!

✍️ጌታሁን አያኖ

በመታመንበየዕለት ህይወታችን ላይ እምነት (መታመን) የሚባለው ነገር የዘወትር ተግባራችንን የያዘ ነው። ለምሳሌ የተቀመጥንበት ወንበር እንደማይጥለን ስለምናምን ያለሀሳብ ዘና ብለን እንቀመጥበታ...
09/05/2026

በመታመን

በየዕለት ህይወታችን ላይ እምነት (መታመን) የሚባለው ነገር የዘወትር ተግባራችንን የያዘ ነው። ለምሳሌ የተቀመጥንበት ወንበር እንደማይጥለን ስለምናምን ያለሀሳብ ዘና ብለን እንቀመጥበታለን። እግዚአብሔር በማንነቱ ታማኝ ስለሆነ በሙሉ ልባችን በእርሱ ላይ እንድንታመን ይፈልጋል። እግዚአብሔርን አምነዋለሁ( መታመኛየ ነው) ማለት ሒወቴን እንድመራበት የሰጠኝ መመሪያ በሰው አይን የሚያዋጣ ባይመስልም ነገር ግን እሱ ለእኔ መልካም የሆነውን ስለሚያስብ ያንን ጎዳና ልጓዝበት ወስኛለሁ ማለት ነው። እግዚአብሔር የመረጠልኝን መንገድ በመከተሌ እንደከሰርኩ ያህል እንዲሰማኝ የሚያደርጉ ድምፆች በዙሪያየ ቢያንባርቁም መንገዱን መጓዝ ግን እቀጥላለሁ ማለት ነው። እሱን በመጠበቄ ጊዜየ እንዳረፈደብኝ ቢሰማኝም በራሴ አካሄድ ቅልጥፍጥፍ ብል ከማገኘው እስማኤል በላይ ጊዜው ያለፈ በሚመስል ወቅት የሚሰጠኝን ይስሀቅን እጠብቃለሁ ማለት ነው። በእግዚአብሔር እታመናለሁ ማለት በራሴ ማስተዋል አልደገፍም ፤ ያገኘሁትን መልካም የሚመስል አጋጣሚ በጠቅላላ ፈቃዱን ሳላረጋግጥ አልጠቀምም ማለት ነው ። ለእግዜሩ ወገንተኛ ሆኜ ከማጣቸው እድሎች በላይ እሱ በራሱ ጊዜ የእሱ ፈቃድ ያለበትን በር ይከፍትልኛል ማለት ነው ባይከፍትልኝም እንኳ እሱ የታመነ አምላክ ነው ብሎ ልብን በእግዚአብሔር ሀሳብ ማፅናት ነው። ቢታመኑት የሚያስታምን ፤ አደራ የማይበላ ፤ ባለመታመን ተከሶ የማያውቅ የፀና ታማኝ አምላክ የሚያደላድል አለት ኢየሱስ ክርስቶስ አለ። ይሄ ጌታ ለላቀው ለዘላለም ሒወት በመስቀል ላይ እስከመሞት የታመነልን አምላክ ነውና ለምድሩ አይጠረጠርም። ለሰማይ ወፎች የሚያስብ ጌታ ለልጆቹማ እንዴት የበለጠ አያስብም?
ልባችን በእርሱ እንዲታመንልን ጌታ ፀጋውን ያብዛልን

✍ ካሌብ ካሳሁን

ቃል ቅምሻእኔ ግን በጸናች ፍቅርህ እታመናለሁ፤ልቤም በማዳንህ ደስ ይለዋል።ቸርነቱ በዝቶልኛልና፣ለእግዚአብሔር እዘምራለሁ።መዝሙር 13፥5-6መታመኛ ሚሆን የጸና ፍቅር የእግዚአብሔር ፍቅር ብቻ ...
02/05/2026

ቃል ቅምሻ

እኔ ግን በጸናች ፍቅርህ እታመናለሁ፤
ልቤም በማዳንህ ደስ ይለዋል።
ቸርነቱ በዝቶልኛልና፣
ለእግዚአብሔር እዘምራለሁ።
መዝሙር 13፥5-6

መታመኛ ሚሆን የጸና ፍቅር የእግዚአብሔር ፍቅር ብቻ ነው ። ፍቅረ እግዚአብሔር መወላወል የሌለበት ፣ ማይናወጽ ፣ ወለም ዘለም ማይል ፣ ወረት ማያወቀው ጽኑ ፍቅር ነው ። ፍቅር ለአምላካችን እግዚአብሔር ባህሪው ብቻ ሳይሆን ስሙ ነው ፤ መገለጫው ብቻ ሳይሆን ማንነቱም ነው ።" እግዚአብሔር በማንነቱ ፍቅር በመሆኑ ሌሎችን የሚያፈቅርበት ፍቅር የሚመነጨው ከራሱ ከማንነቱ ነው ። እግዚአብሔር የዘላለማዊ ፍቅር አንድነት ነው ማለት ነው ።ከዘላለምም እንዲሁ ነበረ ። ዓለምን የወደደበት ፍቅርም እርሱ ራሱ ነው ። "¹ እግዚአብሔር ዓለምን የወደደበትን ፍቅር በክርስቶስ በኩል ለዓለም ገልጧል ።

የፍቅር ትርጉሙም ሌላ ዐይደለም ። "እርሱ ስለ እኛ ነፍሱን አሳልፎ ሰጥቶአልና በዚህ ፍቅርን አውቀናል፤ እኛም ስለ ወንድሞቻችን ነፍሳችንን አሳልፈን እንድንሰጥ ይገባናል።( 1 ዮሐንስ 3:16) "ፍቅር ይህ ነው፤ እኛ እግዚአብሔርን እንደ ወደድነው ሳይሆን እርሱ እንደ ወደደንና ስለ ኀጢአታችን ማስተስረያ ይሆን ዘንድ ልጁን መላኩ ነው።(1 ዮሐንስ 4፥10) " ስለዚህ ፍቅርን ያወቅነው በክርስቶስ መስቀል ነው ፤ ይህም እግዚአብሔርን ይገልጣል ። እግዚአብሔር የሚገኘው የክርስቶስ መስቀል ዘንድ ነውና ።የእግዚአብሔር ፍቅር በአካል ሲገለጥ ለማየት ፣ ኢየሱስን መመልከት ... "² ብቻውን በቂ ነው ።

እግዚአብሔር ጽኑ የሆነውን ፍቅር ፣ አንድያ ልጁ በመስጠት ገለጦልናልና እኛም ነፍሳችንን ፣ ለርሱ እና ለወዳጆቻችን በመስጠት ይህን ፍቅር ልንገልጥ ይገባናል ። ከመግለጥ በፊት ግን ፍቅሩን መረዳት እና በፍቅሩ መታመን ይቀድማል ። ፍቅሩን የተረዳ ፣ በፍቅሩ ይታመናል ።

መታመን መኖርን ያስከትላልና ፣ በፍቅሩ የሚታመን መኖር አይከብደውም ። በክርስቶስ በኩል በተገለጠው ጽኑ ፍቅር መታመን ክርስቲያናዊ ሕይወት መገለጫ በመሆኑ ፤ ሠርክ ማልደን እንደዘማሪው በአንደበታችን " እኔ ግን በጽኑ ፍቅር እታመናለሁ !" እንድንል እንጋበዛለን ። ልባችንንም በማዳን ሥራው ደስ ይሰኝ ።

ልብን ደስ ሚያሰኝ ሌላ ነገር በመሻት አንዛል ፤ ማዳኑን በማሰብ ብቻ በደስታ እንደንሞላ እንሻ ። የበዛውን ዘላለማዊ ቸርነቱን እያወጠነጠንን ኹለንተናችንን ሕያው እና ቅዱስ መሥዋዕት በማድረግ በእውነትና በመንፈስ ለእግዚአብሔር ዝማሬን እናቅርብ ።

✍️ጌታሁን አያኖ
____
1)ጳውሎስ ፍቃዱ የእግዚአብሔር ልጅ ገጽ 32 - 43
2)

ዘፍጥረት || መግቢያ  || ዘለለው አርጋው
01/05/2026

ዘፍጥረት || መግቢያ || ዘለለው አርጋው

1 like. "ዘፍጥረት || መግቢያ || ዘለለው አርጋው"

በፅድቅ ኑሮየሰው ልጅ በዚህ ምድር ሲኖር ሒወትን ቀለል አድርጎ ለመኖር ይፈልጋል። ከዚህም የተነሳ ሊደርስ ካሰበበት ቦታ ለመድረስ ትክክለኛውን ረጅሙን እና ዋጋ የሚያስከፍለውን መንገድ ትቶ አ...
29/04/2026

በፅድቅ ኑሮ

የሰው ልጅ በዚህ ምድር ሲኖር ሒወትን ቀለል አድርጎ ለመኖር ይፈልጋል። ከዚህም የተነሳ ሊደርስ ካሰበበት ቦታ ለመድረስ ትክክለኛውን ረጅሙን እና ዋጋ የሚያስከፍለውን መንገድ ትቶ አቋራጭ መንገዶችን ፤ የእጥፍ ጥልጥፍ አካሄዶችን በመምረጥ ይጓዛል። እግዜሩ ያስቀመጠው የአኗኗር መርህን ለመከተል ትግል ይሆንበታል ምክንያቱስ ቢባል "በፍየል ዘመን በግ አትሁን" የሚለው የዚህች ምድር ብሒል ውስጥ ውስጡን ሰርስሮት ገብቷል። ከዚህም የተነሳ መጓዝ በሚገባው የሒወት መንገድ ላይ የማይገባ አካሄድን መንገድ ቀይሶ ለመንጎድ ሲታትር ይስተዋላል። እግዜሩ ደግሞ ፆድቅ አምላክ ነውና ከእኛ የፅድቅን ኑሮ ይፈልጋል። እግዚአብሔር ነገሮቻችንን በእጃችን እንዳስገባን ብቻ ሳይሆን እነዚያን ስኬቶቻችንን ለማግኘት የሄድንባቸውን መንገዶችም ጭምር ይመዝናቸዋል። እግዚአብሔር የውጤት ብቻ ሳይሆን የሒደትም አምላክ ነው። እግዚአብሔርን በማያከብር መንገድ ሄደን ከምናገኘው ትርፍ ይልቅ በእግዚአብሔር መንገድ ተጉዘን የምናገኘው ጥቂት ነገር ዋጋ አለው። አጠገባችን የሚገኙ ሰዎች ሳያጠኑ ከሌላ ተማሪ ኮርጀው ጥሩ ውጤት ቢያመጡ ፤ ጉቦ ተቀብለው ኑሮአቸውን ቢያስተካክሉ ፤ ዝምድናን ተጠቅመው ስልጣንን ቢይዙ ፤ ውጭ ሀገር ለመሄድ የሀሰት ትዳር ቢመሠርቱ... እግዚአብሔር የፃድቃንን መንገድ ስለሚያውቅ የክፋዎችን ለሚያውቅ የክፋዎች መንገድ መጥፋቱ አይቀርም። እግዚአብሔር ሊያጠፋው እና ነፋስ ጠርጎ እንዲወስደው በወሰነው ከክፋ መንገድ መመለስ ሁነኛ መፍትሄ ነው። እግዚአብሔር ፃድቅ አምላክ ስለሆነ ከእኛም የፅድቅን ኑሮ(የእሱን መርህ እየተከተሉ እንድንኖር) ይፈልጋል ዋጋ ቢያስከፍልም ምክንያቱም መስቀልን መሸከም ይሄ ስለሆነ። ጌታ ፀጋውን ያብዛልን

✍️ ካሌብ ካሳሁን

Address

Queen Elizabeth II
Addis Ababa
34354

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when EvaSUE posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share