Ethiopian Muslim Youth Council

Ethiopian Muslim Youth Council Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Ethiopian Muslim Youth Council, Youth Organization, Torhailoch, Addis Ababa.

በእስልምና አስኳል አሰተምህሮ ላይ የተመሠረተ፣ በዒባዳ የታነፀ፣ ማንነትና እሴቱን የሚያከብር፣ ለህዝብ ደኅንነትና ለሀገር ልማት አስተዋፆ የሚያደርግ፣በእምነት፣ እውቀትና በአገልግሎት መሪ የሆነ ወጣት ትውልድ ማፍራትን እንዲሁም ኢትዮጵያውያን ሙስሊም ወጣቶችን በአንድ ጥላ ስር መሰብሰብ ርዕዩ አድርጎ በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ስር ተቋቋመ ቦርድ መር የወጣት አደረጃጀት ነው።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል በይፋ ተመሰረተ።EMYC || ሚያዝያ 25፤ 2018የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምስረታ መርሃግብር በአርባ ምንጭ...
03/05/2026

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል በይፋ ተመሰረተ።

EMYC || ሚያዝያ 25፤ 2018

የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምስረታ መርሃግብር በአርባ ምንጭ ከተማ ላይ በደመቀ ሁኔታ ተካሄደ።

በዚህ ታሪካዊ የምስረታ በዓል ላይ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ፣ የካውንስሉ ፕሬዚዳንት ኡስታዝ ሐይደር ከድር፣ የካውንስሉ ዋና ጸሐፊ ኢ/ር ከማል አረብ፣ የክልሉ መጅሊስ አመራሮች፣ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

በዕለቱ የክልሉ ወጣቶች ካውንስል አመራሮች የተመረጡ ሲሆን፣ ምስረታው በክልሉ የሚገኙ ሙስሊም ወጣቶችን ተሳትፎና ተቋማዊ አንድነት ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግራል ተብሎ ይታመናል።

የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል

ታሪካዊው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ምስረታ በነገው ዕለት በአርባ ምንጭ ከተማ ይከናወናል!EMYC || 2018 ዓ.ል​የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል የወጣቱን ተሳት...
02/05/2026

ታሪካዊው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ምስረታ በነገው ዕለት በአርባ ምንጭ ከተማ ይከናወናል!

EMYC || 2018 ዓ.ል

​የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል የወጣቱን ተሳትፎ ለማሳደግና ተቋማዊ አደረጃጀቱን ለማጠናከር የሚያደርገውን ጉዞ በመቀጠል፣ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ይፋዊ የምስረታ መርሃ ግብር ነገ ሚያዝያ 25 ቀን 2018 ዓ.ል በአርባ ምንጭ ከተማ በደመቀ ሁኔታ እንደሚካሄድ በደስታ እንገልጻለን።

​ይህን ታላቅና ታሪካዊ ምስረታ በበላይነት ለመምራትና ለመታደም፡-
​የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ክቡር ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ፣ ​የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ፕሬዚዳንት ኡስታዝ ሐይደር ከድር፣ የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ዋና ጸሐፊ ኢ/ር ከማል አረብ እንዲሁም ሌሎች ከፍተኛ ብሔራዊና ክልላዊ አመራሮች በዛሬው ዕለት አርባ ምንጭ ከተማ ገብተዋል።

​ልዑኩ አርባ ምንጭ አየር ማረፊያ ሲደርስ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ የመጅሊስ አመራሮች፣ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች እና የከተማዋ ሙስሊም ወጣቶችና ነዋሪዎች በተገኙበት እጅግ ደማቅና ወንድማማችነት የተሞላበት አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
​ይህ ምስረታ በክልሉ የሚገኙ ሙስሊም ወጣቶች በአንድነት እንዲቆሙ፣ ለሀገር ግንባታና ለዲናዊ ተልዕኮ ስኬት በንቃት እንዲሳተፉ ትልቅ በር የሚከፍት ነው። የነገውን የክልሉን ወጣቶች የለውጥ ጉዞ በዝርዝር መከታተል እንድትችሉ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

​ሚያዝያ 24 ቀን 2018 ዓ.ል
አርባ ምንጭ፣ ኢትዮጵያ
​የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል

የኢትዬጲያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል የአባልት ምዝገባ ተጠናክሮ ቀጥሏል!የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል የጀመረው  የአባላት ምዝገባ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ተጠናክሮ ቀጥሏል። በዛሬው ...
23/04/2026

የኢትዬጲያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል የአባልት ምዝገባ ተጠናክሮ ቀጥሏል!

የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል የጀመረው የአባላት ምዝገባ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ተጠናክሮ ቀጥሏል። በዛሬው ዕለትም የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዩች ጠቅላይ ም/ቤት የዲያስፖራ ዘርፍ ሃላፊ ሼኽ መሀመድ አህመድ ያሲን፣ የአፋር ክልል እስልምና ጉዳዩች ጠቅላይ ም/ቤት ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር መሀመድ ሁሴን፣በኢትዮጵያ ሙስሊም ካውንሰል የአፋር ቅርንጫፍ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሰዒድ ዓሊ ሀሩንና የኢትዮጵያ ሙስሊም ካውንሰል ዋና ፅ/ቤት ባለሞያዎች በተገኙበት የአፋር ክልል የአባላት ምዝገባ በይፋ ተጀምሯል። ይህ የአፋር ክልል የካውንስሉ የአባላት ምዝገባ በተጀመረ በ5 ሰዓታት ውስጥ በኦንላይን ብቻ ከ1120 በላይ አባላት ተመዝግበዋል። ይህም የካውንስሉን ህዝባዊ ቅቡልነት እንዲሁም የአፋር ክልል ሙስሊም ወጣቶቻችን ንቃተ እና ያላቸውን ተስፋ አመላካች ነው።

የኢትዬጲያ ሙስሊም ወጣቶችን መንፈሳዊ ልህቀት ለማሳደግ እና ሁለንተናዊ አቅም ለመገንባት ጥረት እያደረገ የሚገኘው የኢትዬጲያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል በአርሲ ዞን አሰላ ከተማ ደማቅ የአባላት...
19/04/2026

የኢትዬጲያ ሙስሊም ወጣቶችን መንፈሳዊ ልህቀት ለማሳደግ እና ሁለንተናዊ አቅም ለመገንባት ጥረት እያደረገ የሚገኘው የኢትዬጲያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል በአርሲ ዞን አሰላ ከተማ ደማቅ የአባላት ምዝገባ ማብሰሪያ ዝግጅት አድርጓል። ይህ የአባላት ምዝገባ ወጣቶች በመደበኛና ህጋዊ አደረጃጀት ስር ራሳቸውን ከማጎልበት ባሻገር ማህበራዊ ሃላፊነታቸውን የሚወጡበትን ምህዳር የሚፈጥር ነው። ወጣቶች ከመስጂድ ጀምሮ ባሉ መንፈሳዊና ማህበራዊ ተቋምት ጠንካራ ተሳትፎ እያደረጉ የሚገኝ ሲሆን ይህን ተሳትፎና ተሞክሮ በማሳደግና በአንድ ተቋም ጥላ ስር በማድረግ አበርክቷቸውን ማጎልብት ይችላል። የኢትዬጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል የአባላት ምዝገባ ሂደት የተቋሙን ህዝባዊ መስረትና ቅቡልነት የሚያሳድግ ሲሆን ለወጣቶችም የእድል በሮችን የሚከፍት ነው።

የሀገራችን አብዘሀኛው ዜጋ ወጣት መሆኑ ትልቅ ሀገራዊ ሀብትና እድል ነው። ይህን ሀብትና እድል በአግባቡ ለመጠቀም የወጣቶች በመደበኛና ህጋዊ ተቋማት መደራጀት አስፈልጎቱ የጎላ ነው። ይህን ተጨባጭ በመመርኮዝ የኢትዬጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል በወርሀ ረመዳን ሀገር አቀፍ የአባላት ምዝገባ ማስጀመሩ ይታወሳል። ይህ የአባላት ምዝገባ በተለያዩ የሀገራችን ክፍል እየተከናወነ ሲሆን በዛሬው ዕለትም በአርሲ ዞን አሰላ ከተማ በመገኘት በአካባቢው የአባላት ምዝገባ ማስጀመሪያ መርሀ ግብር አከናውኗል። በዚህ መርሀ ግብር የካውንሰሉ ፕሬዝዳንት ኡስታዝ ሀይደር ኸድር፣ የካውንስሉ ዋና ጸሀፊ ኡስታዝ ከማል አረብ፣ የካወንስሉ ስራ አስኪያጅ አብዱራህማን መሀመድ (ዶር)፣ ካፒቴን ሱፍያን ዑስማን፣ ዑለማዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

በርካታ ተሳታፊዎች በተገኙበት በዚ የአባላት ምዝገባ ማስጀመሪያ መርሀ ግብር ላይ ሙሀደራና በካውንስሉ አመራሮች የተለያዩ መልዕክቶች የተላለፉ ሲሆን የካውንስሉ አባል የመሆን ከፍተኛ መነቃቃትና ተነሳሽነት መፍጠር ተችሏል። በአካባቢው እጅግ የተከበሩት ታላቁ አሊም ሽኽ አብዱልከሪም ሽኽ በሽር የካውንስሉ የክብር አባል በመሆኑ የአባልነት መርሀ ግብሩን በይፋ የተቀላቀሉ ሲሆን የመደበኛና የተቋማዊ አባላት ምዝገባ በይፋ ተከናውኗል።

የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል የስራ አስኪያጅ ሹመት ሰጠ!የኢትዮጵያ መስሊም ወጣቶች ካውስል  በኢስላማዊ  ሰነ ምግባር የታነፁ፣ ራሳቸውን፣ ማህበረሰባቸውንና ሀገራቸንን  በተሳመሩበት ዘ...
16/04/2026

የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል የስራ አስኪያጅ ሹመት ሰጠ!

የኢትዮጵያ መስሊም ወጣቶች ካውስል በኢስላማዊ ሰነ ምግባር የታነፁ፣ ራሳቸውን፣ ማህበረሰባቸውንና ሀገራቸንን በተሳመሩበት ዘርፍ በቅንነት በማገልገል ኃላፊታቸውን የሚወጡ ወጣቶችን የማፍራት አላማውን ለማሳካት ሰፊ እንቅስቃሴ እያደረገ ይገኛል።

ይህን ትልቅ መንፈሳዊ፣ ሀገራዊና ህዝባዊ አደራ (አማና)በአላህ እገዛ እንዲወጡ የትምህርት ዝግጅታቸውንና ልምዳቸውን መሰረት በማድረግ ለዶክተር አብዱራህማን መሀመድ የኢትዮጵያ መስሊም ወጣቶች ካውንስል ስራ አስኪያጅ ሆነው በኃላፊነት እንዲያገለግሉ ሹመት ተስጥቷል።

የካውስሉ ስራ አስፈጻሚ ቦርድ ለዚህ ትልቅ ሃላፊነት ለተሾሙት ለአብዱራህማን መሀመድ (ዶ/ር) የአላህ (ሱወ) እገዛ እንዳይለያቸው እና ውጤታማ የሥራ ጊዜ እንዲኖራቸው መልካም ምኞቱን ይገልፃል።

Ethiopian Muslim Youth Council
12/04/2026

Ethiopian Muslim Youth Council

የአክሱም ሙስሊሞች ሰብዐዊና ህገ መንግስታዊ መብቶች እንዲከበር ተጠየቀ!በምዕራብ ወለጋ ዞን ቆንዳላ ከተማ ታላቅ የዳዕዋ እና የቁርዐን ሂፍዝ ተማሪዎች ምርቃት መርሃ ግብር በዛሬው ዕለት የተከ...
12/04/2026

የአክሱም ሙስሊሞች ሰብዐዊና ህገ መንግስታዊ መብቶች እንዲከበር ተጠየቀ!

በምዕራብ ወለጋ ዞን ቆንዳላ ከተማ
ታላቅ የዳዕዋ እና የቁርዐን ሂፍዝ ተማሪዎች ምርቃት መርሃ ግብር በዛሬው ዕለት የተከበሩ አሊሞችና የመጅሊስ አመራሮች፣ ታዋቂ ዱዐቶች፣ የማህበረሰብ መሪዎች እና የክብር እንግዶች በተገኙበት በሺዎች በሚቆጠሩ የአካባቢው ነዋሪዎች ደምቆ ውበ በሆነ መልኩ ተከናውኗል።

የምዕራብ ወለጋ ዞን ሙስሊም ማህበረሰብ በነቂስ በመውጣት የክብር እንግዳው የሆኑትን የዲን መምህሮቹን ልዩ በሆነ ክብርና ሞገሰ አጅቦ የተቀበለ ሲሆን፤ መርሀ ግብሩ በቁርዐን የተዋበ፣ የአንድነት ፋናው የጎላ፣ በአክሱም ለሚገኙ ሙስሊም ወገኖቹ የአጋርነት መልዕክት የተሰተጋባበት መድረክ እንዲሆን አድርጓል።

በዚህ በሺዎች የሚቆጠሩ የቁርዐን ወዳጆች በተገኙበት በዚህ መድረክ ከ1400 አመታት በፊት የእምነት ነፃነታቸው በአምባገነኖች በመገፈፉ ምክኒያት ፍትህን ፍለጋ ለተሰደዱ ከለላ በሆነው ፍትሀዊ መሪ ስትመራ በነበረችው አክሱም ዛሬ የህዝባቸውን ሰብዐዊና ህገ መንግስታዊ የሆነውን የእምነት ነፃነት የሚጋፉ በዳዬችን በማውገዝ ለወገኖቻችን የአጋርነት ድምፅ መሆን ተችሏል።

በመድረኩም ሀገራችን ብዘሀ ሀይማኖት እንደመሆኗ ሰብዐዊና ህጋዊ የሆኑ የሀይማኖት ነፃነቶችን ማክበር የጋራ ሰላማችንን የምናሰጠብቅበት ብቸኛ አማራጭ መሆኑ ተገልጿል። የአክሱም ሙስሊሞች ዘመናት የተሻገረ ጥያቄ ምላሽ ተነፍጎ ባለበት ተጨባጭም መሰል ጥቃቶችን መደረብ አብሮነትን የሚያቃቅርና ለዘላቂ ሰላም እንቅፋት የሚሆን ትንኮሳ ነው። የዜጎችን ሰብዐዊና ህገ መንግስታዊ መብት ማክበር የአብሮነት እሴት ሲሆን በአንድ ሀገርና በአንድ አካባቢ ለሚኖሩ ዜጎች ደግሞ የማህበራዊ ትስስራቸው መሰረት ነው።

በዚህ አጋጣሚ በአክሱም አካባቢ ሙስሊሞች ላይ የሚፈፀሙ የተለያየ መልክ ያላቸው ጥቃቶች በህግም፣ በሀይማኖትም ሆነ በሞራል ውግዝ የሆኑ ተግባራት መሆናቸው አፅንዖት ሊሰጠው ይገባል። እነዚህን ውግዝ ተግባራት ለማሰቆም የአካባቢው አሰተዳደሮች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና የሀይማኖት አባቶች ሁሉም በየፊናው ከማህበረሰቡ ጎን በመቆም ሀላፊነቱን ይወጣ ዘንድ የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ፕሬዝዳንት ኡስታዝ ሀይደር ኸድር ጥሪያቸውን አቅርበዋል።

በመላው አለም ለምትገኙ ሙስሊሞች እንኳን ለ 1447ተኛው ኢድ አል-ፊጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ፣ በዓሉ የመተዛዘን፣ የመረዳዳት እና የደስታ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ። የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣ...
20/03/2026

በመላው አለም ለምትገኙ ሙስሊሞች እንኳን ለ 1447ተኛው ኢድ አል-ፊጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ፣ በዓሉ የመተዛዘን፣ የመረዳዳት እና የደስታ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ።

የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ፕሬዝዳንት ኡስታዝ ሀይደር ከድር

የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች የደስታ ኢድ አል-ፊጥር እንዲሆንላችሁ ይመኛል። ኢድ ሙባረክ!
19/03/2026

የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች የደስታ ኢድ አል-ፊጥር እንዲሆንላችሁ ይመኛል።

ኢድ ሙባረክ!

የታላቁ ሀገራዊ የጎዳና ኢፍጠር በሞጆ ከተማ
16/03/2026

የታላቁ ሀገራዊ የጎዳና ኢፍጠር በሞጆ ከተማ

የሶማሌ ክልል ርእሰ መስተዳደር የተከበሩ ሙስጠፌ ሙሀመድ ኡመር፣ የሱማሌ ክልል ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል አመራሮች፣ የመጅሊስ አመራሮች እና ሌሎችም ባለ ድርሻ አካላት የተገኙበት ታላቁ የጎዳና...
15/03/2026

የሶማሌ ክልል ርእሰ መስተዳደር የተከበሩ ሙስጠፌ ሙሀመድ ኡመር፣ የሱማሌ ክልል ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል አመራሮች፣ የመጅሊስ አመራሮች እና ሌሎችም ባለ ድርሻ አካላት የተገኙበት ታላቁ የጎዳና ኢፍጣር በጅግጅጋ ከተማ።

Address

Torhailoch
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Muslim Youth Council posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Ethiopian Muslim Youth Council:

Share