03/05/2026
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል በይፋ ተመሰረተ።
EMYC || ሚያዝያ 25፤ 2018
የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምስረታ መርሃግብር በአርባ ምንጭ ከተማ ላይ በደመቀ ሁኔታ ተካሄደ።
በዚህ ታሪካዊ የምስረታ በዓል ላይ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ፣ የካውንስሉ ፕሬዚዳንት ኡስታዝ ሐይደር ከድር፣ የካውንስሉ ዋና ጸሐፊ ኢ/ር ከማል አረብ፣ የክልሉ መጅሊስ አመራሮች፣ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
በዕለቱ የክልሉ ወጣቶች ካውንስል አመራሮች የተመረጡ ሲሆን፣ ምስረታው በክልሉ የሚገኙ ሙስሊም ወጣቶችን ተሳትፎና ተቋማዊ አንድነት ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግራል ተብሎ ይታመናል።
የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል