19/03/2026
የቢላሉል ሐበሺ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ጀማል ሙሐመድ የዒድ አል-ፊጥር የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
************
የቢላሉል ሐበሺ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ጀማል ሙሐመድ የዒድ አል-ፊጥር በዓልን ምክንያት በማድረግ ለመላው ሙስሊም ማኅበረሰብ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። ዋና ሥራ አስኪያጁ በመልዕክታቸው፤ ቢላሉል ሐበሺ በተቀደሰው የረመዷን ወር ውስጥ ሰፊ የኢፍጧርና የአስቤዛ ድጋፎችን ለተገቢው የኅብረተሰብ ክፍሎች ሲያደርስ መቆየቱን አስታውሰዋል። በእነዚህ የበጎ አድራጎት ሥራዎች ላይ በገንዘብ፣ በሐሳብ፣ በትብብርና በተለያዩ መንገዶች ከጎናቸው ለነበሩ ደጋፊዎች በሙሉ የላቀ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
አቶ ጀማል አክለውም "ረመዷን ቢያልፍም የኸይር (የመልካም) ሥራ በሕይወት እስካለን ድረስ የማይቋረጥ ነው" በማለት፣ ደጋፊዎችና አጋሮች ድጋፋቸው እንዳይለያቸው ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል። ዒድ የመተሳሰብ፣ የመተዛዘንና የመከባበር በዓል መሆኑን የገለጹት ዋና ሥራ አስኪያጁ፤ ዕለቱ የተቸገሩ ወገኖቻችንን የምናስታውስበትና ከጎናቸው የምንቆምበት በመሆኑ ይህንን መልካም ተግባር እንዳንረሳው አሳስበዋል።
በድጋሚ ዒድ ሙባረክ!
ቢላሉል ሐበሺ - Bilalul Habeshi Community - ኑ ወደ ደግነት