ቢላሉል ሐበሺ - Bilalul Habeshi Community - ኑ ወደ ደግነት

ቢላሉል ሐበሺ - Bilalul Habeshi Community - ኑ ወደ ደግነት Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ቢላሉል ሐበሺ - Bilalul Habeshi Community - ኑ ወደ ደግነት, Charitable organisation, Addis Ababa.

''እኛ ከገንዘባችሁ በፊት ቀልባችሁን እና ማንነታችሁን እንፈልጋለን! ገንዘባችሁ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ላይኖር ስለሚችል ስለ ቀልባችሁ እንጨነቃለን። ምስኪኖች ግን በቅደሚያ ገንዘባችሁን ይፈልጋሉና አስታውሱዋቸው። አሏህ ﷻ እናንተን ያስታውሳችኃል ።''
(ኡስታዝ ሙሐመድ ጀማል ጎናፍር የቢላሉል ሐበሺ ዋና መስራችና የበላይ ጠባቂ )

የቢላሉል ሐበሺ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ጀማል ሙሐመድ የዒድ አል-ፊጥር የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ************የቢላሉል ሐበሺ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ጀማል ሙሐመድ የዒድ ...
19/03/2026

የቢላሉል ሐበሺ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ጀማል ሙሐመድ የዒድ አል-ፊጥር የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
************
የቢላሉል ሐበሺ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ጀማል ሙሐመድ የዒድ አል-ፊጥር በዓልን ምክንያት በማድረግ ለመላው ሙስሊም ማኅበረሰብ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። ዋና ሥራ አስኪያጁ በመልዕክታቸው፤ ቢላሉል ሐበሺ በተቀደሰው የረመዷን ወር ውስጥ ሰፊ የኢፍጧርና የአስቤዛ ድጋፎችን ለተገቢው የኅብረተሰብ ክፍሎች ሲያደርስ መቆየቱን አስታውሰዋል። በእነዚህ የበጎ አድራጎት ሥራዎች ላይ በገንዘብ፣ በሐሳብ፣ በትብብርና በተለያዩ መንገዶች ከጎናቸው ለነበሩ ደጋፊዎች በሙሉ የላቀ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

አቶ ጀማል አክለውም "ረመዷን ቢያልፍም የኸይር (የመልካም) ሥራ በሕይወት እስካለን ድረስ የማይቋረጥ ነው" በማለት፣ ደጋፊዎችና አጋሮች ድጋፋቸው እንዳይለያቸው ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል። ዒድ የመተሳሰብ፣ የመተዛዘንና የመከባበር በዓል መሆኑን የገለጹት ዋና ሥራ አስኪያጁ፤ ዕለቱ የተቸገሩ ወገኖቻችንን የምናስታውስበትና ከጎናቸው የምንቆምበት በመሆኑ ይህንን መልካም ተግባር እንዳንረሳው አሳስበዋል።

በድጋሚ ዒድ ሙባረክ!

ቢላሉል ሐበሺ - Bilalul Habeshi Community - ኑ ወደ ደግነት

ኢትዮ ቴሌኮም በቢላሉል ሐበሺ በአካል በመገኘት የዒድ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ*******የአገራችን የኮሙኒኬሽን ግዙፍ ተቋም የሆነው ኢትዮ ቴሌኮም፣ የዘንድሮውን የዒድ ...
19/03/2026

ኢትዮ ቴሌኮም በቢላሉል ሐበሺ በአካል በመገኘት የዒድ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ
*******
የአገራችን የኮሙኒኬሽን ግዙፍ ተቋም የሆነው ኢትዮ ቴሌኮም፣ የዘንድሮውን የዒድ አል-ፊጥር በዓል ምክንያት በማድረግ በቢላሉል ሐበሺ ዋና መሥሪያ ቤት በአካል በመገኘት ለመላው የቢላሉል ሐበሺ ቤተሰቦች፣ አባላትና ደጋፊዎች በሙሉ "ዒድ ሙባረክ" በማለት የመልካም ምኞት መግለጫውንና ልዩ አክብሮቱን አስተላልፏል።

የተቋሙ ተወካዮች በቦታው ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት፣ ኢትዮ ቴሌኮም ለቢላሉል ሐበሺ ለሚያከናውናቸው ሰብአዊና ማኅበራዊ ተግባራት ያለውን አጋርነት በድጋሚ አረጋግጠዋል። ይህ በአካል የተደረገው ጉብኝት በተቋማቱ መካከል ያለውን ጥልቅ ግኑኝነትና መከባበር ይበልጥ የሚያጠናክር ሲሆን፣ በዓሉ የሰላም፣ የፍቅርና የመረዳዳት እንዲሆንም ተቋሙ መልካም ምኞቱን ገልጿል።

በድጋሚ ዒድ ሙባረክ!
ቢላሉል ሐበሺ - Bilalul Habeshi Community - ኑ ወደ ደግነት

Ethio telecom

የብሉ ሆራይዘን እና የቢላሉል ሐበሺ የጋራ የኢፍጧር መርሃ-ግብር*****ብሉ ሆራይዘን (Blue Horizon) ከቢላሉል ሐበሺ ጋር በመተባበር በረመዳን ወር የተቸገሩ ወገኖችን ለመርዳት ያለመ ...
19/03/2026

የብሉ ሆራይዘን እና የቢላሉል ሐበሺ የጋራ የኢፍጧር መርሃ-ግብር
*****
ብሉ ሆራይዘን (Blue Horizon) ከቢላሉል ሐበሺ ጋር በመተባበር በረመዳን ወር የተቸገሩ ወገኖችን ለመርዳት ያለመ ታላቅ የጋራ የኢፍጧር መርሃ-ግብር በስኬት አከናውኗል።

ይህ በሁለቱ ተቋማት መካከል የተመሰረተው ጠንካራ አጋርነት፣ በረመዳን ወር የሚታየውን የመረዳዳት፣ የመተሳሰብና የመተጋገዝ እሴት በተግባር ለማዋል ታስቦ የተሰናዳ ነው። በመርሃ-ግብሩ ላይ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ለሚገኙ የማኅበረሰብ ክፍሎችና አቅመ ደካሞች የተሟላ የኢፍጧር ምግብና መጠጥ አቅርቦት የተደረገ ሲሆን፣ ይህም በምእመናኑ መካከል ያለውን ወንድማማችነት ይበልጥ ያጠናከረ ሆኖ ተገኝቷል።

የብሉ ሆራይዘንና የቢላሉል ሐበሺ አስተባባሪዎች እንደገለጹት፣ እንዲህ ዓይነት የሰብአዊ ድጋፍ ሥራዎች በረመዳን ወር ብቻ ሳይወሰኑ በቀጣይም በተለያዩ የማኅበራዊ አገልግሎት ዘርፎች ላይ ተጠናክረው የሚቀጥሉ ይሆናል።

ቢላሉል ሐበሺ - Bilalul Habeshi Community - ኑ ወደ ደግነት

የቨረኔል የእርዳታ ድርጅት እና ቢላሉል ሐበሺ የጋራ የኢፍጧር መርሃ-ግብር****በዓለም አቀፍ ደረጃ በሰብአዊ ድጋፍ ሥራዎች ላይ በስፋት የሚንቀሳቀሰው የቱርኩ ቨረኔል (Verenel) የረድኤት...
19/03/2026

የቨረኔል የእርዳታ ድርጅት እና ቢላሉል ሐበሺ የጋራ የኢፍጧር መርሃ-ግብር
****
በዓለም አቀፍ ደረጃ በሰብአዊ ድጋፍ ሥራዎች ላይ በስፋት የሚንቀሳቀሰው የቱርኩ ቨረኔል (Verenel) የረድኤት ድርጅት በኢትዮጵያ ከሚገኘው ቢላሉል ሐበሺ ጋር በመተባበር ታላቅ የጋራ የኢፍጧር መርሃ-ግብር አከናውኗል።

በነቭሼሂር (Nevşehir) ተወካዮች አስተባባሪነት የተዘጋጀው ይህ መርሃ-ግብር፣ በረመዳን ወር የሚታየውን የመረዳዳትና የመተሳሰብ እሴት በተግባር ለማሳየት ታስቦ የተሰናዳ ነው። በተለይም በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የማኅበረሰብ ክፍሎችንና ሕፃናትን ተጠቃሚ ባደረገው በዚህ ፕሮግራም ላይ፣ የተሟላ የኢፍጧር ምግብና መጠጥ አቅርቦት የተደረገ ሲሆን፣ ይህም በሁለቱ አገራትና በተቋማቱ መካከል ያለውን ጠንካራ የወንድማማችነት ትስስር ይበልጥ የሚያጠናክር ሆኖ ተገኝቷል።

ቢላሉል ሐበሺ - Bilalul Habeshi Community - ኑ ወደ ደግነት

የረመዷን መልዕክት 29ረመዷን ቢያልፍም ጌታችን ግን ሁሌም ህያው ነው። ነቢዩ (ﷺ) እንዳሉት፡ "አላህ ዘንድ የተወደደው ስራ ጥቂትም ቢሆን ዘላቂነት ያለው ነው።" የጀመርነውን በጎነት እንቀጥ...
19/03/2026

የረመዷን መልዕክት 29

ረመዷን ቢያልፍም ጌታችን ግን ሁሌም ህያው ነው። ነቢዩ (ﷺ) እንዳሉት፡ "አላህ ዘንድ የተወደደው ስራ ጥቂትም ቢሆን ዘላቂነት ያለው ነው።" የጀመርነውን በጎነት እንቀጥል! ዒድ ሙባረክ!

ኑ ወደ ደግነት!

"የጥበብ ስጦታ ለኢትዮጵያ ከፍታ" 17ኛው አዲስ የኪነጥበብ ፌስቲቫል  መርሀግብር   lአይ ቢላሉል ሐበሺ ሙዚየም ተሳታፊ ሆነ።*************የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባህል እና ...
19/03/2026

"የጥበብ ስጦታ ለኢትዮጵያ ከፍታ" 17ኛው አዲስ የኪነጥበብ ፌስቲቫል መርሀግብር lአይ ቢላሉል ሐበሺ ሙዚየም ተሳታፊ ሆነ።
*************
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባህል እና ኪነጥበብ ቢሮ "የጥበብ ስጦታ ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል 17ኛው አዲስ የኪነጥበብ ፌስቲቫል ከመጋቢት 05 እስከ 07/2018 ዓ.ም በመስቀል አደባባይ በድምቀት ተካሂዷል።

ቢሮው አመታዊ የጥበብ ድግስ የከተማችንን የኪነ-ጥበብ ሀብቶች አጉልቶ ለማሳየት የተዘጋጀ ሲሆን፣ የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣የሀይማኖት አባቶች፣ አባገዳዎች፣ ሀደስንቄዎች፣ አንጋፋና ወጣት የኪነጥበብ ባለሞያዎችና ከአስራ አንዱም ክ/ከተማ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት 17ኛው አዲስ የኪነጥበብ ፌስቲቫል በድምቀት እየተካሄደ ይገኛል።

በፌስቲቫሉ ላይ ማራኪ የኪነ-ጥበብ ውድድሮች፣ ዐውደ ርዕዮች እና ልዩ ልዩ ሥነ-ጥበባዊ ክዋኔዎች፣ በዕይታዊ፣ በክውን እና በሥነ-ፅሑፋዊ ጥበባት መስኮች የተዘጋጁ አዝናኝ እና አስተማሪ ሥራዎች እየቀረቡ ሲሆን በመርሀግብሩ ላይ በከተማዋ የሚገኙ የሥነ-ጥበብ ተቋማት፣ ቴአትር ቤቶች፣ የአ.አ.ዩ የሥነ-ጥበብ ትምህርት ቤቶች፣ የሀይማኖት ተቋማት፣ ከ11ዱም ክፍለ ከተሞች የተወጣጡ ባለሙያዎች፣ ትምህርት ቤቶች እና የሙያ ማህበራት በአንድ መድረክ ላይ እንደሚታደሙ የዝግጅት ክፍሉ አስታውቋል።

​የአዲስ አበባ ባህል እና ኪነጥበብ ቢሮ ኃላፊ ክብርት ዶክተር ሂሩት ካሳው በመድረኩ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልእክት ኪነጥበብ የሀገርን ታሪክ ከመዘከር እና ማንነትን ከመቅረፅ ባለፈ፤ ልዩነቶችን አቻችሎ ሰዎችን በአንድነት የሚያስተሳስርና መግባባትን የሚፈጥር ዓለም አቀፍ ቋንቋ ነው ካሉ በኋላ የጥበብ ባለሙያዎች የተዛቡ አመለካከቶችን በማረም፣ መልካም እሴቶችን በማንቃት እና ማህበረሰብን ለሀገር ከፍታእና ብልፅግና በማስተባበር ሀገርን ወደ ተሻለ ደረጃ የማድረስ ትልቅ ኃላፊነትና የመሪነት ሚና እንዳላቸው አሳስበዋል።

ቢሮ ኋላፊዋ አያይዘውም ይህ ፌስቲቫል የጥበብ ስራዎችን ለማየት ብቻ ሳይሆን የህዝቦችን ወንድማማችነትና አንድነት ለማጉላት የተዘጋጀ ነው ብለዋል ። በኪነጥበብ በመተሳሰብ እና በጋራ በመስራት የኢትዮጵያን ብልፅግና እና ከፍታ ማረጋገጥ ይቻላል! ካሉ በኋላ ይህንን ታላቅ ፌስቲቫል መላው የከተማዋ ነዋሪዎች፣ የኪነጥበብ አድናቂዎች፣ የጥበብ ባለሙያዎች እንዲሁም ሁሉም የሚዲያ ተቋማት በመስቀል አደባባይ ተገኝታችሁ የጥበብን ድግስ እንድትታደሙ በአክብሮት በመጋበዝ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።

ቢላሉል ሐበሺ - Bilalul Habeshi Community - ኑ ወደ ደግነት

የረመዷን መልዕክት 28የተቸገሩትም አብረው እንዲያከብሩ ዘካተል ፊጥርን አውጣ። በሀዲስ እንደተገለጸው፡ ነቢዩ (ﷺ) ዘካተል ፊጥርን ለጾመኛ ከውድቅ ንግግር ማጥሪያ፣ ለምስኪኖች ደግሞ መብል ይ...
19/03/2026

የረመዷን መልዕክት 28

የተቸገሩትም አብረው እንዲያከብሩ ዘካተል ፊጥርን አውጣ።
በሀዲስ እንደተገለጸው፡ ነቢዩ (ﷺ) ዘካተል ፊጥርን ለጾመኛ ከውድቅ ንግግር ማጥሪያ፣ ለምስኪኖች ደግሞ መብል ይሆን ዘንድ ግዴታ አድርገዋል።

ኑ ወደ ደግነት!

የረመዷን መልዕክት 27ዛሬ ላለው ነገር ሁሉ አልሀምዱሊላህ በል።ነቢዩ (ﷺ) እንዳሉት፡ "አላህ አንድ ባሪያ ምግብ በልቶ ወይም ጠጥቶ ሲያመሰግነው ይወድለታል።"ኑ ወደ ደግነት!
19/03/2026

የረመዷን መልዕክት 27

ዛሬ ላለው ነገር ሁሉ አልሀምዱሊላህ በል።
ነቢዩ (ﷺ) እንዳሉት፡ "አላህ አንድ ባሪያ ምግብ በልቶ ወይም ጠጥቶ ሲያመሰግነው ይወድለታል።"

ኑ ወደ ደግነት!

የረመዷን መልዕክት 26ዛሬ አንድን ሰው ይቅር በል።ነቢዩ (ﷺ) እንዳሉት፡ "አንድ ባሪያ ይቅርታ በማድረጉ አላህ ክብሩን እንጂ አይጨምርለትም።"ኑ ወደ ደግነት!
19/03/2026

የረመዷን መልዕክት 26

ዛሬ አንድን ሰው ይቅር በል።
ነቢዩ (ﷺ) እንዳሉት፡ "አንድ ባሪያ ይቅርታ በማድረጉ አላህ ክብሩን እንጂ አይጨምርለትም።"

ኑ ወደ ደግነት!

ቡና ባንክ ለቢላሉል ሐበሺ የ300,000 ብር የገንዘብ ድጋፍ አበረከተ*****​ባቡና ባንክ በተከበረው የረመዷን ወር ያለውን ማህበራዊ ኃላፊነት በመወጣት፣ ለቢላሉል ሐበሺ የ300,000 (ሶስ...
16/03/2026

ቡና ባንክ ለቢላሉል ሐበሺ የ300,000 ብር የገንዘብ ድጋፍ አበረከተ
*****
​ባቡና ባንክ በተከበረው የረመዷን ወር ያለውን ማህበራዊ ኃላፊነት በመወጣት፣ ለቢላሉል ሐበሺ የ300,000 (ሶስት መቶ ሺህ) ብር የገንዘብ ድጋፍ አድርጓል።

​የባንኩ ከፍተኛ አመራሮች እና ሰራተኞች በተገኙበት በተከናወነው የድጋፍ መርሐ-ግብር ላይ፣ የቢላሉል ሐበሺ አመራሮች እና የቦርድ አባላት ለባንኩ ልዑካን ቡድን በማእከሉ ውስጥ ያሉ የስልጠና ማእከላትን እና በሙዚየሙ ውስጥ ያለውን ቅርስ በማስጎብኘት ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል።

​ቡና ባንክ በተከበረው የረመዷን ወር ያሳየው ይህ የሁልጊዜም ትብብር እና ደግነት የሚደነቅ ሲሆን፣ በቢላሉል ሐበሺ ቤተሰቦች ስም ልባዊ ምስጋናችንን እናቀርባለን።

በቀጣይም በበጎ ስራዎች ላይ ሁልጊዜም እንደምንቀራረብ እናምናለን።

ኑ ወደ ደግነት!

ዓለም አቀፉ የረድኤት ድርጅት Hayrat Yardım ልኡካኖች የቢላል ሐበሺ ሙዚየምን ጎበኙ*****​ታዋቂው ዓለም አቀፍ የእርዳታ ድርጅት Hayrat Yardım በኢትዮጵያ እያከናወነ ከሚገኘው...
15/03/2026

ዓለም አቀፉ የረድኤት ድርጅት Hayrat Yardım ልኡካኖች የቢላል ሐበሺ ሙዚየምን ጎበኙ
*****

​ታዋቂው ዓለም አቀፍ የእርዳታ ድርጅት Hayrat Yardım በኢትዮጵያ እያከናወነ ከሚገኘው ዘርፈ ብዙ የበጎ አድራጎት ስራዎች ጎን ለጎን፣ በታሪካዊው የቢላል ሐበሺ ሙዚየም የጉብኝት መርሐ-ግብር አከናውኗል።

​በጉብኝታቸው ወቅት የድርጅቱ ተወካዮች የቢላል ሐበሺን ታላቅ ታሪክና በሙዚየሙ የሚገኙ ድንቅ እሴቶችን ተመልክተዋል። በታዩት የታሪክ ቅርሶችና ትርክቶች እጅግ መደሰታቸውን የገለጹት የድርጅቱ አባላት፣ የኢትዮጵያን ጥልቅ ባህልና ታሪክ የበለጠ ለመረዳት ዕድል እንዳገኘውም ገልጸዋል።

​Hayrat Yardım በሀገራችን እያደረገ ያለው የበጎነት ስራ የሚደነቅ ሲሆን፣ ሌሎች ዓለም አቀፍ ተቋማትም ይህንን አርአያነት በመከተል በኢትዮጵያ የታሪክና የበጎ አድራጎት ስራዎች ላይ እንዲሳተፉ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

​ኑ ወደ ደግነት!
Hayrat Yardım
ቢላሉል ሐበሺ - Bilalul Habeshi Community - ኑ ወደ ደግነት
#ቢላሉልሐበሺ

የረመዷን መልዕክት 25በምስጢር ሰደቃ ስጥ። ነቢዩ (ﷺ) እንዳሉት፡ "በምስጢር የሚሰጥ ሰደቃ የጌታን ቁጣ ያበርዳል።"ኑ ወደ ደግነት!
15/03/2026

የረመዷን መልዕክት 25

በምስጢር ሰደቃ ስጥ።
ነቢዩ (ﷺ) እንዳሉት፡ "በምስጢር የሚሰጥ ሰደቃ የጌታን ቁጣ ያበርዳል።"

ኑ ወደ ደግነት!

Address

Addis Ababa

Opening Hours

Monday 08:30 - 17:00
Tuesday 08:30 - 17:00
Wednesday 08:30 - 17:00
Thursday 08:30 - 17:00
Friday 08:30 - 17:00

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ቢላሉል ሐበሺ - Bilalul Habeshi Community - ኑ ወደ ደግነት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to ቢላሉል ሐበሺ - Bilalul Habeshi Community - ኑ ወደ ደግነት:

Share