ቢላሉል ሐበሺ - Bilalul Habeshi Community - ኑ ወደ ደግነት

ቢላሉል ሐበሺ - Bilalul Habeshi Community - ኑ ወደ ደግነት Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ቢላሉል ሐበሺ - Bilalul Habeshi Community - ኑ ወደ ደግነት, Charitable organisation, Addis Ababa.

''እኛ ከገንዘባችሁ በፊት ቀልባችሁን እና ማንነታችሁን እንፈልጋለን! ገንዘባችሁ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ላይኖር ስለሚችል ስለ ቀልባችሁ እንጨነቃለን። ምስኪኖች ግን በቅደሚያ ገንዘባችሁን ይፈልጋሉና አስታውሱዋቸው። አሏህ ﷻ እናንተን ያስታውሳችኃል ።''
(ኡስታዝ ሙሐመድ ጀማል ጎናፍር የቢላሉል ሐበሺ ዋና መስራችና የበላይ ጠባቂ )

የእዝነቱ ነቢይ!****በዚህ ታላቅ የረቢዕ ወር፣ ለአለማት እዝነት ሆነው የተላኩትን የነቢዩ ሙሐመድን (ﷺ) ውልደት እናስታውሳለን። የእሳቸው መምጣት የጨለማው ዘመን ማብቂያ እና የብርሃን፣ የ...
14/08/2026

የእዝነቱ ነቢይ!
****
በዚህ ታላቅ የረቢዕ ወር፣ ለአለማት እዝነት ሆነው የተላኩትን የነቢዩ ሙሐመድን (ﷺ) ውልደት እናስታውሳለን።

የእሳቸው መምጣት የጨለማው ዘመን ማብቂያ እና የብርሃን፣ የፍቅር እንዲሁም የርህራሄ ጅማሮ ነበር። የህይወት ዘመናቸው ሙሉ የሰው ልጅን ወደ በጎነት የመምራት ጥረት ሆኖ አልፏል።

ኑ ወደ ደግነት! የነቢዩን (ﷺ) የራህመት መንገድ በተግባር በመከተል፣ እጃችንን ወደ ቢላሉል ሐበሺ ማዕከል እንዘርጋ።

ማዕከሉን በመርዳት የእዝነት እና የደግነት ተቋዳሽ እንሁን!

🌸 በራስ መተማመን ያላቸውን ስኬታማ ልጆች ለኡማው እንዴት እናበርክት? 🌸ለተከበራችሁ እናቶች ብቻ የተዘጋጀ ልዩ ፕሮግራም!የነገው ኡማ ተስፋ የሆኑትን ልጆቻችንን በስነ-ምግባር፣ በእምነት እና...
13/08/2026

🌸 በራስ መተማመን ያላቸውን ስኬታማ ልጆች ለኡማው እንዴት እናበርክት? 🌸

ለተከበራችሁ እናቶች ብቻ የተዘጋጀ ልዩ ፕሮግራም!

የነገው ኡማ ተስፋ የሆኑትን ልጆቻችንን በስነ-ምግባር፣ በእምነት እና በጠንካራ የራስ መተማመን አንፀን ለማሳደግ በሚያስችሉ ወሳኝ ጉዳዮች ላይ የምንመክርበት ድንቅ መድረክ ተዘጋጅቶሎታል።

📅 ቀን፦ ቅዳሜ፣ ነሐሴ 9 ቀን 2018 ዓ.ም
⏰ ሰዓት፦ ከጠዋቱ 3፡00 እስከ 6፡00
📍 ቦታ፦ መካኒሳ፣ ቢላሉል ሀበሺ ማዕከል አዳራሽ

🎁 መግቢያ በነጻ !

በዚህ ጠቃሚ ፕሮግራም ላይ ለመታደም እባክዎ ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን አስቀድመው ይመዝገቡ፦

🔗 ለመመዝገብ፦ https://forms.gle/R6DGbwvmoG3aHmd59

ልዩ የጉብኝት መርሐ-ግብር በቢላሉል ሐበሺ ማዕከል! ******​በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያን የተለያዩ ከተሞች እና ቦታዎች እየጎበኙ የሚገኙ ከሳውዲ አረቢያ የመጡ ታላላቅ ኡስታዞች፣ ዳዒዎች እን...
13/08/2026

ልዩ የጉብኝት መርሐ-ግብር በቢላሉል ሐበሺ ማዕከል!
******
​በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያን የተለያዩ ከተሞች እና ቦታዎች እየጎበኙ የሚገኙ ከሳውዲ አረቢያ የመጡ ታላላቅ ኡስታዞች፣ ዳዒዎች እንዲሁም ተፅዕኖ ፈጣሪ የማህበራዊ ሚዲያ አንቂዎች (ታዋቂ ቲክቶከሮች) በቢላሉል ሐበሺ ማዕከል በመገኘት ጉብኝት አድርገዋል።
የተቋማችንን መስራችና የበላይ ጠባቂ ኡስታዝ ሙሐመድ ጀማል ጎናፍርን አግኝተው አነጋግረዋል።

​በነበራቸው ቆይታም ማዕከላችን እያከናወናቸው ባሉ ሰፊ የማህበራዊ ስራዎች እና እንቅስቃሴዎች ዙሪያ የተወያዩ ሲሆን፣ ወደፊት በሁለቱ ወገኖች መካከል ሊጠናከሩ በሚችሉ የትብብር መስኮች ላይም ፍሬያማ ምክክር አድርገዋል።

​ይህ ጉብኝት ለቢላሉል ሐበሺ ማዕከል ልዩ ትርጉም ያለው አጋጣሚ ነው። ክቡራን እንግዶቻችን በማዕከላችን ተዘዋውረው በተመለከቷቸው እና በሰሟቸው ተስፋ ሰጪ ተግባራት ላይ ያላቸውን ልባዊ አድናቆት እና መልካም አስተያየት አስፍረዋል።

​ጊዜያችሁን ሰውታችሁ ተቋማችንን ስለጎበኛችሁ ከልብ እናመሰግናለን!

12/08/2026

ሉህ (ለውሕ)
ጥንታዊው በእንጨት ላይ የተከተበ ቁርአን!

በአፋር ክልል ለሚገኙ ኡለማዎቻችን እና ተማሪዎች የድጋፍ መርሐግብር ተካሄደ!*****ቢላሉል ሐበሺ ማዕከል በአፋር ክልላዊ ቅርንጫፉ አማካኝነት ለተከበሩ ኡለማዎች የገንዘብ እና የአልባሳት፣ እ...
12/08/2026

በአፋር ክልል ለሚገኙ ኡለማዎቻችን እና ተማሪዎች የድጋፍ መርሐግብር ተካሄደ!
*****
ቢላሉል ሐበሺ ማዕከል በአፋር ክልላዊ ቅርንጫፉ አማካኝነት ለተከበሩ ኡለማዎች የገንዘብ እና የአልባሳት፣ እንዲሁም ለተማሪዎች የሚሆን ልዩ ድጋፍ አድርጓል።

ይህ አሁን የተደረገው የቢላሉል ሐበሺ ድጋፍ ጅማሮ ሲሆን፤ በቀጣይም ይህንኑ በጎ ተግባር አጠናክረን የምንቀጥል ይሆናል።

በዕለቱ በርካታ ኡለማዎች፣ ሸይኾች እና ወጣቶች የተገኙ ሲሆን፤ ለተደረገላቸው ድጋፍ እና ማስታወስ ከልብ የመነጨ ምስጋናቸውን ገልፀው ዱዓ አድርገዋል።

ተጨማሪ ከክልሉ የመንግስት አመራሮች ጋር በመነጋገር ለቢላሉል ሐበሺ ማዕከል ግንባታ የሚውል የቦታ (መሬት) ጥያቄ ሂደት እንደሚካሄድ አሳውቀውናል።

ኡለማዎቻችን የዲን አውራዎች ናቸው። ሁላችንም ከጎናቸው በመቆም፣ በማገዝና በማስታወስ የበኩላችንን ኃላፊነት እንድንወጣ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

#አፋር #ኡለማዎች #ድጋፍ

ወ/ሮ አሲያ እና ወንድሞቿ በቢላሉል ሐብሺ ጉብኝት አደረጉ፤ በቀጣይ ይፋ በሚደረጉ የበጎ አድራጎት ፕሮጀክቶች ዙሪያም ሰፊ ውይይት ተካሂዷል***በተለያዩ የማህበራዊ ገፆች ላይ በንቁ ተሳትፎዋ፣...
05/08/2026

ወ/ሮ አሲያ እና ወንድሞቿ በቢላሉል ሐብሺ ጉብኝት አደረጉ፤ በቀጣይ ይፋ በሚደረጉ የበጎ አድራጎት ፕሮጀክቶች ዙሪያም ሰፊ ውይይት ተካሂዷል
***

በተለያዩ የማህበራዊ ገፆች ላይ በንቁ ተሳትፎዋ፣ በኸይር ስራዎቿ የምናውቃት ወ/ሮ አሲያ ወንድሞቿ ጋር በመሆን በቢላሉል ሐብሺ ማዕከል የተሳካ ጉብኝት አድርጋለች።

በጉብኝቱ ወቅትም የማዕከሉ የበላይ ጠባቂ የሆኑት ኡስታዝ ሙሐመድ ጀማል ጎናፍር እና ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ጀማል ሙሐመድ ለእንግዶቹ ደማቅ አቀባበል በማድረግ ማዕከሉን አስጎብኝተዋቸዋል።

በዚህ የጉብኝት መርሃ ግብር ላይ ከስፍራው የስራ ሂደቶች እይታ ባለፈ ሰፊ የምክክር (ሹራ) መድረክ የተካሄደ ሲሆን፣ የውይይቱ ዋና ትኩረትም ወ/ሮ አሲያ በቀጣይ ቀናት ወደ ስራ ለማስገባት ባቀደቻቸው አዳዲስ የበጎ አድራጎት ፕሮጀክቶች ዙሪያ ያተኮረም ነበር።

እነዚህ በወ/ሮ አሲያ አነሳሽነት የታቀዱት የበጎ አድራጎት ፕሮጀክቶቹ እውን በሚሆኑበት ሂደት ከማዕከሉ አመራሮች ጋር በጋራ መስራት በሚቻልባቸው ሁኔታዎች እና በቀጣይ አቅጣጫዎች ላይ ስኬታማ የሃሳብ ልውውጥ ተደርጓል።

በመጨረሻም ወ/ሮ አሲያ እና ወንድሞቿ ከማዕከሉ ስራ አስኪያጅ እና ከኡስታዝ ሙሐመድ ጀማል ጋር በነበራቸው ቆይታ እጂግ ጠቃሚ እና በቢላሉል ሐበሺ ማዕከልም ስለተመለከቱት በርካታ ተግባሮች ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ኑ ወደ ደግነት!

ሰሪ እጆችን እናቋቁም ዘላቂ ለውጥ እናምጣ!***********{ مَّثَلُ الَّذِينَ يُنفِقُونَ أَمْوَالَهُمْ فِي سَبِيلِ اللَّهِ كَمَثَلِ حَبَّةٍ ...
03/08/2026

ሰሪ እጆችን እናቋቁም ዘላቂ ለውጥ እናምጣ!
***********
{ مَّثَلُ الَّذِينَ يُنفِقُونَ أَمْوَالَهُمْ فِي سَبِيلِ اللَّهِ كَمَثَلِ حَبَّةٍ أَنبَتَتْ سَبْعَ سَنَابِلَ فِي كُلِّ سُنبُلَةٍ مِّائَةُ حَبَّةٍ ۗ وَاللَّهُ يُضَاعِفُ لِمَن يَشَاءُ ۗ وَاللَّهُ وَاسِعٌ عَلِيمٌ }

"የእነዚያ ገንዘቦቻቸውን በአላህ መንገድ የሚለግሱ ሰዎች ብጤ፣ ሰባት ዘለላዎችን እንዳበቀለች፣ በየዘለላውም ሁሉ መቶ ቅንጣት (ፍሬ) እንዳለበት አንዲት ብቅል (ዘር) ብጤ ነው። አላህም ለሚሻው ሰው (ምንዳን) ያነባብራል። አላህም (ችሮታው) ሰፊ ዐዋቂ ነው።" [2:261]

በቅዱስ ቁርኣን ውስጥ አላህ (ሱ.ወ) በሱ መንገድ ገንዘባቸውን የሚሰጡ ሰዎችን ምሳሌ "ከእርሷ ሰባት ዘለላዎችን እንዳወጣች፣ በእያንዳንዱ ዘለላ ውስጥ መቶ ፍሬዎች እንዳሉባት አንዲት ቅንጣት"
አድርጎ ገልፆታል።

ችግረኞችን የዕለት ጉርስ ከመስጠት አልፎ በዘላቂነት ማቋቋም ትልቁ አላማችን ነው። የቢላሉል ሐበሺ ተቋም አቅመ ደካሞችን በስራ በማሰማራት እራሳቸውን እንዲችሉ ያደርጋል።

እርስዎም ለዘላቂ ለውጥ አጋር ይሁኑ!
ኑ ወደ ደግነት

በምድር ላሉት እዘኑ በሰማይ ያለው (መላኢካ) ያዝንላችኋል!************በሐዲስ እንደተዘገበው "አዛኝ ለሆኑት አላህ ያዝንላቸዋል፤ በምድር ላሉት እዘኑ በሰማይ ያለው(መላኢካ) ያዝንላችኋ...
02/08/2026

በምድር ላሉት እዘኑ በሰማይ ያለው (መላኢካ) ያዝንላችኋል!
************

በሐዲስ እንደተዘገበው "አዛኝ ለሆኑት አላህ ያዝንላቸዋል፤ በምድር ላሉት እዘኑ በሰማይ ያለው(መላኢካ) ያዝንላችኋልና።"

እዝነት የሰው ልጅ መገለጫ፣ የእስልምናችን መሰረት ነው። በአቅመ ደካሞች፣ በታመሙት እና በተቸገሩ ወገኖቻችን ላይ ርህራሄን ማሳየት የቢላሉል ሐበሺ ተቋም ዋነኛ መርህ ነው።

እጃችንን እንዘረጋ፣ ለወገኖቻችን አለንላችሁ እንበል።

ኑ ወደ ደግነት

እውቀት ብርሃን ነው፤ ትውልድን በእውቀት እናንፅ!********የቅዱስ ቁርኣን የመጀመሪያው ትዕዛዝ "ኢቅረእ" (አንብብ) የሚል ነው። ትውልድን በእውቀት፣ በስነ-ምግባር እና በክህሎት ማነፅ ከ...
01/08/2026

እውቀት ብርሃን ነው፤ ትውልድን በእውቀት እናንፅ!
********

የቅዱስ ቁርኣን የመጀመሪያው ትዕዛዝ "ኢቅረእ" (አንብብ) የሚል ነው። ትውልድን በእውቀት፣ በስነ-ምግባር እና በክህሎት ማነፅ ከሁሉ የተሻለ ዘላቂ ኢንቨስትመንት ነው። የቢላሉል ሐበሺ ተቋም ለተማሪዎች የተለያዩ ስልጠናዎችን እና የትምህርት እድሎችን በማመቻቸት ማህበረሰቡን በዘላቂ እውቀት እያነጸ ይገኛል፡፡

ዛሬ ላይ ሆነን የነገውን ብሩህ ትውልድ አብረን እንገንባ።

ኑ ወደ ደግነት!

የቲሞችን እንከባከብ ነጋቸውን ብሩህ እናድርግ!*****የአላህ መልክተኛ ነብዩ ሙሐመድ ﷺ "እኔና የቲምን የሚያሳድግ ሰው በጀነት ውስጥ እንደዚህ ነን" በማለት ጠቋሚና የመሃል ጣታቸውን አጣምረ...
31/07/2026

የቲሞችን እንከባከብ ነጋቸውን ብሩህ እናድርግ!
*****
የአላህ መልክተኛ ነብዩ ሙሐመድ ﷺ "እኔና የቲምን የሚያሳድግ ሰው በጀነት ውስጥ እንደዚህ ነን" በማለት ጠቋሚና የመሃል ጣታቸውን አጣምረው አሳይተዋል። እናትና አባት በማጣት የተከዙ ህጻናትን እንባ ማበስና መንከባከብ ትልቅ ምንዳ ያለው ተግባር ነው።

የቢላሉል ሐበሺ ተቋም እነዚህን የነገ ተስፋዎች በማቀፍ፣ በማስተማርና በመንከባከብ ላይ ይገኛል።

እርስዎም አሻራዎን ያኑሩ፤ የዚህ ታላቅ አጅር ተካፋይ ይሁኑ!

ኑ ወደ ደግነት!

Address

Addis Ababa

Opening Hours

Monday 08:30 - 17:00
Tuesday 08:30 - 17:00
Wednesday 08:30 - 17:00
Thursday 08:30 - 17:00
Friday 08:30 - 17:00

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ቢላሉል ሐበሺ - Bilalul Habeshi Community - ኑ ወደ ደግነት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to ቢላሉል ሐበሺ - Bilalul Habeshi Community - ኑ ወደ ደግነት:

Shortcuts

Share