Ethiopian Wildlife Conservation Authority

Ethiopian Wildlife Conservation Authority Guardians of the Wild and Native!

The Ethiopian Wildlife Conservation Authority is established under proclamation number 575/2008 having the responsibility to undertake appropriate conservation and development of wildlife for its sustainable use, under the mission “To develop and conserve scientifically Ethiopia’s Wildlife resources and protected areas through active participation of community and other stakeholders, to bring ecol

ogical, economic and social benefits for Ethiopians as well as the global community and pass them to the next generation as a heritage.”

15/07/2026
የማጎ ብሔራዊ ፓርክ ጥበቃን ለማጠናከር የጋራ ቅንጅታዊ ሥራ ለመስራት ምክክር ተካሄደ፣በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቱሪዝም ቢሮ የማጎ ብሔራዊ ፓርክ ጽ/ቤት እና በኣሪ ዞን የባካ ዳዉላ ኣሪ ወረዳ ...
14/07/2026

የማጎ ብሔራዊ ፓርክ ጥበቃን ለማጠናከር የጋራ ቅንጅታዊ ሥራ ለመስራት ምክክር ተካሄደ፣

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቱሪዝም ቢሮ የማጎ ብሔራዊ ፓርክ ጽ/ቤት እና በኣሪ ዞን የባካ ዳዉላ ኣሪ ወረዳ የዱር እንስሳት ጥበቃና የዱር እንስሳት ዉጤቶች ዝዉዉር ቁጥጥር ግብረ ሃይል አባል መስሪያ ቤቶች የጋራ ቅንጅታዊ ሥራ ለመስራት ምክክር አካሂዷል።

በመድረኩ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግርና ሴነድ ያቀረቡት የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቱርዝም ቢሮ የማጎ ብሔራዊ ፓርክ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አርቦር ለሌ ሲሆኑ በንግግራቸውም የማጎ ፓርክ የሁላችን የህልውና ጉዳይ እንደሆነ እና ሁሉም ባለድርሻ አካላት እጅ ለእጅ ተያይዘን የተሯቀተችውን ማጎ ፓርክን ወደተሻለ ደረጃ ማሻገር አለብን ብለዋል።

አያይዘዉም የማጎ ብሔራዊ ፓርክ ግብረሃይል አባል ለፓርኩ ወላጅ አባት/እናት በመሆን መንከባከብ አለበትና ሁላችንም ኃላፊነት ወስደን መስራት አለብን ስሉም የአደራ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

በመድረኩም ሰነድ የቀረበ ሲሆን ሰነዱ ከቀረበ በኋላም ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል።የዉይይት መድረኩንም የማጎ ብሔራዊ ፓርክ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አርቦር ለሌ እና የፓርኩ ግብረሃይል ምክትል ሰብሳቢ እና የባካ ዳዉላ ኣሪ ወረዳ ሠላምና ፀጥታ ጽ/ ቤት ኃላፊ አቶ ዳዊት ተካ በጋራ በመሆን መድረኩን መርተዋል።

በስተመጨረሻም በመድረኩ ማጠቃለያ የባካ ዳዉላ ኣሪ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪና የፓርኩ ግ/ሃይል ሰብሳቢ የሆኑት አቶ መሠረት ቦጋለ በመዝጊያ ንግግራቸዉም በቅድሚያ ከፓርኩ፣ ከኩሬ ከግስቴ እና ከባይጽማል ለመጡ የግበረ ሃይል አባላት ሰላምታ አቅርበው፤

ማጎ ብሄራዊ ፓርክ በደቡብ ኦሞና በኣሪ ዞኖች መካከል የሚገኝ ሲሆን በኣሪ ዞን በባካ ዳውላ እና በጂንካ ከተማ መዋቅሮች በሚገኙ በግስቴ ፣ባይጽማል እና ኩሬ ቀበሌያትን የሚዋሰን በመሆኑ ባሌቤቶች/ወላጆች/ ሆነናል።

በመጨረሻ ባስተላለፉት መልዕክትም በዚህም መሠረት 3ቱ ቀበሌያት ፓርኩና ባካ ዳዉላ ኣሪ ወረዳ የጋራ የማጎ ብሔራዊ ፓርክ የዱር እንስሳት ጥበቃና የዱር እንስሳት ውጤቶች ዝውውር ቁጥጥር ግብረ ሃይል የውል ስምምነት ሰነድ ተፈራርመን በውላችን መሠረት የተቀናጀ ጥበቃ ማድረግ አለብን በማለት የሦስትዮሽ የጋራ ዉል ተፈራርመዋል።

በመድረኩ የጂንካ ከተማ አስተዳደር መዋቅር ቀበሌያት፥ ኩሬና ባይጽማል ተገኝተዋል፤ ምክንያቱ በክልላች ቱሪዝም ቢሮ ማጎ ብሔራዊ ፓርክ በፊት በነበረው አደረጃጀት የፓርኩን ድንበርና ቀበሌያትን በባካ ዳውላ ኣሪ ወረዳ ውስጥ ስለሚያዋስን መሆኑም ተገልጿል።

ደቡብ ኢትዮጵያ ቱሪዝም ቢሮ

የሀገራችን የተፈጥሮ ኩራት ዋልያን ለማዳን የሁሉም ባለድርሻ አካላት ርብርብ በእጅጉ ወሳኝ ነው።ሐምሌ 5/2018 ዓ.ምኢዱጥባየኢትዮጵያ ብርቅዬ እና የተፈጥሮ ምልክት የሆነው ዋልያ አይቤክስ (...
12/07/2026

የሀገራችን የተፈጥሮ ኩራት ዋልያን ለማዳን የሁሉም ባለድርሻ አካላት ርብርብ በእጅጉ ወሳኝ ነው።

ሐምሌ 5/2018 ዓ.ም
ኢዱጥባ

የኢትዮጵያ ብርቅዬ እና የተፈጥሮ ምልክት የሆነው ዋልያ አይቤክስ (Walia Ibex) የህልውና አደጋ ውስጥ መግባቱ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለዓለም የተፈጥሮ ቅርስ ጥበቃ ትልቅ ስጋት ፈጥሯል።

በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኝ ብርቅዬ ፍጥረት ከጥፋት ለመታደግ የአካባቢው መስተዳደር እና ማህበረሰብ፣ አጋር ድርጅቶች፣ የምርምር ተቋማት፣ የሃይማኖት ተቋማትና ሁሉም ባለድርሻ አካላት የተቀናጀና የተጠናከረ ርብርብ ማድረግ ወሳኝ ነው።

የስሜን ተራራዎች ብሔራዊ ፓርክ በ1978 ዓ.ም. በዩኔስኮ የዓለም ቅርስ ዝርዝር ውስጥ ከተመዘገቡ የመጀመሪያዎቹ ቅርሶች አንዱ ነው። ለዚህ የቅርስነት እውቅና ዋልያ በፓርኩ መገኘቱ ከፍተኛ ድርሻ ማበርከቱ ይታወቃል።
ዋልያን መጠበቅ የአንድ የዱር እንስሳ ጥበቃ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የአገራችንን የተፈጥሮ ቅርስ፣ የብዝሃ ሕይወት እና የቱሪዝም እሴት መጠበቅ ጭምር ነው።

በ2016/17 የበጀት ዓመት የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን፣ የስሜን ተራራዎች ብሔራዊ ፓርክ እና ከአፍሪካን ዋይልድ ላይፍ ፋውንዴሽን (AWF) የተውጣጡ የጥናትና ምርምር ባለሙያዎች በመተባበር “Walia Ibex Decline Root Cause Assessment” የተሰኘውን ጥናት አካሂደዋል ።

የጥናቱ ውጤትም ከሰሜኑ ጦርነት ጋር ተያይዞ በዋልያ ህልውና ላይ የደረሱ አሉታዊ ተጽእኖዎችን፣ የመኖሪያ ቦታ መራቆትን፣ ህገ-ወጥ አደንን እና ሌሎች ሰው ሰራሽ ተግዳሮቶችን ለይቶ አሳይቷል።

ይህን ጥናት መነሻ በማድረግ ዓለም አቀፍ የተፈጥሮ ጥበቃ ህብረት (IUCN) የዋልያ አይቤክስን ከነበረበት “ለአደጋ የተጋለጠ” (Vulnerable) ደረጃ ወደ “በእጅጉ ለጥፋት የተጋለጠ” (Critically Endangered) ደረጃ መመደቡን አስታውቋል።

ይህ ምደባ ዋልያ አይቤክስ ከመቼውም ጊዜ በላይ አፋጣኝ እና የተጠናከረ የጥበቃ እርምጃ እንደሚያስፈልገው የዓለም አቀፍ ጥሪ ነው።

በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን ከአጋር ተቋማት፣ ከደባርቅ ዩኒቨርሲቲ፣ ከአካባቢው መስተዳደር እና ማህበረሰብ እንዲሁም በፓርኩ ውስጥ ከሚሰሩ ፕሮጀክቶች ጋር በመቀናጀት የተለያዩ የጥበቃ እርምጃዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል። ከእነዚህም መካከል፦
• በዋና ዋና የዋልያ መኖሪያ ቦታዎች የተጠናከረ የፓትሮል ሥራ ማከናወን፤
• ከሃይማኖት አባቶች ጋር በመቀናጀት ህገ-ወጥ አደንን ለመከላከል ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን ማካሄድ፤
• በቴክኖሎጂ የታገዘ የጥበቃ ክትትል (EarthRanger) ስርዓትን መተግበር፤
• የዋልያ አምባሳደሮችን በማቋቋም የመረጃ ስብሰባና የክትትል ሥራዎችን ማጠናከር፤
• ዋልያን ለመታደግ የ10 ዓመት ብሔራዊ የተግባር ዕቅድ በማዘጋጀት ወደ ትግበራ ማስገባት ተጠቃሾች ናቸው።

ይሁን እንጂ የዋልያ ህልውና ጉዳይ የአንድ ተቋም ኃላፊነት ብቻ አይደለም። አሁን ያለው ሁኔታ የሁሉንም ኢትዮጵያውያን የጋራ ጥረትና ቁርጠኝነት የሚጠይቅ ነው።

በተለይም የአካባቢው ማህበረሰብ ዋልያ የአገራችን የተፈጥሮ ኩራት መሆኑን በመገንዘብ በጥበቃው ውስጥ ያለውን ተሳትፎ የበለጠ ማጠናከር ይገባል።

ዋልያ የአንድ ተቋም ወይም የአንድ ማህበረሰብ ሀብት ብቻ ሳይሆን የመላው ኢትዮጵያና የዓለም የተፈጥሮ ቅርስ ነው።

ስለዚህ ይህን ብርቅዬ ፍጥረት ከጥፋት ለመታደግ ከባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በተጨማሪ የአካባቢው መስተዳደር፣ አጋር ድርጅቶች፣ የምርምር ተቋማት፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የአካባቢ ማህበረሰብ እና ሁሉም ኢትዮጵያውያን የተቀናጀና ቀጣይነት ያለው ርብርብ ማድረግ ይገባቸዋል።

የዋልያ ህልውናን መታደግ የአንድ የዱር እንስሳ ህልውናን መታደግ ብቻ ሳይሆን ለመጪው ትውልድ የኢትዮጵያን የተፈጥሮ ኩራትና የዓለም ቅርስ ጠብቆ ማስረከብ ነው።

Experience-Sharing Workshop Opens in Arba Minch to Strengthen Wildlife ConservationArba Minch, Ethiopia | 8 July 2026 – ...
08/07/2026

Experience-Sharing Workshop Opens in Arba Minch to Strengthen Wildlife Conservation

Arba Minch, Ethiopia | 8 July 2026 – (EWCA)
A two-day Experience-Sharing Workshop on Protected Area Management and Biodiversity Conservation opened today at Haile Resort, Arba Minch, bringing together government institutions, development partners, conservation organizations, national park wardens, regional protected area managers, and other stakeholders to review achievements, share experiences, and discuss future priorities for biodiversity conservation in Ethiopia.

The workshop is jointly organized by the Ethiopian Wildlife Conservation Authority (EWCA) and the Conservation and Sustainable Use of Biodiversity in Priority Protected Areas Project, implemented with the financial and technical support of the Government of Germany through KfW Development Bank.

The Workshop aims to strengthen collaboration among conservation partners by sharing lessons learned, best practices, and practical recommendations for improving protected area management and biodiversity conservation.

The experience sharing workshop focus on conservation challenges facing Ethiopia's protected areas, project responses to conservation threats, evolving best practices, experiences from international exposure visits, and approaches for integrating successful interventions into national conservation strategies.

Opening the workshop, State Minister of Tourism Mr. Sileshi Girma described biodiversity as one of Ethiopia's greatest national assets, emphasizing that protected areas not only conserve unique wildlife but also support sustainable tourism and improve the livelihoods of surrounding communities.

He reaffirmed the Government of Ethiopia's commitment to developing tourism destinations through strong collaboration with local communities, government institutions, and development partners, adding that the workshop provides an important opportunity to learn from both achievements and implementation challenges.

Speaking at the event, EWCA Director General Mr. Kumera Wakjira expressed his appreciation to the Government of Germany for its longstanding financial and technical support through KfW, highlighting its significant contribution to biodiversity conservation in Ethiopia.

He noted that Ethiopia's rich ecosystems and unique wildlife are of national, regional, and global importance and reaffirmed the Government's commitment to strengthening the country's protected area system and conserving its extraordinary biodiversity.

Representing KfW/GITEC, Mr. Peter Keil-Bruder presented the project's major achievements, implementation experiences, and challenges, underscoring the importance of continued partnership in enhancing conservation efforts.

The workshop will continue through 9 July 2026, with participants expected to develop practical recommendations that will further strengthen protected area management and biodiversity conservation across Ethiopia.

07/07/2026
የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን በተቋም ደረጃ እየተከናወኑ ያሉ የሪፎርም ሥራዎችን ገምግሟልሰኔ 2018 ዓ.ም. – አዲስ አበባ (ኢዱጥባ)የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣ...
03/07/2026

የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን በተቋም ደረጃ እየተከናወኑ ያሉ የሪፎርም ሥራዎችን ገምግሟል

ሰኔ 2018 ዓ.ም. – አዲስ አበባ (ኢዱጥባ)

የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን በተቋም ደረጃ በዝግጅት ምዕራፍ እየተተገበሩ ያሉ የሪፎርም ሥራዎችን አፈጻጸም ለመገምገም ባዘጋጀው መድረክ፣ የዋና መሥሪያ ቤቱ ሠራተኞችና የሪፎርም ኮሚቴ አባላት የተሳተፉበት ሰፊ ውይይት አካሂዷል።

በመድረኩ የባለሥልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን መኮንን እንደገለጹት፣ ተቋማዊ ሪፎርም የተቋሙን አደረጃጀትና አፈጻጸም ለማሻሻል፣ የሥራ ሂደቶችን ለማዘመን እና የሰው ኃይል አቅምን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ለማሳደግ ወሳኝ መሣሪያ ነው።

አቶ ሰለሞን አክለውም፣ ባለሥልጣኑ ቀጣይ የልማት ጉዞውን በውጤታማነት ለማስቀጠል ዘመናዊ የተቋም አደረጃጀት፣ ብቁና ብቃቱ የተረጋገጠ የሰው ኃይል፣ እንዲሁም ምቹ የሥራ አካባቢ መፍጠር የግድ መሆኑን ጠቅሰዋል። ይህንንም ለማሳካት ሁሉም ሠራተኞች የሪፎርሙ አካል ሆነው በንቃት መሳተፍና ለለውጡ ዝግጁ መሆን እንደሚገባቸው አሳስበዋል።

በውይይቱ ወቅት በየደረጃው የተቋቋሙ የሪፎርም ኮሚቴዎች እስካሁን ያከናወኗቸውን ተግባራትና የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት በዝርዝር በማቅረብ፣ በቀጣይ የሚወሰዱ እርምጃዎች ላይ ሰፊ ምክክር ተካሂዷል።

በመጨረሻም ሠራተኞች የሪፎርሙ ሂደት ዋና ተዋናዮች መሆናቸውን በመገንዘብ፣ በቀጣይ የሚከናወነውን የብቃት መለኪያ ምዘና በተሻለ ውጤት ለማጠናቀቅ ከወዲሁ በሙያ፣ በክህሎትና በሥነ-ምግባር ራሳቸውን ማዘጋጀት እንደሚገባቸው ተገልጿል።

የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የተቋማዊ ሪፎርም ሥራዎቹን በማጠናከር ቀልጣፋ፣ ተጠያቂ፣ ውጤታማ እና ዘመናዊ ተቋም በመገንባት በሀገሪቱ የዱር እንስሳት እና የብዝሀ ሕይወት ጥበቃ እና ዘላቂ የተፈጥሮ ሀብት አስተዳደርን በተመለከተ የተጣለበተን ኃላፊነት በተሻለ መልኩ ለመወጣት በትኩረት እየሠራ መሆኑ ተጠቁሟል።

የቱሪዝም ሚዲያ ፎረም በይፋ ተመሰረተሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ. ም አዳማየሀገሪቱን የቱሪዝም ሃብቶች ይበልጥ ለማስተዋወቅና የመረጃ ልውውጡን ስልታዊ በሆነ መንገድ ለመምራት የሚያስችል የቱሪዝም...
03/07/2026

የቱሪዝም ሚዲያ ፎረም በይፋ ተመሰረተ

ሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ. ም
አዳማ

የሀገሪቱን የቱሪዝም ሃብቶች ይበልጥ ለማስተዋወቅና የመረጃ ልውውጡን ስልታዊ በሆነ መንገድ ለመምራት የሚያስችል የቱሪዝም ሚዲያ ፎረም በአዳማ ከተማ በይፋ ተመስርቷል።

በፎረሙ ምስረታ ላይ የፌደራልና የክልል የቱሪዝም ቢሮዎች የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች፣ የቱሪዝም ዘርፍ ጋዜጠኞች እንዲሁም የተለያዩ የሚዲያ ተቋማት ኃላፊዎች ተሳትፈዋል።

ፎረሙ መመስረት ዋና ዓላማ ሀገሪቱ ለቱሪዝም ዘርፉ ከሰጠችው ከፍተኛ ትኩረት አኳያ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ስራዎችን በተቀናጀ መንገድ በመስራት ትልቅ ሀገራዊ ኃላፊነት እንደሚወጣ ያለመ ነው።

የፎረሙ መመስረት እስካሁን በዘርፉ በዘልማድ ከሚታየውና ለአንድ ወቅት ብቻ ከሚደረግ የመረጃ ልውውጥ ባለፈ በአባል ክልሎችና በሚዲያ ተቋማት መካከል ወጥነት ያለው የቱሪዝም መረጃ ልውውጥ በመዘርጋት፣ የሁለትዮሽ ግንኙነቶችን በማጠናከር የመረጃ ቅብብሎሽ ስርዓቱን የሚያሳልጥ ይሆናል።

ሮረሙ የሚዲያና የማኅበራዊ ሚዲያን ተፅዕኖ በመጠቀም የሀገሪቱን ጸጋዎች በተሻለ ጥራት ለማስተዋወቅ ትልቅ አቅም ይፈጥራል።

የፎረሙ አባላት በሙያዊ ብቃታቸው አዳዲስና ነባር የቱሪዝም መዳረሻዎችን በስፋት በማስተዋወቅ፣ የሀገርን በጎ ገጽታ በመገንባትና ለሕብረተሰቡ ዘላቂ የቱሪዝም መረጃ በማድረስ በቁርጠኝነት እንዲሰሩ ጥሪ ቀርቦላቸዋል።

Address

Head Office, Mexico Square
Addis Ababa
386

Opening Hours

Monday 08:30 - 17:30
Tuesday 08:30 - 17:30
Wednesday 08:30 - 17:30
Thursday 08:30 - 17:30
Friday 08:30 - 17:30

Telephone

+251115504838

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Wildlife Conservation Authority posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share