Voice Of Ethiopia

Voice Of Ethiopia 🌍🇪🇹 "Dive into Ethiopia's Tapestry: News, Culture, and Perspectives."

10/05/2026
05/05/2026

"የልጄ የሄቨን ጉዳይ ነገ ረቡዕ ፍርድ ቤት ስለሚታይ፣ እንድትገኙልኝ ጥሪዬን አስተላልፋለሁ።" — ወይዘሮ አብቅየለሽ

ሰላም ቤተሰቦች፤ አብቅየለሽ ነኝ የህፃን ሄቨን እናት። ዛሬ ፍርድ ቤት ቀጠሮ ነበረን፤ ለረቡዕ ተቀጥረናል።

አዲስ አበባ አካባቢ የምትኖሩ እህት ወንድሞቼ የሴቶች ሞት ጥቃት ይመለከተናል የምትሉ እንድትገኙልን በትህትና እጠይቃለሁ፤ አመሰግናለሁ።"

ነገ ሚያዝያ 28 ቀን 2018 ዓ.ም በህፃን ሄቨን ላይ የደረሰውን አሰቃቂ ግፍ ተከትሎ የተመሰረተው ክስ በችሎት ይታያል።

በ6 ኪሎ የካቲት ሆስፒታል ፊት ለፊት በሚገኘው ፍርድ ቤት ከጠዋቱ 3፡00 ጀምሮ የፍርድ ሂደቱ የሚከናወን ይሆናል።

በቪዲዮው ላይ የህፃን ሄቨን እናት አብቅየለሽ፣ የሴቶችና የህፃናት ጥቃት ጉዳይ የሚመለከተን ሁሉ በአካል በመገኘት ድጋፋችንን እንድናሳይ ጥሪ አቅርበዋል።

22/04/2026

የድምፃዊ ቴዲ አፍሮ ቀኝ እጅ የሆኑት ቁልፍ ግለሰቦች በፌደራል ፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋሉበት ምክንያት እስካሁን አልተገለፀም:: የቴዲ አፍሮ ምክትል ማናጀር፣ ቃል አቀባይ እና የአዲሱ አልበሙ ስራዎች መሪ (ኦስትሪያዊት የዜግነት ያላት)። የረጅም ዘመን የልብ ወዳጁ እና በስቱዲዮ ስራዎቹ የማይለየው ባለሙያ።
እስካሁን በቁጥጥር ስር የዋሉበት ይፋዊ ምክንያት ያልታወቀ ሲሆን፣ ድንገተኛው እስር ከአርቲስቱ ጋር ካላቸው ጥብቅ የስራ እና የጓደኝነት ግንኙነት ጋር የተያያዘ ሊሆን ይችላል የሚሉ ስጋቶች እየተደመጡ ነው። ጉዳዩ በብዙዎች ዘንድ ጥያቄንና ውግዘትን እየቀሰቀሰ ይገኛል።
አዳዲስ መረጃዎችን እንደደረሱን የምናጋራችሁ ይሆናል፤ ገጻችንን ይከታተሉ።

ሲፒጄ ( ) ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች የታገተው የ   ኤዲተር እንዲለቀቅ ጥሪ አቀረበ​አዲስ አበባ — የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ተቋም (CPJ)፤ በዋና ከተማዋ ከአዲስ ስታንዳርድ የዜና ክፍል...
18/04/2026

ሲፒጄ ( ) ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች የታገተው የ ኤዲተር እንዲለቀቅ ጥሪ አቀረበ

​አዲስ አበባ — የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ተቋም (CPJ)፤ በዋና ከተማዋ ከአዲስ ስታንዳርድ የዜና ክፍል ማንነታቸው ባልታወቁ ግለሰቦች ተወስዶ የተሰወረው ሚሊዮን በየነ በአስቸኳይ ያለበት ተለይቶ እንዲለቀቅ የኢትዮጵያ ባለሥልጣናትን ጠየቀ።
​ሲፒጄ ሚያዝያ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ፤ ሚሊዮን ረቡዕ ዕለት ረፋዱ ላይ በአዲስ አበባ ከሚገኘው የመገናኛ ብዙኃኑ የዜና ክፍል በሲቪል ልብስ በለበሱ ሰዎች ተይዞ ወደማይታወቅ ቦታ መወሰዱን ገልጿል።

​የአዲስ ስታንዳርድ አሳታሚ የሆነው ጃኬን ፐብሊሺንግ (JAKENN Publishing PLC)፤ ማኔጂንግ ኤዲተሩ ሚሊዮን በየነ ማንነታቸው ባልታወቁ ግለሰቦች ከተወሰደ 48 ሰዓታት ያለፉ ቢሆንም እስካሁን ያለበት ቦታ እንዳልታወቀ አስታውቋል። አሳታሚው ዛሬ ጠዋት ባወጣው መረጃ፤ በሚሊዮን ደኅንነት ላይ ያለው ስጋት እየጨመረ መሆኑንና ቤተሰቦቹም “በከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ” እንደሚገኙ ገልጿል።

ጊዜ ቆጣቢው የመረጃ ምንጭ ይፋ ሆነ! www.tiktok.com/
14/04/2026

ጊዜ ቆጣቢው የመረጃ ምንጭ ይፋ ሆነ!
www.tiktok.com/

ጋዜጠኛ መስከረም አበራ በአሳሳቢ ሁኔታ ላይ ትገኛለች!ከሦስት ዓመታት በፊት፡ በሚያዝያ 9 ቀን፣ በአማራ ክልል ያለውን ግጭት በመዘገቧ ምክንያት በቁጥጥር ስር የዋለችው ጋዜጠኛ መስከረም አበራ...
10/04/2026

ጋዜጠኛ መስከረም አበራ በአሳሳቢ ሁኔታ ላይ ትገኛለች!
ከሦስት ዓመታት በፊት፡ በሚያዝያ 9 ቀን፣ በአማራ ክልል ያለውን ግጭት በመዘገቧ ምክንያት በቁጥጥር ስር የዋለችው ጋዜጠኛ መስከረም አበራ ዛሬም በአሳሳቢ ሁኔታ ትገኛለች።በሽብርተኝነት የተከሰሰችው መስከረም፣ የሞት ቅጣትን ሊያስከትል የሚችል የክስ ሂደት ይጠብቃታል ሲል CPJ ብልፅግናን አስጠንቅቋል::የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት (CPJ) መስከረም በአስቸኳይ እንድትፈታና መንግስት በጋዜጠኞች ላይ የሚያደርገውን ማዋከብ እንዲያቆም ጥሪ አቅርቧል።
#ኢትዮጵያ

አቶ ክርስቲያን ታደለ የፓርላማ አባል ቢሆኑም ያለመከሰስ መብታቸው ተነስቶ፣ የህክምና ክልከላ እየተደረገባቸው በእስር ስቃይ ላይ ይገኛሉ። የታሰሩት ለጭቁኑ የአማራ ህዝብ ድምፅ ስለሆኑ ብቻ ነ...
06/04/2026

አቶ ክርስቲያን ታደለ የፓርላማ አባል ቢሆኑም ያለመከሰስ መብታቸው ተነስቶ፣ የህክምና ክልከላ እየተደረገባቸው በእስር ስቃይ ላይ ይገኛሉ። የታሰሩት ለጭቁኑ የአማራ ህዝብ ድምፅ ስለሆኑ ብቻ ነው። አማራ ሆይ፣ የጮኸልህን ድምፅ አታጥፋ! ዝምታህን ሰብረህ ለፍትህ ጩህ!
> "

ለመላው የአማራ ህዝብ ድምፅ በመሆኗ በእስር እንግልት ላይ ትገኛለች! ድምፅ የሆነችለት ህዝብ ግን ለእሷ ድምፁን አጥፍቷል🤔ጋዜጠኝነት ወንጀል አይደለም። ፍትህ ለመስከረም አበራ!
06/04/2026

ለመላው የአማራ ህዝብ ድምፅ በመሆኗ በእስር እንግልት ላይ ትገኛለች! ድምፅ የሆነችለት ህዝብ ግን ለእሷ ድምፁን አጥፍቷል🤔
ጋዜጠኝነት ወንጀል አይደለም። ፍትህ ለመስከረም አበራ!

Address

Sheger
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Voice Of Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share