25/08/2026
ፕሬዝዳንት ይስሃቅ ሄርዞግ፡ የሀገር ውስጥ ደህንነት መስሪያ ቤት “ሻባክ”በሃይማኖት ካሳው ፍለጋ ላይ እየተሳተፈ ነው አሉ!
የእስራኤል ፕሬዝዳንት ይስሃቅ ሄርዞግ ከሃይማኖት ካሳው ቤተሰብ ጋር ባደረጉት ውይይት፣ የሀገር ውስጥ ደህንነት መስሪያ ቤት በጉዳዩ ላይ በቀጥታ መሳተፉን ገልጸዋል።
ፕሬዝዳንቱ እንደተናገሩት የደህንነት መስሪያ ቤቱ በሃይማኖት ፍለጋ እና መረጃዎችን በማጣራት ረገድ የበኩሉን ሚና እየተጫወተ ይገኛል ብለዋል::
“ሻባክ” ከሀገሪቱ ዋና የደህንነት ተቋም “ሞሳድ” ያልተናነሰ ሀይል እንዳለዉ ይነገራል:: በሁለቱ የሀገሪቱ ከፍተኛ የደህንነት ተቋማት ያለዉ ብቸኛ ልዮነት “ሻባክ” በሀገሪቱ ዉሰጥ የሚፈፀሙትን ከፍተኛ ወንጀሎች ሲቆጣጠር “ሞሳድ” ደንበር ተሻጋሪ የደህንነት ሰራዎችን ይሰራል! ተብሏል::