Ethiopian Human Rights Commission

Ethiopian Human Rights Commission EHRC is an independent NHRI tasked with the promotion and protection of human rights in Ethiopia.

 ፦ በሰብአዊ መብቶች እና ሽግግር ፍትሕ ላይ የተካሄደ የዐቅም ግንባታ ዐውደ ጥናት..የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት ጋር በመተባበር በሰብአ...
07/05/2026

፦ በሰብአዊ መብቶች እና ሽግግር ፍትሕ ላይ የተካሄደ የዐቅም ግንባታ ዐውደ ጥናት..

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት ጋር በመተባበር በሰብአዊ መብቶች እና በሽግግር ፍትሕ ላይ ያተኮረ የዐቅም ግንባታ ዐውደ ጥናት ሚያዝያ 7 እና 8 ቀን 2018 ዓ.ም. በአሶሳ ከተማ አካሂዷል፡፡ በዚህ ዐውደ ጥናት የክልሉ ሕግ አውጪ፣ ተርጓሚ እና አስፈጻሚ አካላት፣ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤን ጨምሮ፣ የጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ የፍትሕ ቢሮ፣ የፖሊስ ኮሚሽን፣ የማረሚያ ቤቶች አስተዳደር እና ሌሎች የክልሉ የሥራ ኃላፊዎችና ተወካዮች ተሳትፈዋል።

በዐውደ ጥናቱ የሰብአዊ መብቶች ጽንሰ ሐሳቦች እና መሠረታዊ መርሖች፣ ዓለም አቀፍ እና አህጉራዊ የሰብአዊ መብቶች ድንጋጌዎች፣ የኢሰመኮ ሥልጣን፣ ተግባርና ኃላፊነት እንዲሁም ዓለም አቀፍ፣ አህጉራዊ እና ብሔራዊ የሽግግር ፍትሕ መርሖች እና የኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫዎች የተዳሰሱ ሲሆን፣ በእያንዳንዱ ርዕሰ ጉዳይ ላይ የቀረቡ ገለጻዎችን ተከትሎ ተሳታፊዎች በዝርዝር ተወያይተዋል።

በውይይቱ የተሳተፉ የክልሉ ልዩ ልዩ ተቋማት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች የዐቅም ግንባታ ዐውደ ጥናቱ ጠቃሚ መሆኑን ጠቁመው፣ መሰል መድረኮች በተለያዩ ተቋማት ውስጥ ለሚገኙ በርካታ ሠራተኞች ተደራሽ እንዲሆኑ ጠይቀዋል። በተጨማሪም ሰብአዊ መብቶችን ማስከበርና ማስፋፋት የሁሉም ባለድርሻ አካላት የጋራ ኃላፊነት መሆኑንም አጽንዖት ሰጥተዋል።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት ዋና አፈጉባኤ ክብርት ወ/ሮ አስካል አልቦሮ የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥና ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን የሰብአዊ መብቶች ጥበቃ ጉልህ ሚና እንዳለው ገልጸዋል። አክለውም ምክር ቤቱ በክልሉ ያለው የዴሞክራሲ ሥርዓት ይበልጥ እንዲጎለብትና ሰብአዊ መብቶች እንዲከበሩ ለማስቻል የዴሞክራሲ ተቋማት የጋራ ፎረም ለማቋቋም ከኢሰመኮ ጋር እየሠራ መሆኑን አብራርተዋል፡፡

የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ ባለፉት ዓመታት በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባጋጠሙ የጸጥታ ችግሮች ሳቢያ የተከሰቱ እና የተባባሱ የሰብአዊ መብቶች ጉዳዮችን በመጥቀስ፣ የጥሰት መንስዔዎችን መፍትሔ መስጠት እንደሚገባ በአጽንዖት ገልጸዋል፡፡ ዋና ኮሚሽነሩ የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በመድረኩ ያገኙትን ግንዛቤ ወደ ተግባር በመቀየር በክልሉ ለሚታዩ የሰብአዊ መብቶች ጥበቃ ተግዳሮቶች ተገቢውን ምላሽ እንደሚሰጡ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል። ሰላም ለሰብአዊ መብቶች ጥበቃ መሠረታዊ ቅድመ-ሁኔታ መሆኑን በመጥቀስ ለዘላቂ ሰላም ቅድሚያ እንዲሰጥም አሳስበዋል። በመጨረሻም ክልሎች በኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ ሥር የተጣለባቸውን ኃላፊነት መወጣት እንዳለባቸው በመግለጽ፣ በሀገራዊ የሽግግር ፍትሕ ሂደት ውስጥ ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።

🔗 https://ehrc.org/?p=37606

🇪🇹

በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።

የሲቪክ ምኅዳርን ማስፋት እና የሰብአዊ መብቶች ተሟጋቾች ጥበቃን ማጠናከር ላይ ያተኮረ ምክክር..የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከአፍሪካ ብሔራዊ የሰብአዊ መብቶች ተቋማት ትስስ...
06/05/2026

የሲቪክ ምኅዳርን ማስፋት እና የሰብአዊ መብቶች ተሟጋቾች ጥበቃን ማጠናከር ላይ ያተኮረ ምክክር..

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከአፍሪካ ብሔራዊ የሰብአዊ መብቶች ተቋማት ትስስር (Network of African National Human Rights Institutions (NANHRI)) ጋር በመተባበር በኢትዮጵያ ያለውን የሲቪክ ምኅዳር ለማስፋት እና የሰብአዊ መብቶች ተሟጋቾች ጥበቃን ለማጠናከር ያለመ የምክክር መድረክ ሚያዝያ 7 እና 8 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ አካሂዷል። በምክክሩ ከተ.መ.ድ. የሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር የምሥራቅ አፍሪካ ቢሮ (Office of the High Commissioner for Human Rights-East African Regional Office (OHCHR-EARO))፣ ከአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን የፖለቲካ፣ የሰላም እና ጸጥታ ክፍል፣ ከዴንማርክ ሰብአዊ መብቶች ኢንስቲትዩት (Danish Human Rights Institution – DHRI)፣ ከኬንያ ሰብአዊ መብቶች ብሔራዊ ኮሚሽን (Kenya National Commission for Human Rights – KNCHR) እና ከተለያዩ የሲቪክ ማኅበረሰብ ድርጅቶች የተውጣጡ ተወካዮች ተሳትፈዋል፡፡

በምክክሩ የሲቪክ ምኅዳርን እና የሰብአዊ መብቶች ተሟጋቾች ጥበቃን የተመለከቱ ዓለም አቀፍ እና አህጉራዊ የሕግ ማዕቀፎች እና መመዘኛዎች ላይ ያተኮሩ ጽሑፎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል። በተጨማሪም ኢሰመኮ ክትትል፣ ጥናት እና ሕዝባዊ መድረክ (Public Inquiry) በማከናወን እንዲሁም ሞዴል ሕግ በማዘጋጀት የሲቪክ ምኅዳሩን ለማስፋት እና የሰብአዊ መብቶች ተሟጋቾች መብቶችን ለማስጠበቅ ሲያከናውን የቆያቸው ተግባራት በመድረኩ ቀርበዋል።

የምክክሩ ተሳታፊዎች በኢትዮጵያ የተሻለ የሲቪክ ምኅዳር ለመፍጠር የሕግ ማዕቀፎችን ማሻሻል፣ የሰብአዊ መብቶች ተሟጋቾች በአካል እና በበይነመረብ (Online) የመብቶች ጥሰት እንዳይደርስባቸው በቂ ጥበቃ መስጠት እንደሚገባ አጽንዖት ሰጥተዋል።

የአፍሪካ ብሔራዊ የሰብአዊ መብቶች ተቋማት ትስስር (Network of African National Human Rights Institutions (NANHRI)) ዋና ዳይሬክተር ጊልበርት ሰቢሆጎ (Gilbert Sebihogo) የሲቪክ ምኅዳርን ለማስፋት እና የሰብአዊ መብቶች ተሟጋቾች ጥበቃን ለማጠናከር የመንግሥት ቁርጠኝነት እንዲሁም የኢሰመኮ እና የሲቪክ ማኅበረሰብ ድርጅቶች ትብብር ወሳኝ መሆኑን አስረድተዋል።

የኢሰመኮ የሲቪል እና የፖለቲካ መብቶች ሥራ ክፍል ዳይሬክተር መቅደስ አመኑ የመደራጀት፣ሐሳብን በነጻነት የመግለጽ እና የመረጃ ነጻነት መብቶች መከበር የሲቪክ ምኅዳርን ለማስፋት እና የሰብአዊ መብቶች ተሟጋቾች ጥበቃን ለማጠናከር ወሳኝ መሆኑን አንስተው የሲቪል ማኅበረብ ድርጅቶችን ጨምሮ ሁሉም ባለድርሻ ለተግባራዊነቱ በቅንጅት እንዲሠሩ ጥሪ አስተላልፈዋል።

🔗 https://ehrc.org/?p=37584

🇪🇹

በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።

 #ሶማሊ፦ በአርብቶ አደር አካባቢዎች ትምህርት የማግኘት መብት አተገባበርን አስመልክቶ የተካሄደ ምክክር..የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በሶማሊ ክልል በተመረጡ የአርብቶ አደር...
05/05/2026

#ሶማሊ፦ በአርብቶ አደር አካባቢዎች ትምህርት የማግኘት መብት አተገባበርን አስመልክቶ የተካሄደ ምክክር..

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በሶማሊ ክልል በተመረጡ የአርብቶ አደር አካባቢዎች የትምህርት መብት አተገባበርን አስመልክቶ ባከናወነው የሰብአዊ መብቶች ክትትል የተለዩ ግኝቶች እና የተሰጡ ምክረ ሐሳቦች ላይ መጋቢት 29 ቀን 2018 ዓ.ም. በጅግጅጋ ከተማ ከባለድርሻ አካላት ጋር ምክክር አካሂዷል። በውይይቱ ከሶማሊ ክልል ትምህርት ቢሮ፣ መስኖና ቆላማ አካባቢዎች፣ ሴቶችና ሕፃናት፣ አደጋ ሥጋት አመራር ቢሮዎች እንዲሁም ከተለያዩ የወረዳ ትምህርት ጽሕፈት ቤቶች የተውጣጡ ተወካዮች ተሳትፈዋል።

በመድረኩ ኢሰመኮ የትምህርት መብት በዓለም አቀፍና ሀገራዊ የሕግ ማዕቀፎች የተሰጠውን ጥበቃ ጨምሮ በአርብቶ አደር አካባቢዎች የመብቱ አተገባበር ላይ ባከናወነው ክትትል የተለዩ ግኝቶች ቀርበው ሰፊ ውይይት ተደርጎባቸዋል።

በውይይቱ በከፍተኛ ንፋስ ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸው ትምህርት ቤቶችን መልሶ መገንባት እና የመሠረተ ልማት ዝርጋታን ማስፋፋት እንዲሁም የመምህራንን ዕውቀት እና ክህሎት ለማሳደግ ቀጣይነት ያለው ስልጠና መስጠት አስፈላጊ መሆኑ ተገልጿል። በተጨማሪም ተንቀሳቃሽ እና አዳሪ ትምህርት ቤቶችን ማስፋፋትን ጨምሮ ከአርብቶ አደሩ የኑሮ ዘይቤ ጋር የሚጣጣሙ የትምህርት ስልቶችን መቀየስ አጽንዖት ሊሰጠው እንደሚገባ ተመላክቷል፡፡

የውይይቱ ተሳታፊዎች አርብቶ አደሮች የሚገጥሟቸውን ተግዳሮቶች በዘላቂነት ለመፍታት በየደረጃው ያሉ የመንግሥት አካላት፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች እና ሌሎች የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መሥራት እንዳለባቸው ገልጸዋል።

የኢሰመኮ የማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ መብቶች ሥራ ክፍል ኃላፊ ሃዊ አስፈው፣ በአርብቶ አደር አካባቢዎች የትምህርት መብትን ለማረጋገጥ ከማኅበረሰቡ የኑሮ ዘይቤ ጋር ማጣጣምና ተደራሽነቱን ማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል። አክለውም የመሠረተ ልማት ችግር እና ሌሎች ተግዳሮቶችን ለመቅረፍ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የተቀናጀ ጥረት እንዲያደርጉና የመፍትሔ እርምጃዎችን እንዲወስዱ ጥሪ አቅርበዋል።

🔗 https://ehrc.org/?p=37559

🇪🇹

በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።

የአዳዲስ ኮሚሽነሮች የትውውቅ እና የመልካም ምኞት መግለጫ መርኃ ግብር..የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በቅርቡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተሾሙለትን ምክትል ዋና ኮሚሽነር ...
02/05/2026

የአዳዲስ ኮሚሽነሮች የትውውቅ እና የመልካም ምኞት መግለጫ መርኃ ግብር..

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በቅርቡ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተሾሙለትን ምክትል ዋና ኮሚሽነር እና የዘርፍ ኮሚሽነሮች ከሠራተኞች እና ከአጋር አካላት ጋር የማስተዋወቂያ መርኃ ግብር ሚያዚያ 22 ቀን 2018 ዓ.ም. አዲስ አበባ በሚገኘው ዋና መሥሪያ ቤት አካሂዷል። በመርኃ ግብሩ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እና አባላትን ጨምሮ የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀነራል የኑስ ሙሉ፣ ጥሪ የተደረገላቸው አጋር አካላት እና የኢሰመኮ ሠራተኞች ተገኝተዋል።

በመርኃ ግብሩ ላይ የኢሰመኮ ምክትል ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ሚዛኔ አባተ፣ የሴቶች እና የሕፃናት መብቶች ኮሚሽነር አሸነፈች አበበ፣ የሰብአዊ መብቶች ትምህርት እና ስልጠና ኮሚሽነር በዳሳ ለሜሳ፣ እንዲሁም የአካል ጉዳተኞች እና አረጋውያን መብቶች ኮሚሽነር አቶ መሀመድ አህመድ ዝርዝር የሙያ፣ የክህሎት እና የትምህርት መግለጫ ቀርቧል። ተሳታፊዎች በበኩላቸው በገለልተኛ አስመራጭ ኮሚቴ አማካኝነት ግልጽ የሆነ የሕዝብ ጥቆማና የመመልመያ ሂደትን ተከትሎ ለተሾሙ ኮሚሽነሮች ደስታቸውን ገልጸው ውጤታማ የሥራ ዘመን እንዲሆንላቸው መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል።

በተጨማሪም በተባበሩት መንግሥታት የኢኮኖሚ፣ ማኅበራዊ እና ባህላዊ መብቶች ኮሚቴ (CESCR) እና በአፍሪካ የሕፃናት መብቶችና ደኅንነት የባለሙያዎች ኮሚቴ (ACERWC) አባልነት ተመርጠው ለሀገራቸውና ለኢሰመኮ ኩራት ለሆኑት የሥራ ባልደረቦች ዶ/ር አብዲ ጅብሪል እና አልባብ ተስፋዬ የእውቅና እና የእንኳን ደስ አላችሁ መርኃ ግብር ተከናውኗል።

የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀነራል የኑስ ሙሉ ክፍት የነበሩ የአመራር ቦታዎች ዘርፉን በአግባቡ በሚረዱ ባለሙያዎች መሞላታቸው ኢሰመኮ በተሟላ ዐቅሙ ተቋማዊ ተልዕኮውን እንዲወጣ ያስችለዋል ብለዋል። አክለውም የሰብአዊ መብቶችን የማክበርና የማስከበር ሥራ በአንድ ተቋም ብቻ የሚሳካ ባለመሆኑ፣ በማረሚያ ቤት የሚገኙ ሰዎችን መብቶች በተሟላ ሁኔታ ለማረጋገጥ ከኢሰመኮ ጋር በቅርበት እንደሚሠሩ ጠቁመዋል።

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ አቶ እውነቱ አለነ፣ ተሿሚዎቹ መስፈርቱን ካሟሉ 72 ዕጩዎች መካከል በከፍተኛ ውድድር እንደተመረጡ አስረድተዋል። የሰብአዊ መብቶችን መጠበቅ እና ማስፋፋት “ለራሳችን ስንል የምንሠራው ሥራ ነው” ያሉት ሰብሳቢው፤ ምክር ቤቱ የኢሰመኮን ተቋማዊ ነጻነት እና ገለልተኝነት ጠብቆ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልጸዋል። ተሿሚዎቹም የሕዝብ እና የመንግሥትን አደራ በሕግ እና በመርሕ ላይ በመጽናት እንዲወጡ አሳስበዋል።

የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ አብዛኛዎቹ ተሿሚዎች በኢሰመኮ ውስጥ በተለያዩ ኃላፊነቶች ሲያገለግሉ የነበሩ መሆናቸው ለተቋሙ ተጨማሪ ዐቅም እንደሚፈጥር ገልጸዋል። ይህም ተቋሙ በሰብአዊ መብቶች ዘርፍ ለበርካታ አመራሮችና ባለሙያዎች መፍለቂያ እየሆነ መምጣቱን የሚያሳይ ተስፋ ሰጪ እርምጃ መሆኑን ጠቅሰዋል። ዋና ኮሚሽነሩ አክለውም፤ በሥራ ዘመናቸው ኢሰመኮ ነጻነቱን ጠብቆ፣ የሰብአዊ መብቶች ማስከበር ተግባሩ ተጠናክሮ እና የሚሰጣቸው ምክረ ሐሳቦች ተፈጻሚነት ተሻሽሎ ማየት ዋነኛ ዓላማቸው መሆኑን ገልጸው፣ ተሿሚ ኮሚሽነሮች ይህንን እውን ለማድረግ የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ መክረዋል።

🔗 https://ehrc.org/?p=37496

🇪🇹

በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።

ሰብአዊ መብቶችን ማስፋፋት:- በ2018 በጀት ዓመት በ3ኛው ሩብ ዓመት የተሰጡ ስልጠናዎች..የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከጥር 1 ቀን 2018 ዓ.ም. እስከ መጋቢት 30 ቀን...
28/04/2026

ሰብአዊ መብቶችን ማስፋፋት:- በ2018 በጀት ዓመት በ3ኛው ሩብ ዓመት የተሰጡ ስልጠናዎች..

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከጥር 1 ቀን 2018 ዓ.ም. እስከ መጋቢት 30 ቀን 2018 ዓ.ም. ባለው የበጀት ዓመቱ 3ኛ ሩብ ዓመት በሰብአዊ መብቶች እና በሽግግር ፍትሕ ላይ ያተኮሩ ተከታታይ የአሰልጣኞች ስልጠናዎችን በተለያዩ ከተሞች ሰጥቷል።

የአረጋውያን ሰብአዊ መብቶች እንዲሁም መብቶቹን ለማስከበርና ለማስፋፋት የሚያስችሉ ክህሎቶችን በተመለከተ ከየካቲት 2 እስከ 6 ቀን 2018 ዓ.ም. ከሲዳማ እና ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልሎች ለተውጣጡ የአረጋውያን እና የጡረተኞች ማኅበራት አመራሮችና አባላት በሃዋሳ እና በአርባ ምንጭ ከተሞች፤ ከመጋቢት 14 እስከ 17 ቀን 2018 ዓ.ም. ለትግራይ አረጋውያን ማኅበር አባላት በመቀሌ ከተማ፤ እንዲሁም ከመጋቢት 21 እስከ 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ለሐረሪ ክልል አረጋውያን እና ጡረተኞች ማኅበራት አባላት በሐረር ከተማ ስልጠናዎች ተሰጥተዋል። ስልጠናዎቹ የስልጠናው ተሳታፊዎች አረጋውያን ላይ የሚፈጸሙ የመብት ጥሰቶችን ሪፖርት እና ውትወታ የማድረግ ክህሎታቸውን እንዲያዳብሩ የሚያስችሉ ተግባራዊ ልምምዶችን ያካተቱ ናቸው።

በተጨማሪም ኢሰመኮ በሕፃናት መብቶች ጥበቃ ዙሪያ ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ አባላት እና የሥራ ኃላፊዎች ከየካቲት 10 እስከ 13 ቀን 2018 ዓ.ም. በቢሾፍቱ ከተማ ስልጠና ሰጥቷል። ይህ ስልጠና ሕፃናት በወንጀል ድርጊት ተሳታፊ ወይም ተጎጂ በሚሆኑበት ጊዜ ሊከበሩላቸው የሚገቡ መብቶችን በተመለከተ በስልጠናው የተሳተፉ አካላትን ግንዛቤ ለማሳደግ ያለመ ሲሆን፣ ተሳታፊዎች በቡድን ውይይት አማካኝነት ልምድ ተለዋውጠዋል። በሌላ በኩል፣ ከባሌ ዞን እና ከሮቤ ከተማ የሴቶች እና የሕፃናት ጽሕፈት ቤቶች ለተውጣጡ ባለሙያዎች ከየካቲት 30 እስከ መጋቢት 4 ቀን 2018 ዓ.ም. የሴቶች መብቶች ላይ ያተኮረ ስልጠና በሮቤ ከተማ ተሰጥቷል።

የታራሚዎችን አያያዝ በተመለከተ፣ ከማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የተለያዩ ማረሚያ ቤቶች እና ከፍትሕ ቢሮ ለተውጣጡ የሥራ ኃላፊዎች ከየካቲት 9 እስከ 13 ቀን 2018 ዓ.ም. በሆሳዕና ከተማ፤ እንዲሁም ከአማራ ክልል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን እና ከስድስት ማረሚያ ቤቶች ለተውጣጡ የማረሚያ ቤት ፖሊስ አባላት ከመጋቢት 21 እስከ 25 ቀን 2018 ዓ.ም. በባሕር ዳር እና ኮምቦልቻ ከተሞች ስልጠና ተሰጥቷል። በተጨማሪም የፖሊስ አባላት ሰብአዊ መብቶችን የማክበርና የማስከበር ዐቅም ለመገንባት ያለመ ስልጠና በወንጀል መከላከልና ምርመራ ዘርፍ ለተሰማሩ የፖሊስ አባላት ከየካቲት 9 እስከ 13 ቀን 2018 ዓ.ም. በሆሳዕና ከተማ፤ ከየካቲት 16 እስከ 20 ቀን 2018 ዓ.ም. በደሴ ከተማ እና ከመጋቢት 14 እስከ 17 ቀን 2018 ዓ.ም. በቢሾፍቱ ከተማ ስልጠናዎች ተሰጥተዋል። ስልጠናዎቹ የታራሚዎች እና ተጠርጣሪዎች ሰብአዊ መብቶች አያያዝን በተመለከተ ዕውቀት፣ አመለካከት እና ክህሎትን ለመገንባት የሚያግዙ ናቸው።

በሌላ በኩል ኢሰመኮ በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች መብቶች ዙሪያ ከሐረሪ እና ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች የተውጣጡ ለሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች አገልግሎት ለሚሰጡ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች ከየካቲት 30 እስከ መጋቢት 4 ቀን 2018 ዓ.ም. በሐረር እና በአሶሳ ከተሞች ስልጠና ሰጥቷል፡፡ የስልጠናው ተሳታፊዎችም በስልጠናው ያገኙትን የሰብአዊ መብቶች ዕውቀት፣ እና ክህሎት በመጠቀም ተግባራዊ እርምጃ ለመውሰድ ያላቸውን ተነሳሽነት ገልጸዋል፡፡
በሌላ በኩል ኢሰመኮ ከፕሮጀክት ኤክስፒዳይት ጀስቲስ (Project Expedite Justice) ጋር በመተባበር የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጀቶች በሽግግር ፍትሕ ሂደት ውስጥ ያላቸውን ሚና እንዲወጡ ለማስቻልና የሽግግር ፍትሕ ሂደትን ለማጠናከር ከአማራ ክልል ለተውጣጡ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ከጥር 4 እስከ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዳማ ከተማ ስልጠና ሰጥቷል። በተመሳሳይ የኪነ ጥበብ እና ሥነ ጥበብ ባለሙያዎች በሽግግር ፍትሕ ትግበራ ወቅት ያላቸውን ሚና በተመለከተ ከድሬዳዋ እና ከሐረር ለተውጣጡ ባለሙያዎች ከጥር 26 እስከ 30 ቀን 2018 ዓ.ም. በድሬዳዋ፣ እንዲሁም ከጅማ እና ከአጋሮ ለተውጣጡ ባለሙያዎች ከየካቲት 16 እስከ 20 ቀን 2018 ዓ.ም. ስልጠናዎች ተሰጥተዋል።

በተጨማሪም በሰብአዊ መብቶች እና በሽግግር ፍትሕ ዙሪያ የወጣቶችን ሚና ለማሳደግ ቀደም ሲል የአሰልጣኞች ስልጠና የወሰዱ የሶዶ ከተማ የወጣቶች ማኅበራት አመራሮች፣ ከጥር 28 እስከ 30 ቀን 2018 ዓ.ም. ለ40 አባላቶቻቸው በሶዶ ከተማ ስልጠና ሰጥተዋል፡፡ ኢሰመኮ የሰብአዊ መብቶች እሴቶች እና መርሖች እንዲሁም ዓለም አቀፍ እና ሀገራዊ የአካል ጉዳተኞች መብቶችን በተመለከተ ከመጋቢት 22 እስከ 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ለአካል ጉዳተኞች ማኅበራት አመራሮች እና አባላት በጋምቤላ ከተማ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል።

🔗 https://ehrc.org/?p=37391

🇪🇹

በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።

The Ethiopian Human Rights Commission (EHRC) is an independent federal state body established by Parliament as the national human rights institution with the mandate for the promotion and protection of human rights.

6ኛው ዓመታዊ ሀገር አቀፍ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሰብአዊ መብቶች ምስለ-ችሎት (Human Rights Moot Court) ውድድር ተጠናቀቀ..በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመ...
25/04/2026

6ኛው ዓመታዊ ሀገር አቀፍ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሰብአዊ መብቶች ምስለ-ችሎት (Human Rights Moot Court) ውድድር ተጠናቀቀ..

በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አዘጋጅነት ሲካሄድ የነበረው 6ኛው ዓመታዊ ሀገር አቀፍ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሰብአዊ መብቶች ምስለ-ችሎት (6th National High Schools Human Rights Moot Court Competition) ውድድር ሚያዝያ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ በተካሄደ የፍጻሜ ውድድር ተጠናቋል፡፡ ውድድሩ ከጥር 23 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በክልሎች እና በሀገር አቀፍ ደረጃ ሲካሄድ የቆየ ሲሆን በ12 ክልሎች እና 2 ከተማ አስተዳደሮች ከሚገኙ 91 ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ 182 ተወዳዳሪ ተማሪዎች ተሳትፈውበታል።

በክልሎች እና በከተማ አስተዳደር ደረጃ በተካሄደው የምስለ ችሎት ውድድር ከፍተኛ ነጥብ ያስመዘገቡ 8 ቡድኖች ወደ አዲስ አበባ ከተማ በመምጣት የሩብ እና የግማሽ ፍጻሜ ሀገር አቀፍ የቃል ክርክር ውድድር ከሚያዝያ 12 እስከ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. ሲያደርጉ ቆይተው የፍጻሜ ውድድር አድርገዋል፡፡

በፍጻሜ ውድድሩ ተማሪ መርስን ተፈራ እና ተማሪ ቦንቱ ታደሰ ከአዲስ አበባ ከተማ እቴጌ መነን የሴቶች አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እንዲሁም ተማሪ ይዲድያ ብሩክ እና አናቤል ነብዩ ከደብረብርሃን ከተማ ሀይሌ ማናስ አካዳሚ አመልካችና ተጠሪን ወክለው የቃል ክርክራቸውን አካሂደዋል። በዚሁ መሠረት:-
ተማሪ መርሰን ተፈራ እና ቦንቱ ታደሰ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እቴጌ መነን የሴቶች አዳሪ ትምህርት ቤት የፍጻሜ ውድድሩ አሸናፊዎች ሆነዋል፡፡

ተማሪ አናቤል ነብዩ ከደብረብርሃን ከተማ ሀይሌ ማናስ አካዳሚ የውድድሩ ምርጥ የቃል ተከራካሪ በመሆን ያሸነፈች ሲሆን፤

ተማሪ ኪብሮን ነጻነት እና ተማሪ ዲኒያ ናስር ከሸገር ከተማ ሒል ቶፕስ አካዳሚ በምርጥ የጽሑፍ ክርክር አሸናፊዎች ሆነዋል፡፡

የዘንድሮው ውድድር ምናባዊ ጉዳይ ትኩረቱን ያደረገው “የመማር መብት በግጭት ዐውድ ውስጥ” (The Right to Education in the Context of Armed Conflict) ላይ ሲሆን፣ የትምህርት መብትን በተለይም የትምህርት ተገኝነትን (availability) ተደራሽነትን (accessibility)፣ ተቀባይነትን (acceptability) እና ተላማጅነትን (adaptability)፤ በግጭት ዐወድ ውስጥ የትምህርት መብት መርሖችን እንዲሁም የትምህርት መብትን ከማክበር፣ ማስከበር እና ማሟላት አኳያ የመንግሥት መሠረታዊ ግዴታዎችን የተመለከቱ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች መመዘኛዎች ላይ ተመሥርቷል። ይህም በግጭት ዐውድ ውስጥ የትምህርት ቀጣይነትን የተመለከቱ የሰብአዊ መብቶች መመዘኛዎችን በማንሳት ተወዳዳሪ ተማሪዎች በመብቶቹ ዙሪያ ጥልቅ ውይይትና ንባብ እንዲያደርጉ እና ዕውቀት እንዲያካብቱ አጋጣሚ ፈጥሯል።

የምስለ ችሎት ውድድሩ በሕግና ሰብአዊ መብቶች ባለሙያዎች የተዳኘ እና የመደበኛ ፍርድ ቤት ክርክር ሥርዓትን የተከተለ ሲሆን፤ ተወዳዳሪ ተማሪዎች ተገቢው ገለጻና አጭር ስልጠና ከተሰጣቸው በኋላ ለውድድሩ በተመረጠው ምናባዊ የሰብአዊ መብቶች ጉዳይ (hypothetical case) ላይ አመልካች እና ተጠሪን በመወከል የጽሑፍ እና የቃል ክርክር ያደረጉበትም ነው።

በዚህ የፍጻሜ ውድድር ላይ የኢሰመኮ ኮሚሽነሮችን ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የክልል ትምህርት ቢሮዎች ተወካዮች፣ መንግሥታዊ እና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ተወካዮች፣ የተወዳዳሪ ተማሪዎች ቤተሰቦች እንዲሁም ተማሪዎች ተገኝተዋል፡፡

የኢሰመኮ ምክትል ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ሚዛኔ አባተ ኢሰመኮ የወጣቶችን የሰብአዊ መብቶች ግንዛቤና ክህሎት ለማሰደግ እንዲሁም አመለካከት ለመቀየር ከሚጠቀምባቸው ስልቶች መካከል የምስለ ችሎት ውድድር አንዱ መሆኑን ጠቅሰው፣ በግጭት ዐውድ ውስጥ የትምህርት ቀጣይነትን ማረጋገጥ ሀገር ተረካቢ ትውልድ በመፍጠር ሀገራት ከግጭት ዐውድ ውስጥና ከሰብአዊ መብቶች ጥሰተቶች አዙሪት ሊወጡ የሚችሉበት የተሻለ አማራጭ መሆኑን ተረድተው፣ ይህንኑ በውድድሩ የተለያዩ ዙሮች ላይ ለተሳተፉ ተማሪዎች፣ የትምህርት ቤት ማኅበረሰብ አባላት፣ ወላጆች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ማስገንዘብ እንደቻሉ ገልጸዋል። አክለውም “6ኛው ሀገር አቀፍ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች የሰብአዊ መብቶች ምስለ ችሎት ውድድር ወቅታዊ እና ሀገራዊ የሰብአዊ መብቶች አጀንዳዎችን ተገንዘቦ አስተዋጽዖ የማድረግ ዐቅም ያለው ትውልድ በማፍራት ሰብአዊ መብቶች ባህል የሆኑባት ኢትዮጵያን እውን ማድረግ እንድንችል ዕድል የሠጠን ነው” ብለዋል።

🔗 https://ehrc.org/?p=37324

🇪🇹

በነጻ የስልክ መስመራችን 7307 ላይ በመደወል የሰብአዊ መብቶች ጥሰት አቤቱታ ማቅረብ ወይም ጥቆማ መስጠት ይችላሉ።

24/04/2026

🎥 Live Now: Final Moot Court Competition

24/04/2026

We are live from the Final Round of the 6th High Schools Human Rights Moot Court Competition.
Watch as top students present their final arguments on “The Right to Education in Situations of Armed Conflict.”
Join the live stream and follow the competition.

⏸️ Short BreakWe’ll resume the Final Moot Court Competition shortly. Stay tuned!
24/04/2026

⏸️ Short Break

We’ll resume the Final Moot Court Competition shortly. Stay tuned!

24/04/2026

We are live from the Final Round of the 6th High Schools Human Rights Moot Court Competition.

Watch as top students present their final arguments on “The Right to Education in Situations of Armed Conflict.”

Join the live stream and follow the competition.

Address

Headquarters: Meskel Square, On Bole Airport Road Next To Hyatt Regency Hotel
Addis Ababa

Telephone

+251115504031

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Human Rights Commission posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Ethiopian Human Rights Commission:

Share