16/08/2026
የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት የመስክ ግምገማ (Site Visit) ካጠናቀቀ በኋላ፣ ተወዳዳሪ ድርጅቶችን በየዘርፋቸው በጋራ የመገምገም ሥራውን አጠናክሮ ቀጥሏል!
ቅዳሜ ነሐሴ 09 ቀን 2018 ዓ.ም፤ በ13ኛው ዙር አገር አቀፍ የጥራት ሽልማት ውድድር ከተሳተፉ የማኑፋክቸሪንግ ድርጅቶች መካከል የሃይኒከን ኢትዮጵያ፣ የኢስት አፍሪካ ቦትሊንግ (ኮካ ኮላ)፣ ኮማሪ ቢቬሬጅ፣ ዳሸን ቢራ ፋብሪካ፣ ቶፕ ውኃ፣ ዲና ምግብ ማቀነባበሪያ፣ ኢትዮ ኤዥያ፣ የሴንቸሪ ቢዝነስ ግሩፕ እና የሌሎችንም ድርጅቶች የመስክ ምልከታ ያደረጉ የቴክኒክ ኮሚቴ አባላት በጋራ ተገኝተዋል።
የኮሚቴው አባላት በተናጥል የገመገሟቸውን ኩባንያዎች ውጤት እርስ በእርስ የማጣጣም (Harmonize የማድረግ) እና የጋራ መለኪያዎችን የማስተካከል (Calibrate የማድረግ) ወሳኝ ሥራዎችን በጋራ አከናውነዋል።
ይህ በየዘርፉ የሚደረግ የጋራ ግምገማ፤ በባለሙያዎቹ መካከል ግልጽ ግንኙነትና መናበብ ለመፍጠር እንዲሁም ወጥነት ያለው እና አስተማማኝ የግምገማና የውጤት አሰጣጥ ሥርዓት እንዲኖር ለማስቻል ታስቦ የሚከናወን ነው::
እንዲህ ያሉ ይበልጥ ውጤታማ የሆኑ የጋራ ውይይቶች በቀጣይ የእረፍት ቀናትም (Weekends) ተጠናክረው የሚቀጥሉ ይሆናል።
ጥራት ቀዳሚ አገራዊ አጀንዳ እንዲሆን እንተጋለን!