IEDC I EDC Africa
Innovation and Entrepreneurship Development center

24/12/2023

የእንቆጳ ጉባዔ ነገ ይጀምራል

ትኩረቱን በሥራ ፈጠራ፣ ቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ላይ ያደረገው የእንቆጳ ጉባዔ ከጥቅምት 1 – 2 /2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል፡፡

በሚሊኒየም አዳራሽ በሚካሄደው በዚህ ጉባኤ ሥራ ፈጣሪዎች፣ ቴክኖሎጂ አልሚዎች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ ጀማሪ የንግድ ሥራ ባለሙያዎች፣ ኢንቨስተሮች እንዲሁም የትምህርትና የፋይናንስ ተቋማት ይሳተፋሉ፡፡

የጉባኤው ዓላማ ኢትዮጵያ በዲጂታል የሥራ ፈጠራ ያላትን እምቅ አቅም በማስተዋወቅ በዘርፉ የሚፈጠሩ የሥራ ዕድሎችን ማስፋት ሲሆን ለሁለት ተከታታይ ቀናት በሚካሄደው መርሃ ግብር በክህሎት ልማት፣ በሥራ ዕድል ፈጠራና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ የፓናል ውይይቶች ይካሄዳሉ፡፡

ከውይይቶቹ ጎን ለጎንም ጀማሪ ሥራ ፈጣሪዎች ምርትና አገልግሎታቸውን የሚያስተዋውቁበት እና የገበያ ትስስር የሚፈጥሩበት ኤግዚቢሽን ይካሄዳል፡፡

መስከረም 30/2016 ዓ.ም የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መረጃዎች
በድረገጽ፡- http://mols.gov.et/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/MolsFDRE
ቴሌግራም፦https://t.me/fdre_mols
ቲክቶክ:- mols_official በመወዳጀት ይከታ

24/12/2023
24/12/2023
24/12/2023



በሀገራችን ለመጀመሪያ ጊዜ በፈጠራና ቴክኖሎጂ ላይ የሚሰማሩ አካላት ተቋማዊ ቅንጅት ፈጥረው ለአዳዲስ ሥራ ፈጠራና ጀማሪ ቢዝነሶች ምቹ ሥነ-ምህዳር ለመፍጠር በጋራ የሚሰሩበት The Next Ethiopian StartUp Initiative -NEST) መርሃ ግብር ማስጀመሪያ መርሃ ግብር እየተካሄደ ነው።

በማሰጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የኢፌዴሪ ም/ል ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር አቶ ደመቀ መኮንን፣ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል እና የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ክቡር ዶ/ር በለጠ ሞላን ጨምሮ የተለያዩ ሥራ ፈጣሪዎች፣ የኢንዱስትሪ መሪዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

ጥቅምት 13/2016 ዓ.ም የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መረጃዎች
በድረገጽ፡- http://mols.gov.et/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/MolsFDRE
ቴሌግራም፦https://t.me/fdre_mols
ቲክቶክ:- tiktok.com/

24/12/2023

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when IEDC posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to IEDC:

Share