የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር / Addis Ababa Youth Association

የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር / Addis Ababa Youth Association Addis Abaab Youth Association is a non governmental organization. የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር በኢፌድሪ የበጎ አድራጎትና ማህበራት ኤጀንሲ የካቲት 22 ቀን 1990 ዓ.ም የተመሰረተ ተቀዳሚ ማህበር ነው።

የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር የመጀመሪያው የ National Care Leavers Associations ስፖርት ፌስቲቫል በታላቅ ድምቀት ተጠናቋል።​ሰኔ 7 ቀን 2018 ዓ.ም (አ.አ.ወ.ማ.ኮ)...
14/06/2026

የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር የመጀመሪያው የ National Care Leavers Associations ስፖርት ፌስቲቫል በታላቅ ድምቀት ተጠናቋል።

​ሰኔ 7 ቀን 2018 ዓ.ም (አ.አ.ወ.ማ.ኮ)

​የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር ከተለያዩ አጋር አካላት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የመጀመሪያው የ national Care Leavers Associations የስፖርት ፌስቲቫል በዛሬው ዕለት የወጣቶች ንቁ ተሳትፎ የተስተዋለበት ደማቅ የማጠቃለያ መርሃ ግብር ተጠናቋል።

ማህበሩ የስፖርት ፌስቲቫሉን የመክፈቻ ፕሮግራም በግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ.ም በሰላም የሕፃናት መንደር በእግር ኳስና በእጅ ኳስ ውድድሮች በይፋ ማስጀመሩ ይታወሳል።

በማስጀመሪያ ፕሮግራሙ ላይ የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር ምክትል ፕሬዚዳንት ወጣት ፎሊ ንጉሴ፣ እንዲሁም የማህበሩ አመራሮች የተገኙ ሲሆን፤ የኤስ ኦኤስ (SOS) አልሙናይ youth Association የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም የከተማ አስተዳደሩ የወጣቶችና ስፖርት እና የሴቶችና ሕጻናት ቢሮ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተው የማበረታቻ መልዕክት ማስተላለፋቸው ይታወሳል።

በውድድሩም ላይ፦
◉ ​የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር (Addis Ababa Youth Association)

◉ ሰላም ፍሩት ማህበር ( selam Fruit association )

◉ National 4 care leavers association

◉ ​የኤስ ኦኤስ አልሙናይ youth Association ቡድኖች በከፍተኛ ስፖርታዊ ጨዋነት ተሳትፈዋል።

ወንዶች በእግር ኳስ እንዲሁም ሴቶች በእጅ ኳስ ተጋጥመዋል። ውድድሩ ከስፖርታዊ ፉክክርነቱ ባለፈ በወጣቶቹ መካከል ያለውን የእርስ በእርስ ግንኙነትና ትስስር ይበልጥ ለማጠናከር የተካሄደ በመሆኑ ዓላማውን ስኬታማ በሆነ መልኩ አሳክቷል።

የስፖርት ፌስቲቫሉን ይበልጥ ትርጉም ባለው መልኩ ለማጠቃለል፣ ችግኝ ተከላም የተካሄደ ሲሆን

በአጠቃላይ ​በስፖርት ፌስቲቫሉ ማጠቃለያ ላይ የተገኙት ወጣቶችና የማህበሩ አመራሮች በጋራ በመሆን የአካባቢ ጥበቃ መልዕክታቸውን በችግኝ ተከላ ያሰሙ ሲሆን፤ ወጣቱ በስፖርቱ መስክ ንቁ እንደሆነ ሁሉ ለሀገራዊው የአረንጓዴ ልማትም የበኩሉን አሻራ ማሳረፍ እንዳለበት በተግባር አሳይተዋል።

በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ወቅት በታዛቢነት እና በአስተባባሪነት ለተሳተፉ  ወጣቶች የምስጋና የምስክር ወረቀት ተበረከተ።(የአ.አ.ወ.ማ ሰኔ 5/2018 ዓ.ም)የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር አራዳ ...
12/06/2026

በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ወቅት በታዛቢነት እና በአስተባባሪነት ለተሳተፉ ወጣቶች የምስጋና የምስክር ወረቀት ተበረከተ።

(የአ.አ.ወ.ማ ሰኔ 5/2018 ዓ.ም)

የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር አራዳ ክፍለ ከተማ ቅርንጫፍ በ2018 ዓ.ም በተካሄደው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ወቅት በታዛቢነት፣ በአስተባባሪነት እና በመራጮች ትምህርት ስራዎች ላይ በንቃት ለተሳተፉ ወጣቶች የምስጋና እና የእውቅና ምስክር ወረቀት አበረከተ።

በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር ፕሬዝዳንት ወጣት በረከት ቢርቢርሳ፣ ወጣቶች በምርጫው ሂደት ፍትሃዊነትን፣ ሰላማዊነትን እና ስኬታማነትን ለማረጋገጥ ያበረከቱት ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸው፣ ለሀገራቸው የዴሞክራሲ ግንባታ ያሳዩት ቁርጠኝነትና የላቀ አገልግሎት ከፍተኛ አድናቆት የሚገባው መሆኑን አስገንዝበዋል።

በተመሳሳይ የአራዳ ክፍለ ከተማ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ሃላፊ አቶ የዋላሸት በቀለ፣ “የወጣቶች ተሳትፎ የሀገር የወደፊት ተስፋ ነው” በማለት ወጣቶች በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ስኬት ውስጥ የተጫወቱትን ጉልህ ሚና አድንቀዋል። ለምርጫው ሰላማዊና ውጤታማ አፈፃፀም በግንባር ቀደምትነት የተሰለፉ ወጣቶች ልዩ ምስጋና እንደሚገባቸውም ገልጸዋል።

የአራዳ ቅርንጫፍ ሰብሳቢ ወጣት ማቲዮስ ብርሃኑ በበኩላቸው፣ በክፍለ ከተማው ከ150 በላይ ወጣቶች በታዛቢነት እና በመራጮች ትምህርት ስራዎች ላይ መሳተፋቸውን ገልጸው፣ ማህበሩ በምርጫው ዲሞክራሲያዊ ሂደት ላይ የላቀ አስተዋፅኦ ማበርከቱን አስታውቀዋል። በቀጣይም በወጣቶች ተሳትፎ፣ ተጠቃሚነት እና አቅም ግንባታ ዙሪያ ተጨማሪ ስራዎች እንደሚከናወኑ ጠቁመዋል።

በመጨረሻም የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር አራዳ ቅርንጫፍ፣ በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ወቅት ሀገራዊ ኃላፊነታቸውን በብቃትና በቁርጠኝነት ለተወጡ ወጣቶች የምስክር ወረቀት በማበርከት የክብር እውቅና ሰጥቷል።

"ወጣቶች ለሀገር ግንባታ የጀመሩት ጉዞ ይቀጥላል!" 🇪🇹✨

"በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ አብላጫውን ድምፅ በማግኘት  ወደ ስልጣን የሚመጣ ፓርቲ ሁለንታዊ የወጣቶችን ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት ማረጋገጥ አለበት"  ወጣት በረከት ብርቢርሳ የ​አዲስ አበባ ወጣቶች...
11/06/2026

"በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ አብላጫውን ድምፅ በማግኘት ወደ ስልጣን የሚመጣ ፓርቲ ሁለንታዊ የወጣቶችን ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት ማረጋገጥ አለበት"
ወጣት በረከት ብርቢርሳ የ​አዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር ፕሬዝዳንት

አዲስ አበባ| ሰኔ 4/2018 (አ.አ.ወ.ማ.ኮ.ፅ/ቤት)

የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር የ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ሂደትንና በማህበሩ የተከናወኑ ተግባራትን የገመገመ ሲሆን በዚህም በወቅታዊና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ከሁሉም ክፍለ ከተሞች ከተወጣጡ ከማህበሩ አመራሮች ጋር ሰፊ ውይይት አድርገዋል።

በውይይቱም ላይ ምርጫው ፍትሐዊ፣ተዓማኒ እና ዴሞኪራሳዊ እንዲሆን ከማስተማር ጀምሮ እስከ መታዛብ ድረስ ማህበሩ የአንበሳ ድርሻ መወጣቱን የገለፁት የማህበሩ ፕሬዝዳንት ወጣት በረከት ብርቢርሳ ከምርጫ በኋላም አሸናፊው ፓርቲ የወጣቱን ተሳትፎ እና ተጠቀሚነትን ማረጋገጥ እንደለበት ገልጿል።

ፕሬዝዳንቱ የሀገሪቷ ህዝብ ከ70% የሚገመት ወጣት ስለሆነ ወጣትን ማዕከል ያላደረገ ልማት እና እድገት ውጤት ማምጣት ስለማይችል ወጣትነት ማዕከል አድርገው መስራት አለበት ተብሏል።

ወጣት በረከት በምርጫው የሕዝብ ሉዓላዊ ስልጣን የተንጸባረቀበት ሁኔታ እንደነበር ማህበሩ በታዛቢነት በተሰማራበት ምርጫ ክልሎች ሁሉ መረጋጋጥ የቻለ መሆኑን በመጥቀስ የተገኘው የሕዝብ ድምፅ በሁሉም ወገን መከበር እንዳለበትም አፅኖት ተሰጥቷል።

18ኛው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የመፅሐፍ ዐውደ ርዕይ
08/06/2026

18ኛው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የመፅሐፍ ዐውደ ርዕይ

የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር የመጀመሪያው የ Care Leavers Associations Sport Festival ፕሮግራም እንደቀጠለ ነው ።ግንቦት 30/2018 ዓ.ም (አ.አ.ወ.ማ.ኮ) ይህ የ...
07/06/2026

የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር የመጀመሪያው የ Care Leavers Associations Sport Festival ፕሮግራም እንደቀጠለ ነው ።

ግንቦት 30/2018 ዓ.ም (አ.አ.ወ.ማ.ኮ)

ይህ የስፖርት ፌስቲቫል፣ ወጣቶች ጤናቸውን እንዲጠብቁና አቅማቸውን እንዲያሳድጉ ጉልህ ተሞክሮ ሲሆን በአሁኑ ሰዓትም ውድድሮቹ በታላቅ ድምቀት እንደቀጠሉ ይገኛሉ።

 #በከተማችን ዉበት እና ጽዳት የወጣቶች ሚና ምን ይመስላል? #የኮሪደር ልማት ለወጣቶች የመዝናኛ እና የስራ አማራጭ ከመፍጠር አንጻር ያለዉን ሚና እና በዘርፉ ያሉ ቅንጅታዊ ስራዎች ምን ይመ...
03/06/2026

#በከተማችን ዉበት እና ጽዳት የወጣቶች ሚና ምን ይመስላል?
#የኮሪደር ልማት ለወጣቶች የመዝናኛ እና የስራ አማራጭ ከመፍጠር አንጻር ያለዉን ሚና እና በዘርፉ ያሉ ቅንጅታዊ ስራዎች ምን ይመስላሉ?

ወጣት በረከት ብርቢርሳ የአዲስ አበባ ከተማ ወጣቶች ማህበር ፕሬዝዳንት ልዩ ቆይታ በኢቢሲ አንጋፋው fm አዲስ 97.1 ሀሙስ ግንቦት 27/2018
ከቀኑ 8:30_10 ሰዓት በቀጥታ ስርጭት ይጠብቁ

የአዲስ አበባ ከተማ ወጣቶች ማህበር ፕሬዝዳንት እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራ እና ክህሎት ቢሮ አመራሮች የዶን ቦስኮ ካቶሊክ የቴክኒክ እና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋምን ጎበኙ። ግንቦት 2...
03/06/2026

የአዲስ አበባ ከተማ ወጣቶች ማህበር ፕሬዝዳንት እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራ እና ክህሎት ቢሮ አመራሮች የዶን ቦስኮ ካቶሊክ የቴክኒክ እና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋምን ጎበኙ።

ግንቦት 2018 ዓ/ም (የአ.አ.ወ.ማ.ኮ)

በአዲስ አበባ ከተማ ስራ እና ክህሎት ቢሮ በቢሮ ሃላፊ ማዕረግ ም/ቢሮ ሃላፊ አቶ ሚዴቅሳ ከበደ የተመራ የስራ ቡድን በዶን ቦስኮ የቴክኒክ እና ሙያ ተቋም የስራ እንቅስቃሴዎችን ጎበኙ።

በጉብኝት ፕሮግራም አቶ ሚዴቅሳ ከበደን ጨምሮ የቢሮው በቢሮ ሃላፊ ማዕረግ የቴክኒክ እና ሙያ ተቋማት ዘርፍ ም/ቢሮ ሃላፊ ወ/ሮ ዳግማዊት እና የአዲስ አበባ ከተማ ወጣቶች ማህበር ፕሬዝዳንት ወጣት በረከት ብርቢርሳ እንዲሁም የቢሮው የተለያዩ ዳሮክትሬቶች የተሳተፉበት እንደነበር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ይህንን መሰል የማህበረሰቡን ችግር የሚቀርፉ ተቋማት ያስፈልጉናል ያሉት ምክትል ቢሮ ሃላፊው አቶ ሚዴቅሳ ከበደ በተቋሙ ባዩት ነገር መደነቃቸውን ገልጸው ተቋሙ ለማህበረሰቡ እየሰራ ያለው ነገር የሚበረታታ ነገር መሆኑን ገልፀዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ ወጣቶች ማህበር ፕሬዝዳንት ወጣት በረከት ብርቢርሳ በበኩሉ ይህንን መሰል ተቋማት ለከተማችን ወጣቶች ክህሎት እንዲያዳብሩ በነጻ ይህንን መሰል ትምህርት መሰጠቱ በጣም የሚበረታታ መሆኑን ገልጸው ማህበሩ በቀጣይ ከተቋሙ ጋር በርካታ ስራዎችን ለመስራት ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል።

በቴክኒክ እና ሙያ ተቋማት ደረጃ ትልቅ ተሞክሮ የሚቀሰምበት ተቋም በመሆኑ ለሌሎች ተቋማትም ልምዶችን ማካፈል ይገባል ሲሉ የገለጹት ደግሞ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የስራና ክህሎት ቢሮ በቢሮ ሃላፊ ማዕረግ የቴክኒክ እና ሙያ ተቋማት ዘርፍ ም/ል ቢሮ ሃላፊ ወ/ሮ ዳግማዊት ሲሆኑ በቀጣይም በርካታ ድጋፍፎችን እና በጋራ ስራዎችን በተቋሙ ጋር እንደሚሰራ አሳውቀዋል።

ባጠቃላይ በተቋሙ የሚሰሩ ስራዎችን በመጎብኘት ቀጣይ በጋራ የሚሰሩ ስራዎችን በመለየት ፕሮግራሙ ተጠናቋል።

የአውሮፓ ኅብረት አባል ሀገራት፣ ካናዳ፣ ኖርዌይ እና ስዊዘርላንድ በጋራ ባወጡት መግለጫ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም የተካሄደውን 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ያደነቁ ሲሆን፤ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ...
03/06/2026

የአውሮፓ ኅብረት አባል ሀገራት፣ ካናዳ፣ ኖርዌይ እና ስዊዘርላንድ በጋራ ባወጡት መግለጫ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም የተካሄደውን 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ያደነቁ ሲሆን፤ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ ለፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ለእጩዎችና ለሲቪል ማኅበራት ለምርጫው ስኬት ላበረከቱት አስተዋጽኦ እንዲሁም ለአፍሪካ ኅብረትና ለኢጋድ የምርጫ ታዛቢነት ሚና እውቅና ሰጥተዋል።

የምስጋና መልዕክት ከአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር​ውድ የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር አባላት፣ የከተማችን የፀጥታ አካላት፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስፈጻሚዎች እንዲሁም መላው የአዲስ ...
02/06/2026

የምስጋና መልዕክት ከአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር

​ውድ የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር አባላት፣ የከተማችን የፀጥታ አካላት፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስፈጻሚዎች እንዲሁም መላው የአዲስ አበባ ነዋሪዎች፤
​ሀገራችን ኢትዮጵያ በስኬት ባስተናገደችው 7ተኛው ሀገራዊ ምርጫ ወቅት፣ በ11ዱም ክፍለ ከተሞች ያሳያችሁት የላቀ የዜግነት ተሳትፎ፣ የሰለጠነ ዲሲፕሊን እና የኃላፊነት ስሜት ታሪክ የማይረሳውና በእጅጉ የሚያኮራ ነው።

​የቀኑን የሚያቃጥል ፀሐይ፣ የሌሊቱንና የንጋቱን ቁርና ብርድ፣ እንዲሁም የሥራውን ውጥረት፣ ረሃብና ድካም ሳይበግራችሁ፤ በምርጫ ጣቢያዎች በታዛቢነትና በአስተባባሪነት የተሰማራችሁ ወጣቶቻችን፣ የህዝቡን ደህንነት የጠበቃችሁ የፀጥታ ኃይሎች እና ሂደቱን በገለልተኝነት የመራችሁ አስፈጻሚዎች በሙሉ የከፈላችሁት መስዋዕትነት በቀላሉ የሚገመት አይደለም።
​"ዓይኖቻችሁ በእንቅልፍ እጥረት እየደከሙ፣ አካላችሁ በብርድ እየተፈተነ፣ ለደቂቃ እንኳ ሳታርፉ ለሊቱን ከንጋት ያገናኛችሁት እናንተ የሰላም እና የዲሞክራሲ እውነተኛ ባለአደራዎች ናችሁ።"

​ይህ ታላቅ ሀገራዊ ኩነት በሰላም፣ በፍትሃዊነትና በታማኝነት እንዲጠናቀቅ ላበረከታችሁት ወደር የሌለው አስተዋጽኦ በራሴና በአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር ስም ከልብ የመነጨ የላቀ ምስጋናዬንና አክብሮቴን አቀርባለሁ። ለሀገራችን ሰላምና ለወጣቶች ጥንካሬ ያሳያችሁት ይሄው ቁርጠኝነት ለቀጣይ የጋራ አላማዎቻችን ትልቅ የብርታት ምንጭና ታላቅ አርአያ ነው።

​ለዚህ ስኬት ጊዜያችሁን፣ እውቀታችሁንና ጉልበታችሁን ለሰጣችሁ ውድ የሀገር ባለውለታዎች በሙሉ ምስጋናዬ ይድረስ! ወደፊት በጋራ የምንሻገረውና የምንሰራው ብዙ አብይ ስራ ይጠብቀናል፤ ሁልጊዜም በርቱ!

​ወጣት በረከት ቢርቢርሳ
የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር ፕሬዝዳንት

02/06/2026

Address

Addis Ababa

Telephone

+251111232399

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር / Addis Ababa Youth Association posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር / Addis Ababa Youth Association:

Share