14/06/2026
የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር የመጀመሪያው የ National Care Leavers Associations ስፖርት ፌስቲቫል በታላቅ ድምቀት ተጠናቋል።
ሰኔ 7 ቀን 2018 ዓ.ም (አ.አ.ወ.ማ.ኮ)
የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር ከተለያዩ አጋር አካላት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የመጀመሪያው የ national Care Leavers Associations የስፖርት ፌስቲቫል በዛሬው ዕለት የወጣቶች ንቁ ተሳትፎ የተስተዋለበት ደማቅ የማጠቃለያ መርሃ ግብር ተጠናቋል።
ማህበሩ የስፖርት ፌስቲቫሉን የመክፈቻ ፕሮግራም በግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ.ም በሰላም የሕፃናት መንደር በእግር ኳስና በእጅ ኳስ ውድድሮች በይፋ ማስጀመሩ ይታወሳል።
በማስጀመሪያ ፕሮግራሙ ላይ የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር ምክትል ፕሬዚዳንት ወጣት ፎሊ ንጉሴ፣ እንዲሁም የማህበሩ አመራሮች የተገኙ ሲሆን፤ የኤስ ኦኤስ (SOS) አልሙናይ youth Association የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም የከተማ አስተዳደሩ የወጣቶችና ስፖርት እና የሴቶችና ሕጻናት ቢሮ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተው የማበረታቻ መልዕክት ማስተላለፋቸው ይታወሳል።
በውድድሩም ላይ፦
◉ የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር (Addis Ababa Youth Association)
◉ ሰላም ፍሩት ማህበር ( selam Fruit association )
◉ National 4 care leavers association
◉ የኤስ ኦኤስ አልሙናይ youth Association ቡድኖች በከፍተኛ ስፖርታዊ ጨዋነት ተሳትፈዋል።
ወንዶች በእግር ኳስ እንዲሁም ሴቶች በእጅ ኳስ ተጋጥመዋል። ውድድሩ ከስፖርታዊ ፉክክርነቱ ባለፈ በወጣቶቹ መካከል ያለውን የእርስ በእርስ ግንኙነትና ትስስር ይበልጥ ለማጠናከር የተካሄደ በመሆኑ ዓላማውን ስኬታማ በሆነ መልኩ አሳክቷል።
የስፖርት ፌስቲቫሉን ይበልጥ ትርጉም ባለው መልኩ ለማጠቃለል፣ ችግኝ ተከላም የተካሄደ ሲሆን
በአጠቃላይ በስፖርት ፌስቲቫሉ ማጠቃለያ ላይ የተገኙት ወጣቶችና የማህበሩ አመራሮች በጋራ በመሆን የአካባቢ ጥበቃ መልዕክታቸውን በችግኝ ተከላ ያሰሙ ሲሆን፤ ወጣቱ በስፖርቱ መስክ ንቁ እንደሆነ ሁሉ ለሀገራዊው የአረንጓዴ ልማትም የበኩሉን አሻራ ማሳረፍ እንዳለበት በተግባር አሳይተዋል።