የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር / Addis Ababa Youth Association

የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር / Addis Ababa Youth Association Addis Abaab Youth Association is a non governmental organization. የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር በኢፌድሪ የበጎ አድራጎትና ማህበራት ኤጀንሲ የካቲት 22 ቀን 1990 ዓ.ም የተመሰረተ ተቀዳሚ ማህበር ነው።

17/08/2026

📌 የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር ከጀግናው መከላከያ ሰራዊት ጋር በጦር ሀይሎች ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል

የሰዎች ህገ-ወጥ ዝውውርን ለመከላከል የግንዛቤ ስልጠና ተሰጠየአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር ልደታ ቅርንጫፍ በሰዎች ህገ-ወጥ ዝውውርና በስደት ዙሪያ ለወጣቶች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ።በ...
15/08/2026

የሰዎች ህገ-ወጥ ዝውውርን ለመከላከል የግንዛቤ ስልጠና ተሰጠ

የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር ልደታ ቅርንጫፍ በሰዎች ህገ-ወጥ ዝውውርና በስደት ዙሪያ ለወጣቶች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ።

በመድረኩ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር ልደታ ቅርንጫፍ ም/ሰብሳቢ ወጣቶች ለስደትና ለሰዎች ህገ-ወጥ ዝውውር ተጋላጭ ከሚሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች መካከል ዋነኛዎቹ መሆናቸውን ጠቁመው፣ በክፍለ ከተማው በሚገኙ ሁሉም አካባቢዎች ለሚኖሩ ወጣቶች በጉዳዩ ዙሪያ ቀጣይነት ያለው ግንዛቤ ማስጨበጥ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

በተለይም ህገ-ወጥ ስደት ሊያስከትላቸው ስለሚችሉ አስከፊ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና የሰብዓዊ መብት ጉዳቶች ወጣቶችን ማስተማር እና ማሳወቅ ወሳኝ መሆኑን ገልጸው፣ በክፍለ ከተማው ህገ-ወጥ ስደትን ለመከላከል በትኩረት መስራት እንደሚገባ አመልክተዋል። አክለውም የማህበሩ የወረዳ አመራሮች ጉዳዩን በተለየ ትኩረት በመያዝ ተግባራዊ ስራዎችን እንዲያጠናክሩ ጥሪ አቅርበዋል።

ስልጠናውን የሰጡት አቃቤ ህግ ዮናታን በበኩላቸው፣ የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር ከጽ/ቤታቸው ጋር በቅርበት በመስራት መሰል ተግባራትን ሲያከናውን መቆየቱን ገልጸዋል። በያዝነው የበጀት ዓመትም ትብብሩን በማጠናከር ወጣቶችን ከህገ-ወጥ ስደትና ከተያያዙ ጉዳቶች ለመታደግ የጋራ ስራዎችን ማከናወን እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

በስልጠናው የሰዎች ህገ-ወጥ ዝውውር መንስኤዎች፣ የሚያስከትላቸው ጉዳቶች፣ ወጣቶች ሊወስዷቸው ስለሚገቡ የጥንቃቄ እርምጃዎችና ህጋዊ አማራጮች ላይ ሰፊ ማብራሪያ ተሰጥቷል።

ከስልጠናው ጋር በተያያዘ በተሳታፊዎች የተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶችም በስልጠና ሰጪው በቂ ማብራሪያ ተሰጥቶባቸው መድረኩ ተጠናቋል።

ማህበሩ በክረምት የትራፊክ በጎ ፈቃድ አገልግሎት የትራፊክ ፍሰትን በማሳለጥና አቅመ-ደካሞችን በማገዝ ረገድ አበረታች ስራዎችን እየሰራ መሆኑ ተገለፀ።ነሀሴ09/2018ዓ.ምአዲስ አበባ ወጣቶች ...
15/08/2026

ማህበሩ በክረምት የትራፊክ በጎ ፈቃድ አገልግሎት የትራፊክ ፍሰትን በማሳለጥና አቅመ-ደካሞችን በማገዝ ረገድ አበረታች ስራዎችን እየሰራ መሆኑ ተገለፀ።

ነሀሴ09/2018ዓ.ም

አዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት በክረምት የትራፊክ በጎ ፈቃድ አገልግሎት የትራፊክ ፍሰትን በማሳለጥና አቅመ-ደካሞችን በማገዝ ረገድ አበረታች ስራዎችን እየሰራ መሆኑንገልጿል።

በክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ከሚከናወንባቸው ዘርፎች መካከል አንዱ የትራፊክ አገልግሎት ሲሆን በዚህም በርካታ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች አላማውን ደግፈው ማህበረሰቡንና መንግስትን በማገልገል ላይ ይገኛል።

ማህበሩ ያሰማራቸው በጎ ፍቃደኞች ከትራፊክ አገልግሎት በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች ጋር ቆይታ ያደረገ ሲሆን በክረምት ወቅት የሚከሰተውን የትራፊክ ፈሰት በማሳለጥና አቅመ-ደካሞችንና አካል ጉዳተኞችን መንገድ በመምራት ረገድ በራስ ተነሳሽነት በማገልገላቸው መደሰታቸውን ገልፀዋል።

በጎ ፈቃድ አገልግሎት ጥቅም ሳይፈልጉ በራስ ተነሳችነት ለበጎ አላማ የምንሰለፍበትና የህሊና እርካታን የምናገኝበት መልካም ተግባር ነው ያሉ በጎ ፈቃደኞች በተመደቡበት ቦታ ለማህበረሰቡ ግንዛቤ በመስጠትና ለትራፊክ አደጋ እንዳይጋለጡ በማድረግ ረገድ አበረታች ስራዎችን እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።

የአዲስ አበባ ወጣት ማህበር የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ዋና ፀሀፊ የሆኑት ወጣት ተስፋዬ ፀጋዬ በበኩላቸው በትራፊክ በጎ ፈቃድ አገልግሎት በጎ ፈቃደኛ ወጣቶችን በማሳተፍና በቂ ግንዛቤ በማስጨበጥ ወደስራ እንዲገቡ ተደርጓል ብለዋል።

የትራፊክ ፍሰት በሚበዛባቸው መንገዶች ላይ በሁለት ፈረቃ ጠዋትና ማታ በጎ ፈቃደኞችን በመመደብ አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን የገለፁት ወጣት ተስፋዬ የትራፊክ አደጋን በመከላከልና የመኪና ፍሰቱን በማሳለጥ ረገድ ተጨባጭ ውጤት ማምጣት መቻሉን ተናግረዋል።

"እኛ ወጣቶች ለመከላከያ ሰራዊታችን ደጀን ነን" የአራዳ ክፍለከተማ ወጣቶችነሐሴ 8/2018 ዓ/ም (አ.አ.ወ.ማ.ኮሚሽን ጽ/ቤት)የአዲስ አበባ ከተማ ወጣቶች ማህበር አራዳ ክፍለ ከተማ ቅርንጫ...
14/08/2026

"እኛ ወጣቶች ለመከላከያ ሰራዊታችን ደጀን ነን" የአራዳ ክፍለከተማ ወጣቶች

ነሐሴ 8/2018 ዓ/ም (አ.አ.ወ.ማ.ኮሚሽን ጽ/ቤት)

የአዲስ አበባ ከተማ ወጣቶች ማህበር አራዳ ክፍለ ከተማ ቅርንጫፍ “እኛ ወጣቶች ለመከላከያ ሰራዊታችን ደጀን ነን" በሚል መሪ ቃል ለመከላከያ ሰራዊታችን ያለውን አጋርነትና ድጋፍ አሳይቷል።

የክረምት የወጣቶች በጎ ፈቃድ መርሃ ግብር አካል የሆነው “በጎነት በሆስፒታል” መርሃ ግብር በጦር ኃይሎች ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ተካሂዷል።

በመርሃ ግብሩ የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር ፕሬዝዳንት ወጣት በረከት ቢርቢርሳ፣ የአራዳ ክፍለ ከተማ ቅርንጫፍ ሰብሳቢ ወጣት ማቲዮስ ብርሃኑ፣ የጦር ኃይሎች ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ብርጋዴር ጀነራል ገነት ይማም፣ የአራዳ ክፍለ ከተማ መሬት ማኔጅመንት ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አላፊ አቶ መልካሙ ተገኝ፣ የአራዳ ክፍለ ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት አላፊ አቶ ተሰራ ማማዬ፣ እንዲሁም የማህበሩ በየደረጃው ያሉ አመራሮችና በጎ ፍቃደኞች ተሳትፈዋል።

የማህበሩ ፕሬዝዳንት ወጣት በረከት ብርቢርሳ ባደረጉት ንግግር፣ የወጣቶች በጎ ፈቃደኝነት ለማህበረሰቡ የሚያበረክተውን ድርሻ አጉልተው በመግለፅ የዛሬውን የበጎ ፍቃድ ተግባር ልዩ የሚያደረገው ደግሞ ለሀገራቸው ውድ ሕይወታቸውን በመስጠት ከተዋደቁ ጀግኖች ቤት መገኘታችን ነው ሲሉ ገልፀዋል።

ፕሬዝዳንቱ አክለውም ወጣቶች የበጎ ፍቃድ ተግባር በሁሉም ህብረተሰብ ክፍል ባህል እንዲሆን እየሰሩት ያሉትን ተግባር እንዳለ ሆነው በሀገረመንግስት ግንባታ፣ በልማት፣ እንዲሁም ለሀገራቸው ውድ ህይወታቸውን ሁሉ ሳይሳስቱ ሀገራችን ታፍራና ተከብራ ለቀጣይ ትውልድ እንድትተላለፍ ላደረጉ ጀግኖች ክብርና እውቅና በመስጠት እኛም ከጎናቸው መሆናችንን እንገልፃለን ስሉ በአፅኖት ተነግሯል።

የሆስፒታሉ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ብርጋዴር ጀነራል ገነት ይማም የወጣቶችን በጎ ፈቃደኝነትና ያላቸውን አጋርነት አድንቀው፣ የማህበረሰብ ተሳትፎና መረዳዳት በተለይም በሆስፒታል ውስጥ ለሚገኙ ወገኖች የሚኖረውን ሞራላዊና ማህበራዊ ጠቀሜታ አጉልተው ገልጸዋል።

“ለሀገር የሚተጋ ሰራዊት ከጎኑ የሚቆም ህዝብና ወጣት አለው። ዛሬ የምናደርገው ድጋፍ በጎ ፈቃድ ብቻ ሳይሆን የአንድነታችን፣ የአጋርነታችንና የሀገራዊ ኃላፊነታችን መገለጫ ነው” ሲሉም የአረዳ ክፍለከተማ መሬት መነጅመንት ቅ/ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ መልካሙ ተገኝ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ወጣቶች ከሀገራቸውን ባለውለታ ጎን በመሆን ያላቸውን አለኝታ ማሳያታቸውን በማድናቅ በቀጣይም ወጣቱ የራሱን ታሪክ መስራቱን አጠናክሮ መቀጠል እንዳለባቸው የአረዳ ክፍለከተማ ወጣቶችና ስፖርት ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ተሰራ ማማዬ ገልጿል።

መርሃ ግብሩ የወጣቶችን የበጎነት፣ የመረዳዳትና የሀገራዊ አጋርነት እሴት የሚያጠናክር ሲሆን፣ የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበርም በቀጣይ ወጣቶችን በማሳተፍ በጎ ፈቃደኝነትንና የመረዳዳት ባህልን የማጠናከር ተግባሩን እንደሚቀጥል ተገልጿል።

የአዲስ አበባ  ወጣቶች ማህበር በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት  የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ይገኛልየአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቅርንጫ...
14/08/2026

የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት እየተሰጠ ይገኛል

የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በ2018 ዓ.ም. የክረምት በጎ ፈቃደኝነት ማጠናከሪያ ትምህርትን በክፍለ ከተማው በሚገኙ የተለያዩ ትምህርት ቤቶች እያስተባበረ ይገኛል።

የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርቱ ተማሪዎች በትምህርት ያገኙትን እውቀት እንዲያጠናክሩ፣ የጥናትና የንባብ ልምዳቸውን እንዲያሳድጉ እንዲሁም ለቀጣዩ የትምህርት ዘመን የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ የሚያስችላቸውን ዝግጅት እንዲያደርጉ የሚያግዝ ነው።

በተጨማሪም ተማሪዎች ከትምህርት ሳይርቁ በክረምት ወቅት ቀጣይነት ያለው የመማር ሂደት እንዲኖራቸው በማድረግ የትምህርት ጥራትንና የተማሪዎችን የትምህርት ውጤት ለማሻሻል አዎንታዊ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።

ይህም በትምህርት ዘርፉ የሚሳተፉ ባለድርሻ አካላትን፣ ወጣቶችንና ሌሎች አካላትን በማስተባበርና በትብብር በመስራት ለተማሪዎች የተሻለ የመማሪያ ሁኔታ ለመፍጠር የሚደረግ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ነው።

የምክክር ጉባኤው የተለያዩ ሀሳቦች በነፃነት እንዲንሸራሸሩ በማስቻል ችግሮችን በምክክር ለመፍታት ሰፊ ዕድል ፈጥሯል-ተመካካሪዎችአዲስ አበባ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክ...
13/08/2026

የምክክር ጉባኤው የተለያዩ ሀሳቦች በነፃነት እንዲንሸራሸሩ በማስቻል ችግሮችን በምክክር ለመፍታት ሰፊ ዕድል ፈጥሯል-ተመካካሪዎች

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የተለያዩ ሐሳቦች በነፃነት እንዲንሸራሸሩ በማስቻል፣ ነባር ችግሮችን በምክክር ለመፍታት ሰፊ ዕድል መፍጠሩን ተመካካሪዎች ገለጹ።

የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል እየተካሄደ ይገኛል።

በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን የሚወክሉ አራት ሺህ ተመካካሪዎች በስምንት ዐበይት አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ጥልቅና አሳታፊ ምክክር እያካሄዱ ናቸው።

አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ተመካካሪዎች፤ በምክክሩ እየተነሱ የሚገኙት ሀሳቦች ለዘላቂ የሀገር ግንባታ አስተዋጽኦ የሚያበረክቱ ናቸው ብለዋል።

ከተመካካሪዎቹ መካከል የሲቪክ ማህበረሰብ ተቋምን በመወከል እየተመካከሩ የሚገኙት ተመካካሪ አብዲሳ አበበ(ዶ/ር) እንደገለጹት፤ ምክክሩ ከመላው ኢትዮጵያ የተውጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎች እየተሳተፉበትና ሁሉም ሰው ሀሳቡን በነፃነት እያቀረበበት ይገኛል።

ምክክሩ የተለያዩ ሀሳቦች ያለ ገደብ እንዲነሱ ዕድል መፍጠሩን ጠቁመው፤ ይህም ችግሮችን አሳታፊ በሆነ መንገድ በመመካከር ለዛሬ ብቻ ሳይሆን ለነገ የሚበጁ መፍትሄዎችን ማምጣት እንደሚያስችል ተናግረዋል።

በተመካካሪዎች እየተነሱ ያሉት ሀሳቦች ኢትዮጵያን ወደ ዘላቂ ሰላም፣ ከፍታና እድገት ለማሻገር እንደሚያግዝ ገልፀው፤ ሂደቱ ለሀገሪቱ የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታም ከፍተኛ አስተዋጽኦ አለው ብለዋል።

የሲዳማ አርነት ንቅናቄ ፓርቲ ተወካይ ስማቸው እንግሶ በበኩላቸው፤በኢትዮጵያ ታሪክ በርካታ ሕዝብ በአንድ ላይ ሲመካከር የመጀመሪያው መሆኑን ገልጸው፤ በምክክሩ እየተነሱ ባሉ ሐሳቦች ላይ በመምከር ወደ አንድ የጋራ መግባቢያ እየተመጣ መሆኑን ጠቁመዋል።

ምክክሩ ለችግሮች ዘላቂ መፍትሄ ለማበጀት ትልቅ ዕድል መፍጠሩን ጠቁመው፤ ይህም የተሻለች ሀገርን ለመጪው ትውልድ ለማስረከብ እንደሚያግዝ ተናግረዋል።

ሀገራዊ ምክክሩ ኢትዮጵያ ሕብረ ብሔራዊነቷን በማጠናከር ከአፍሪካ አልፋ በዓለም አቀፍ ደረጃ አዎንታዊ ሚና እንድትጫወት የሚያስችል አስተዋጽኦ እንዳለው ገልጸዋል።

የምክክር ጉባኤው የወጣቶችን ተስፋ የሚያለመልም የመግባባት ምክረ ሀሳብ የሚፈልቅበት የጋራ መድረክ እንደሚሆን እንጠብቃለን - የአዲስ አበባ ወጣቶችአዲስ አበባ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የ...
12/08/2026

የምክክር ጉባኤው የወጣቶችን ተስፋ የሚያለመልም የመግባባት ምክረ ሀሳብ የሚፈልቅበት የጋራ መድረክ እንደሚሆን እንጠብቃለን - የአዲስ አበባ ወጣቶች

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የወጣቶችን ተስፋ የሚያለመልም ሀገራዊ የመግባባት ምክረ ሀሳብ የሚፈልቅበት የጋራ መድረክ እንደሚሆን እንጠብቃለን ሲሉ የአዲስ አበባ ወጣቶች ገለጹ።

የኢትዮጵያ ዋናው ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ በሚገኘው አዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል በሰፊ ተሳትፎና በጥልቅ ምክክር መካሄዱን ቀጥሏል።

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽንም በመንግሥት አደረጃጀትና ቅርጽ፣ በፖለቲካ ሥርዓት፣ በፖለቲካ ውክልናና በምርጫ ሥርዓት፣ በሙስናና በመልካም አስተዳደር፣ በሃይማኖት ጉዳዮችና በሰላም ግንባታ ዙሪያ በተካሄዱ ምክክሮች ተመካካሪዎች ባቀረቧቸው ምክረ ሀሳቦች ላይ መግባባት መደረሱን ይፋ አድርጓል።

ይህ ሂደት በተለይ ለቀጣዩ ትውልድ ትልቅ ተስፋን የሚያለመልም መሆኑን በአዲስ አበባ ኢዜአ ያነጋገርናቸው ወጣቶች ገልጸዋል።

እንደ ወጣቶቹ አስተያየት ምክክርና መደማመጥን የሚያስቀድሙ ሀገራዊ መድረክ ዘላቂ ሰላምን፣ ሀገራዊ መግባባትንና የጋራ የልማት ርዕይን ለመገንባት ጠንካራ መሠረት ይጥላል።

የአዲስ አበባ ነዋሪዋ ወጣት ልዩወርቅ ሙሉጌታ እንደገለጸችው፤ ምክክርን በማስቀደም ሀገራዊ መግባባትን ለመፍጠር የሚደረጉ ማንኛውም ዓይነት ጥረቶች የወጣቱን ተስፋ የሚያለመልሙ ናቸው።

ሀገር ስትመክር የተሻለች ኢትዮጵያን እንድናይ ያስችለናል ያለችው ወጣቷ፤ በምክክር የምትገነባ ሀገርም የዜጎቿን ዕድገትና ብልፅግና ለማሳለጥ ጠንካራ መደላድል መፍጠር እንደምትችል ገልጻለች።

የምክክር ጉባኤው የወጣቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት፣ በሰላም ግንባታና በልማት ሂደት ያላቸውን ተሳትፎ በማጠናከር ለቀጣዩ ትውልድ ተስፋ የሚሰጥ የጋራ መድረክ መሆኑንም ተናግራለች።

ከጉባኤው የሚፈልቁ የጋራ መግባባት ምክረ ሀሳቦችም ሰላምና አንድነቷን ጠብቃ ወደ ዘላቂ ዕድገትና ብልፅግና የምትራመድ ኢትዮጵያን ለመገንባት አጋዥ ሚና እንደሚኖራቸው ሀሳቧን አንስታለች።

ሌላው የመዲናዋ ወጣት ንጉሥ አይጋበዝ በበኩሉ፤ የምክክር ጉባኤው ቀጣዩ ትውልድ መደማመጥንና ምክክርን የአስተሳሰብና የኑሮ ባህል እንዲያደርግ ትልቅ መሠረት የሚጥል መሆኑን ተናግሯል።

በሕዝብ ወኪል ተመካካሪዎች መካከል የሚፈጠረው መግባባትና የሚቀርቡት ምክረ ሀሳቦችም በመሠረታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ የጋራ አቋም በመገንባት ሰላምን፣ አንድነትንና የጋራ ሀገራዊ ጥቅምን ለማስከበር ወሳኝ አበርክቶ እንደሚኖራቸው ገልጿል።

ሀገራዊ መግባባትን በመገንባት የወጣቶችን በሀሳብ የበላይነት፣ በሰላም የተመሠረተና የብልፅግና ርዕይ ያለው ሀገር መሻት ምላሽ ለመስጠት ጉባኤው ጠቃሚ መሆኑን ደግሞ ነብያት ስብሀቱ ተናግራለች።

ኢትዮጵያ እየመከረች ነው ያለችው ወጣቷ፤ የጉባኤውን ሂደትም በሚገባ በመከታተል የጋራ መግባባት ውጤቶችን በጉጉት እየተጠባበቀች መሆኑን ገልጻለች።

ሌላኛው የአዲስ አበባ ወጣት አብነት ንጉሴ በበኩሉ፤ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤው የትውልድን የመመካከርና የመደማመጥ የአስተሳሰብ ባህል የሚያጎለብት የጋራ መድረክ ነው ብሏል።

በመደማመጥና በመመካከር ለዘመናት የቆዩ አለመግባባቶችንና ቁርሾዎችን በሰለጠነና ሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ጉባኤው የሚያበረክተው ሚና ከፍተኛ መሆኑንም ገልጿል።

ወጣቶች የዛሬ ተስፋ፣ የነገ መሪዎችየአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር የወጣቶች ቀንን ስናከብር፣ ወጣቶች የሀገራችን የለውጥ ኃይል፣ የፈጠራ ምንጭ እና የተሻለች ኢትዮጵያ ግንባታ ቀዳሚ ተዋናዮች መ...
12/08/2026

ወጣቶች የዛሬ ተስፋ፣ የነገ መሪዎች

የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር የወጣቶች ቀንን ስናከብር፣ ወጣቶች የሀገራችን የለውጥ ኃይል፣ የፈጠራ ምንጭ እና የተሻለች ኢትዮጵያ ግንባታ ቀዳሚ ተዋናዮች መሆናቸውን በድጋሚ እናረጋግጣለን።

ወጣቶች ያላቸውን እውቀት፣ ክህሎት፣ ፈጠራ እና ጉልበት ለሀገርና ለህብረተሰብ በሚጠቅም መልኩ ማዋል ሲችሉ፣ የለውጥ ተሳታፊ ብቻ ሳይሆኑ የለውጡ መሪዎች ይሆናሉ። ስለሆነም ወጣቶችን ማብቃት፣ እድል መፍጠር እና ድምፃቸውን ማዳመጥ የጋራ ኃላፊነታችን ነው።

በዚህ ልዩ ቀን ለአዲስ አበባና ለመላው ኢትዮጵያ ወጣቶች ያለንን አክብሮት እየገለጽን፣ በአንድነት፣ በትጋት፣ በፈጠራ እና በኃላፊነት በመስራት የምንመኛትን ብሩህ ሃገር እንድንገነባ ጥሪዬን አቀርባለሁ።

መልካም የወጣቶች ቀን!
ወጣቶች ለሀገር እድገትና ለሰላም የሚጫወቱት ሚና ይጠናከር!

ወጣት በረከት ቢርቢርሳ
የአዲስ አበባ ከተማ ወጣቶች ማህበር ፕሬዝዳንት

መልካም የወጣቶች ቀን🇪🇹​ዛሬ የወጣትነታችንን ጉልበት፣ ፈጠራና የማይበገረውን መንፈስ የምናከብርበት ልዩ ቀን ነው:: ወጣቶቻችን የሀገር ለውጥ ሞተሮች፣ የነገው ተስፋ ተሸካሚዎች እና የብሩህ ...
12/08/2026

መልካም የወጣቶች ቀን🇪🇹

​ዛሬ የወጣትነታችንን ጉልበት፣ ፈጠራና የማይበገረውን መንፈስ የምናከብርበት ልዩ ቀን ነው:: ወጣቶቻችን የሀገር ለውጥ ሞተሮች፣ የነገው ተስፋ ተሸካሚዎች እና የብሩህ የወደፊት መሀንዲሶች ናቸው። በእውቀት የታጠቀ፣ በሥራ የሚያምን እና በአንድነት የቆመ ወጣት የሀገርን ታሪክ የመለወጥ አቅም አለው::

​ፈተናዎች ቢኖሩም፣ ወጣቶች መጪው ትውልድ ትልቅ ተስፋ እንዲኖረው ዛሬውኑ አቅማቸውን እንዲጠቀሙ ጥሪ እናቀርባለን። እንማር፣ እንሥራ፣ አዳዲስ ነገሮችን እንፍጠር፣ በሀገር ግንባታ እንሳተፍ!

​መልካም የወጣቶች ቀን ለሁሉም ወጣቶች

የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር ኮሚኒኬሽን ጽ/ቤት

የደግነትና የመረዳዳት እሴቶችን እናጎልብት ነሐሴ 5/2018 ዓ/ም (አ.አ.ወ.ማ.ኮሚኒኬሽን ጽ/ቤት)የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር  የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት እና በቂርቆስ ክፍለ...
11/08/2026

የደግነትና የመረዳዳት እሴቶችን እናጎልብት

ነሐሴ 5/2018 ዓ/ም (አ.አ.ወ.ማ.ኮሚኒኬሽን ጽ/ቤት)

የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት እና በቂርቆስ ክፍለ ከተማ አሽከርካሪ ተሽከርካሪ ጽ/ ቤት በጋራ አስተባባሪነት የክረምት በጎ ፍቃድ የማዕድ ማጋራት ፕሮግራም ተካሂዷል።

​በመርሃ-ግብሩ ወቅት ለተመረጡ አረጋውያን እናቶች የማዕድ ማጋራት እና የተለያዩ ድጋፎች የተደረጉ ሲሆን፣ ለአረጋውያኑ አስፈላጊውን እንክብካቤ የማድረግ ሥራዎች ተከናውነዋል።

​በስነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት የቂርቆስ ክፍለ ከተማ አሽከርካሪ ተሽከርካሪ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ደረጄ እንደገለፁት፣ አቅመ-ደካሞችን እና አረጋውያንን መደገፍ የሁሉም ተቋማትና ዜጎች ማህበራዊ ኃላፊነት ነው። አክለውም ጽሕፈት ቤታቸው ከመደበኛ አገልግሎቱ ጎን ለጎን ማህበረሰብ አቀፍ የበጎ አድራጎት ሥራዎችን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።

​በተመሳሳይ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወጣቶች ማህበር ምክትል ሰብሳቢ ወጣት የቻለ ጋቴ በበኩላቸው፣ ወጣቱ ባለው ጉልበት እና ቀና አስተሳሰብ አረጋውያን እናቶችንና አቅመ-ደካሞችን መደገፍ እንዳለበት ገልፀው፤ ይህ የማዕድ ማጋራት መርሃ-ግብር አረጋውያንን በማስደሰትና አክብሮትን በማሳየት ረገድ ትልቅ የህሊና እርካታ የሚሰጥ የበጎነት ተግባር መሆኑን ገልፀዋል።

​በዕለቱ የማዕድ ማጋራት ድጋፍ የተደረገላቸው አረጋውያን እናቶች በበኩላቸው በተደረገላቸው ድጋፍ የተሰማቸውን ከፍተኛ ደስታ ገልፀው፣ ለአዘጋጆቹ እና አመራሮችና አባላት ምርቃትና ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

Address

Addis Ababa

Telephone

+251111232399

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር / Addis Ababa Youth Association posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር / Addis Ababa Youth Association:

Shortcuts

Share