Ethiopian National Assocation of the Deaf የኢትዮጵያ መስማት የተሳናቸው ብሔራዊ ማኅበር

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Ababa
  • Ethiopian National Assocation of the Deaf የኢትዮጵያ መስማት የተሳናቸው ብሔራዊ ማኅበር

Ethiopian National Assocation of the Deaf  የኢትዮጵያ መስማት የተሳናቸው ብሔራዊ ማኅበር ENAD is a non profit, non-governmental Association established by the Deaf with the assistance of some of their hearing friends in 1970.

01/06/2026
29/05/2026

1.......29

የኢትዮጵያ መስማት የተሳናቸው ብሔራዊ ማህበር ወልቂጤ ቅርንጫፍ የብሔራዊ ማህብሩ 29 ቅርንጫፍ በመሆን ህጋዊ እውቅና በመስጠት መቋቋሙን ስናበስር በደስታ ነው።

ብሔራዊ ማህበራችን አድማሱን እያሰፋ ይቀጥላል!!

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታይ በሙሉ፣ እንኳን ለኢድ አል አደሃ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ኢድ ሙባረክ!
27/05/2026

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታይ በሙሉ፣

እንኳን ለኢድ አል አደሃ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

ኢድ ሙባረክ!

ጊዜያቸውን እና ጉልበታቸውን ለመስማት ለተሳናቸው ማህበረሰብ ለሚሰጡ ለሁሉም የምልክት ቋንቋ አስተርጓሚዎች በሙሉ መልካም የምልክት ቋንቋ አሰተርጓሚዎች ቀን።Happy Sign Language In...
07/05/2026

ጊዜያቸውን እና ጉልበታቸውን ለመስማት ለተሳናቸው ማህበረሰብ ለሚሰጡ ለሁሉም የምልክት ቋንቋ አስተርጓሚዎች በሙሉ መልካም የምልክት ቋንቋ አሰተርጓሚዎች ቀን።

Happy Sign Language Interpreters Appreciation Day to all the dedicated interpreters who devote their time and energy to the Deaf community.

በሳፋሪኮም ኢትዮጵያ እና ቮዳኮም ግሩፕ አዘጋጅነት የ “Accessibility & Disability Inclusion Conference” ሚያዚያ 16 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ጀም...
25/04/2026

በሳፋሪኮም ኢትዮጵያ እና ቮዳኮም ግሩፕ አዘጋጅነት የ “Accessibility & Disability Inclusion Conference” ሚያዚያ 16 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ጀምሮ ለመጀመሪያ ጊዜ በአዲስ አበባ አካሂዷል።

በዚህ ኮንፈረንስ ከ28 አመታት በላይ በአካል ጉዳተኞች አካታችነት ላይ የዳበረ ልምድ ያላቸው የቮዳኮም ግሩፕ የአክሰሰቢሊቲ ኃላፊ እና የአፍሪካ አክሰሰቢሊቲ ፎረም ሰብሳቢ፣ ከፍተኛ የመንግስት ኃላፊዎች እና የሲቪክ ማህበራት በተገኙበት ተካሂዷል።

በዚህ መድረክ የተሳተፈው ብሄራዊ ማህበሩም
በደቡብ አፍሪካ እና ኬኒያ በመተግበር ላይ የሚገኙ ቴክኖሎጂዎች ወደ ሀገራችን በማምጣት እንዲተገበሩ፣
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ እውቅና እንዲያገኘ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በተቋሙ ውስጥ አካትች እንዲያደርግ፣
አካታችነትን በማራመድ የተግባቦት ችግሮችን መቅረፍ፣
የተቀናጀ ምርምር በኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ እና በዴፍ ባህል ዙሪያ የተቀናጀ ምርምር እንዲደረግ እና ውጤቶች ተገምግመው እንዲተገበሩ ምክረ ሃሳብ አቅርቧል።

የኢመየብማ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ እና ቮዳኮም ግሩፕ በአካል ጉዳተኞች ትኩረት በመስጠት እያደረገ ላለው ተጨባጭ ለውጥ ልባዊ ምስጋናውን ያቀርባል።

የኢመየብማ

የኢትዮጵያ መሰማት የተሳናቸው ብሄራዊ ማህበር ከፊንላንድ ኤምባሲ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የሁለት ቀናት ስልጠና  በዛሬው እለት በስኬት ተጠናቋል። ስልጠናው በስኬት እንዲጠናቀቅ ላደረጋችሁት ...
17/04/2026

የኢትዮጵያ መሰማት የተሳናቸው ብሄራዊ ማህበር ከፊንላንድ ኤምባሲ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የሁለት ቀናት ስልጠና በዛሬው እለት በስኬት ተጠናቋል። ስልጠናው በስኬት እንዲጠናቀቅ ላደረጋችሁት አፅተዋፅኦ ምስጋናችን የላቀ ነው።

የኢትዮጵያ መሰማት የተሳናቸው ብሄራዊ ማህበር ከፊንላንድ ኤምባሲ ጋር በመተባበር በተመረጡ ቅርንጫፎቹ በሚተገበረው "የመስማት የተሳናቸው ሴቶች በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተካታችንትና በአኗኗር ዘ...
16/04/2026

የኢትዮጵያ መሰማት የተሳናቸው ብሄራዊ ማህበር ከፊንላንድ ኤምባሲ ጋር በመተባበር በተመረጡ ቅርንጫፎቹ በሚተገበረው "የመስማት የተሳናቸው ሴቶች በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተካታችንትና በአኗኗር ዘይቤ ማብቃት" ፕሮጀክት የመክፈቻ ፕሮግራሙን በዛሬው እለት ጥሪ በተደረገላቸው ተቋማትና የማህብሩ ቅርንጫፍ ተወካዮች በተገኙበት አስጀምሯል።

ለሁለት ቀናት በሚቆየው የመክፈቻና የግንዛቤ ማስጨበጫ ፕሮግራም በቀጣይ በሊተገበሩ ተግባራቶች የመስማት የተሳናቸው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተካታችነት ላይ ተጨባጭና ትርጉም ያለውጥ ለማምጣት ያለመ ነው።

የኢመየብማ

እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳዔ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! በዓሉ የሰላም፣ የጤና እና የመተሳሰብ እንዲሆንላችሁ እመኛለን!የኢመየብማ
11/04/2026

እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳዔ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! በዓሉ የሰላም፣ የጤና እና የመተሳሰብ እንዲሆንላችሁ እመኛለን!

የኢመየብማ

10/04/2026

በመስማት የተሳናት ወጣት መኪያ ላይ ፆታዊ ጥቃት ያደረሰው ተጠርጣሪ ግለሰብ በአዳማ ከተማ ፖሊስ በቁጥጥር ስር ውሏል።
በኢትዮጵያ መስማት የተሳናቸው ብሄራዊ ማህበር የአዳም መስማት የተሳናቸው ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ጉዳዩ በቅርበት በመሆን ክትትል አያደረገ መሆኑን እናሳውቃለን።

መስማት የተሳናት መኪያ አካል ጉዳተኝነቶን ሽፋን በማድረግ በደረሰባት ጾታዊ ጥቃት ማዘናችንን እየገለጽን ብሄራዊ ማህበራችን ከአዳማ ቅ/ጽ/ቤት እና በማህባችን የህግ አማካሪና ጠበቃ ጋር በመሆ...
09/04/2026

መስማት የተሳናት መኪያ አካል ጉዳተኝነቶን ሽፋን በማድረግ በደረሰባት ጾታዊ ጥቃት ማዘናችንን እየገለጽን ብሄራዊ ማህበራችን ከአዳማ ቅ/ጽ/ቤት እና በማህባችን የህግ አማካሪና ጠበቃ ጋር በመሆን ጉዳዩ ቤተሰቧን በቀጥታ በማነጋገር የተቻለ ሲሆን ተጠርጣሪው በፖሊስ ቁጥጥር ስር ለማድረግ ክትትል ላይ ይገኛል። ብሄራዊ ማህበራችን ተገቢውን የህግ ድጋፍ በማድረግ ክትትል ማድረጉን ይቀጥላል።

የኢመየብማ

Address

Https://goo. Gl/maps/6Vfhgq62uAe96T4c 7
Addis Ababa

Opening Hours

Monday 09:00 - 17:30
Tuesday 09:00 - 17:30
Wednesday 09:00 - 17:30
Thursday 09:00 - 17:30
Friday 09:00 - 17:30

Telephone

+251111222517

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian National Assocation of the Deaf የኢትዮጵያ መስማት የተሳናቸው ብሔራዊ ማኅበር posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Ethiopian National Assocation of the Deaf የኢትዮጵያ መስማት የተሳናቸው ብሔራዊ ማኅበር:

Share