Buzuayehu Tadele Family Foundation

Buzuayehu Tadele Family Foundation Buzuayehu Tadele Family Foundation is a non-governmental organization (NGO) Buzuayehu Tadele and His Family Foundation (BTFF).

is a non-governmental organization established in 2019, registered with the FDRE Charities and Societies Agency (License No. 4381) as an Ethiopian Residents Charity. The Foundation represents East African Holding's philanthropic effort, intended to fulfill the company's corporate social commitments. BTFF is driven by a mission to assist the underprivileged, In line with its corporate social respon

sibilities, BTFF has adopted a guiding principle of actively involving with and benefiting the local community through diverse initiatives. Essentially, the Foundation aims to carry out community-based services and environmentally friendly projects, mobilize the local community on a large scale as well as support the society to create strength and sense of ownership for the company's socially benefiting businesses.

መልካም ገና ! ብዙአየሁ ታደለና ቤተሰቡ ፋውንዴሽን በዓሉ የደስታና የፍሰሃ እንዲሆንላችሁ ይመኛል!!
06/01/2026

መልካም ገና !

ብዙአየሁ ታደለና ቤተሰቡ ፋውንዴሽን በዓሉ የደስታና የፍሰሃ እንዲሆንላችሁ ይመኛል!!

የጌታችን የመድሃኒታችን የእየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓል ገናን ምክንያት በማድረግ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጋር በመተባበር ማዕድ አጋርተናል።በተጨማሪም በቪላ አፍሪካ የምገባ መርሃ ግብራ...
05/01/2026

የጌታችን የመድሃኒታችን የእየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓል ገናን ምክንያት በማድረግ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጋር በመተባበር ማዕድ አጋርተናል።

በተጨማሪም በቪላ አፍሪካ የምገባ መርሃ ግብራችን የዕለት ጉርስ ለምናቀብላቸው ወገኖችም እንደዚሁ ማዕድ አጋርተናል።

ፋውንዴሽናችን በዘድሮው የገና በአል በድምሩ ለ1200 ዜጎች ማዕድ አጋርቷል።

ባለፉት ተከታታይ 4 አመታት በበአላት ወቅት ለወገኖቻችን ማዕድ በማጋራት እና ሌሎች ማህበራዊ ድጋፎች በማድረግ ፋውንዴሽናችን አጋርነቱን ሲያሳይ ቆይቷል ።

ኢኮኖማያዊ አቅማቸው ዝቅተኛ ለሆኑ ወኖች ድጋፍ ማድረጋችንን በማጠናከር ማህበራዊ ሃላፊነታንን እንወጣለን።

12/12/2025
ብዙአየሁ ታደለና ቤተሰቡ ፋውንዴሽን በልደታ ክፍለ ከተማ ላበረከታቸው  የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች  እውቅና ተሰጠው ።ክ/ከተማው ለፋውንዴሽናችን እውቅና የሰጠው የ2017 ዓ.ም የክረምት የበጎ ...
05/12/2025

ብዙአየሁ ታደለና ቤተሰቡ ፋውንዴሽን በልደታ ክፍለ ከተማ ላበረከታቸው የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶች እውቅና ተሰጠው ።

ክ/ከተማው ለፋውንዴሽናችን እውቅና የሰጠው የ2017 ዓ.ም የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን ለመዝጋትና የ2018 ዓ.ም የበጋ በጎ ፈቃድ አገልግሎት ለማስጀመር ባዘጋጀው መርሃ ግብር ላይ ነው ።

ብዙአየሁ ታደለና ቤተሰቡ ፋውንዴሽን በክፍለ ከተማው በአቅመ ደካሞች መኖሪያ ቤት እና የንግድ ሱቆች ገንብቶ ማስረከብ፤ በቪላ አፍሪካ ምገባ ፕሮግራም ላለፉት 2 አመታት የእለት ጉርስ የሌላቸውን አረጋውያን መመገብ፤ በአከባቢ ጥበቃና አረንጓዴ ልማት፤ የህፃናት ማቆያ ቁሳቁስ በማሟላቱ ፤ የበአላት ወቅት ማዕድ ማጋራት እና ሌሎች የአቅም ግንባታ ድጋፎችን ማድረጉ በክፍለ ከተማው እውቅናውን አሰጥቶታል።

ብዙአየሁ ታደለና ቤተሰቡ ፋውንዴሽን እና ለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ከእንሳሮ ወረዳ አስተዳደር እውቅና ተሰጣቸው፡፡ሁለቱም ተቋማት የኢስት አፍሪካ ሆልዲንግ እህት ድርጅቶች ሲሆኑ ፤ ፋውንዴሽኑ ለአቅ...
12/11/2025

ብዙአየሁ ታደለና ቤተሰቡ ፋውንዴሽን እና ለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ከእንሳሮ ወረዳ አስተዳደር እውቅና ተሰጣቸው፡፡

ሁለቱም ተቋማት የኢስት አፍሪካ ሆልዲንግ እህት ድርጅቶች ሲሆኑ ፤ ፋውንዴሽኑ ለአቅመ ደካማ ወገኖች ቤት በመጠገን፤ በሺዎች ለሚቆጠሩ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ በማቅረቡ እንደዚሁም በወረዳው ለሚሰራው የአቅም ግንባታ ስራዎች ነው እውቅናው የተሰጠው፡፡

ለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ደግሞ በሃገር አቀፍ ደረጃ የነበረውን የሲሚንቶ እጥረትና የዋጋ ንረት በማረጋጋቱ እንደዚሁም በወረዳው ላመጣው ኢኮኖሚያዊ መነቃቃና ለውጥ፤ በተጨማሪም ለአከባቢው ወጣቶች ለፈጣራቸው የስራ እድሎች ነው፡፡

04/11/2025

ብዙአየሁ ታደለና ቤተሰቡ ፋውንዴሽን (ማኅበራዊ አገልግሎታችንን የሚፈጽመው ምግባረ ሰናይ ተቋማችን) በተሰማራባቸው አካባቢዎች ሁሉ ማኅበራዊ ለውጥና እድገትን ለማምጣት በቁርጠኝነት ይሠራል። #ትብብር፣ እና ሰንቀን፣ ብሩኅ መጪ ጊዜን ለመገንባት እንተጋለን!

በበጎ ፈቃደኝነት አብራችሁን ለመሥራት ይህንን ሊንክ ይጫኑ፡ buzuayehufoundation.org/index.php/volunteer

_
At Buzuayehu Tadele Family Foundation (our wing), we are dedicated to creating lasting impact in everycommunity we serve. Through , and , we work to uplift lives and build a brighter future!

Join our efforts and be part of this meaningful journey by volunteering today: buzuayehufoundation.org/index.php/volunteer
_

ብዙአየሁ ታደለና ቤተሰቡ ፋውንዴሽን እና ኢስት አፍሪካ ሪልእስቴት ሃላፊነነቱ የተወሰነ የግል ማህበር በአዲስ አበባ ከተማ ላደረጉት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የብርና የወርቅ ደረጃ እውቅና ተሰጣ...
23/10/2025

ብዙአየሁ ታደለና ቤተሰቡ ፋውንዴሽን እና ኢስት አፍሪካ ሪልእስቴት ሃላፊነነቱ የተወሰነ የግል ማህበር በአዲስ አበባ ከተማ ላደረጉት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የብርና የወርቅ ደረጃ እውቅና ተሰጣቸው።

ኢስት አፍሪካ ሪልእስቴት በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ባለ 4 ወለል ህንጻ ለአቅመ ደካሞች ገንብቶ በማስረከቡ ፤ፋውንዴሽኑ ደግሞ ፤ "ለነገዋ "የሴቶች ታሃድሶ እና ክህሎት ማበልፀግያ ማዕከል ድጋፍ በማድረጉ በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ለህጻናት ማቆያ ማዕከል ቁሳቁስ በማሟላቱ ፣ በ20ኛው ተስፋ ብርሃን የምገባ ማዕከል ለ500 አረጋውያን በየእለቱ በመመገብ እንደዚሁም በቪላ አፍሪካ ከ50 በላይ ለሆኑ አረጋውያን ለሚያደርገው ምገባ ነው እውቅና የተሰጠው።

ሁለቱም ተቋማት በኢስት አፍሪካ ሆልዲንግ ስር የሚገኙ ሲሆኑ ብዙአየሁ ታደለና ቤተሰቡ ፋውንዴሽን ትቋሙ ማህበራዊ ሃሊፊነቱን ለመወጣት የመሰረተው የበጎ አድራጎት ድርጅት ነው ።

27/09/2025
በ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን 400 ለሚሆኑ ተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ  ድጋፍ እድርገናል ። ድጋፉ የተደረገው ለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ በሚገኝበትበሰሜን ሸዋ ዞን እንሳሮ ወረዳ  ነው ...
16/09/2025

በ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን 400 ለሚሆኑ ተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ እድርገናል ።

ድጋፉ የተደረገው ለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ በሚገኝበት
በሰሜን ሸዋ ዞን እንሳሮ ወረዳ ነው ።

በወረዳው ከተለያዩ ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ ኢኮኖሚያዊ አቅማቸው ዝቅተኛ ለሆኑ 400 ተማሪዎች የተከፋፈለ 4800 የመማሪያ ደብተር ፡ 2400 እርሳስና 2400 እስኪርብቶ የእንሳሮ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አከበረኝ አላማውን ጨምሮ ሌሎች የወረዳው አመራሮች በተገኙበት ነው ድጋፉ የተደረገው።

እንኳን ለአዲሱ አመት በሰላም አደረሳችሁ!ምግባችንን ከጎረቤቶቻችን ጋር እንካፈል! ብዙአየሁ ታደለና  ቤተሰቡ ፋውንዴሽን እንደሁልጊዜው ለአዲስ አመት ከወገኖቹ አልተለየም፡፡የዛሬ  ሁለት አመት...
10/09/2025

እንኳን ለአዲሱ አመት በሰላም አደረሳችሁ!

ምግባችንን ከጎረቤቶቻችን ጋር እንካፈል!

ብዙአየሁ ታደለና ቤተሰቡ ፋውንዴሽን እንደሁልጊዜው ለአዲስ አመት ከወገኖቹ አልተለየም፡፡

የዛሬ ሁለት አመት ምግባችንን ከጎረቤቶቻችን ጋር እንካፈል በሚል መሪ ቃል በጀመርነው የፍቅር ማዕድ በቪላ አፍሪካና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ማዕድ አጋርተናል፡፡

በብዙየሁ ታደለና ቤተሰቡ ፋንዴሽን የፍቅር ማዕድ በተደረገው መርሃ ግብር ላይ የልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ የ 8 ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ደረጄ ፈይሳና የብዙአየሁ ታደለና ቤተሰቡ ፋውንዴሽን ዋና ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ መሰረት ታደሰ ተገኝተዋል፡፡

አዲሱ አመት ለእርስዎና ለቤተሰብዎ የሰላም፣ የጤናና የስኬት ይሁን !

መልካም አዲስ ዓመት!

Address

Sarbet
Addis Ababa

Opening Hours

Monday 08:00 - 17:00
Tuesday 08:00 - 17:00
Wednesday 08:00 - 17:00
Thursday 08:00 - 17:00
Friday 08:00 - 17:00
Saturday 08:00 - 12:00

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Buzuayehu Tadele Family Foundation posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share