ኢትዮጵያ ወጣቶች ህብረት

ኢትዮጵያ ወጣቶች ህብረት ህብረት ከወጣትነት!

የሀዲያ ዞን ወጣቶች ማህበር ጽ/ቤት "በወጣቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎ የተሳካ ምርጫ" በሚል መሪ ሀሳብ ከሆሳዕና ከተማ ወጣቶች ጋር  የውይይት መድረክ አካሄደ።ሆሳዕና፣ሚያዚያ 16/2018 ዓ/ም ...
24/04/2026

የሀዲያ ዞን ወጣቶች ማህበር ጽ/ቤት "በወጣቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎ የተሳካ ምርጫ" በሚል መሪ ሀሳብ ከሆሳዕና ከተማ ወጣቶች ጋር የውይይት መድረክ አካሄደ።

ሆሳዕና፣ሚያዚያ 16/2018 ዓ/ም የሀዲያ ዞን ወጣቶች ማህበር ጽ/ቤት "በወጣቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎ የተሳካ ምርጫ" በሚል መሪ ሀሳብ ከሆሳዕና ከተማ ወጣቶች ጋር የውይይት መድረክ ያካሄደ ሲሆን በመድረኩ የሀዲያ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ዲሞክራሲና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ስዩም ደጉ፣የዞኑ ወጣቶች ማህበር ጽ/ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ስንታየሁ አለማየሁ፣ የሆሳዕና ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኪበሞ ሰለሞንን ጨምሮ የዞን እና የሆሳዕና ከተማ ወጣት አደረጃጀቶች ተገኝተዋል።

የሀዲያ ዞን ብልጽግና ፓርቲ ዲሞክራሲና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ስዩም ደጉ እንደገለፁት ወጣቶች ለ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ቅድመ ዝግጅት እንቅስቃሴ ላይ እያደረጉት ላለው ብርቱ ጥረት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

አያይዘውም የዛሬው መድረክ ከዚህ በፊት በወጣቶች ለተሰሩ ስራዎች እውቅና የሚሰጥበት እና ቀጣይ ለምንሰራቸው ሥራዎች አቅጣጫ የምንይዝበት ነው በማለት ተናግረዋል።

ወጣቶችን የብልጽግና መንግስት ይፈልጋቸዋል ያሉት አቶ ስዩም ደጉ አፍራሽ ሀይሎችም ወጣቱን ለእኩይ አላማቸው መጠቀም ስለሚፈልጉ የዞናችን ወጣቶች የተለመደውን በጎ ስብዕና በማስቀጠል 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊ እንዲሆን ከወዲሁ መስራት ይጠበቅባችኋል ብለዋል።

የሀዲያ ዞን ወጣቶች ማህበር ጽ/ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ስንታየሁ አለማየሁ በበኩላቸው የሆሳዕና ከተማ ወጣቶች ህዝቡ የምርጫ ካርዲ እንዲያወጣ ከመቀስቀስ እና ግንዛቤ ከመፍጠር ጀምሮ ላበረከቱት ጉልህ ሚና ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

7ኛው ሀገራዊ ምርጫ የተሳካ እንዲሆን የወጣቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎ የላቀ መሆኑን የገለፁት አቶ ስንታየሁ የምርጫው ቀን እስኪደርስ ለመራጩ ማህበረሰብ ግንዛቤ መፍጠርና በምርጫው ቀን ሁሉም በነቂስ ወጥቶ እንዲመርጥ ማድረግ ከወጣቱ ይጠበቃል ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የሆሳዕና ከተማ ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኪበሞ ሰለሞን አክለው በሆሳዕና ከተማ በሁሉም ቀበሌዎች ህዝቡ የምርጫ ካርድ እንዲወስድ የተደረገው ብርቱ ጥረት በሁሉም መስክ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል በማለት ጠቁመዋል።

የሆሳዕና ከተማ የወጣቶች ስብዕና ማዕከል ለወጣቱ ክፍት ሆኖ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን ጠቅሰው ወጣቱ ትርፍ ጊዜውን አልባሌ ቦታ ከመዋል ወደ ወጣቶች ስብዕና ማዕከል በመሄድ እንዲዝናናም ጥሪ አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ መንግስት በትግርኛ ቋንቋ የህመምተኞች ፖለቲካ ብሎ የተናገሩት እነማንን ነው? በእርግጥ ተሜናል ። ነገር ግን ህመማችን ስለ ኢትዮጵያ ሰላም ፣አንድነት እና ብልፅግና እንጂ ስለ ካጆ...
05/03/2026

የኢትዮጵያ መንግስት በትግርኛ ቋንቋ የህመምተኞች ፖለቲካ ብሎ የተናገሩት እነማንን ነው? በእርግጥ ተሜናል ። ነገር ግን ህመማችን ስለ ኢትዮጵያ ሰላም ፣አንድነት እና ብልፅግና እንጂ ስለ ካጆች ፣አስመሳዮች ብሎም ስለ የገዛ እናታቸው ጡት ነካሾች አይዴለም። በእርግጥ ይህ ሀሳብ ጥሩ ነው ብለው ለመቀበል እራሱ በመጋራጃቸው ውስጥ ከልሆነ በስተቀር በአደባባይ ብሎም በግልጽ ጥሩ አስተሳሰብ ነው ብሎ ለመቀበል ሽንፈታቸው አድርገው ይወስዳሉ። መታመም ማንም ይተመማል። ነገር ግን ጠባሳ ሆኖበት ይቀራል እንጂ ታሞ የማይድን በሽተኛ ዬለም።

ሚንልክ በአደዋ ድል ከቀኝ ግዛት ነፃ አወጣን። ደርግ ከከበርቴ እና ከበለመሬት ጭኮና ነፃ አወጣን። ኢህአዴግ ከመለኮታዊና ከአሃዳዊ እምነት አስተሳሰብ ነፃ አወጣን። ነገር ግን ይህ ሁሉ ስርዓ...
02/03/2026

ሚንልክ በአደዋ ድል ከቀኝ ግዛት ነፃ አወጣን። ደርግ ከከበርቴ እና ከበለመሬት ጭኮና ነፃ አወጣን። ኢህአዴግ ከመለኮታዊና ከአሃዳዊ እምነት አስተሳሰብ ነፃ አወጣን። ነገር ግን ይህ ሁሉ ስርዓት /መንግስታት እስከአሁን ድረስ እኛን ነፃ ማውጣት የተሳናቸው ነገር አለ። ይህም የአስተሳሰብ ጫና ወይም ባሪነት ነው። ይህ ጫና ከፖለቲካ ፣ ከዘረኝነት፣ ከሰፈርተኝነት ፣ አልፎ አልፎም ከእምነት እና ከአክራሪነት ጋር ተዋህዶ ያለውና ከቀኝ ግዛት፣ ከከበርቴ እንዲሁም ከመለኮታዊ ባሪነት በላይ የአትዮጵያውያንን እንዲሁም የአፍርካውያንን አእምሮ ተቆጣጥሮ ያለው ባሪነት ነው። ይህ ባሪነት ለምን አሰባችሁ ባይልም እንኳ ስለምተነሰው ሀሳብ ወይም ችግር ቀጥተኛ መፍትሔ ብሎም እውቅና አይሰጥም። ይልቁንም አስተዳደራዊ በደል እና ከላይ ያዘረዘርኳቸው አካል ጉዳተኛ አመለካከቶች በተዘዋዋሪ አንቴ/ች ላይ እንድ ፀኑ ያደርጋል። ለምሳሌ፦ በኢህአዴግ ዘመን በተለያዩ ግዜ ፅፌሃል፣ ተናግሬሃል በማላት ወህን ቤት አስገብቶኝ የአእምሮ ጉዳት አድርሰውብኛል። ነገር ግን የዛሬው አስተዳደር እስከአሁን ድረስ በየሰስረኝም እንኳ ዛሬም እንደ ትላንትናው "ለምን ተናገረ? ፣ አፉን ዘግተው አይቀመጥም? ፣ እሱን ምን አገባው? ፣ እኛ የሚንናገር ጠፍቶን ነው? " በማላት ይዘምቱብኛል። ሌለው ቀርተው የብልፅግና አባል ሆነህ ለምን በብልፅግና ስም ትታገለዋለህ? በማላት ተከስሼ አውቃለሁ። ይሁን እንጂ ከዚህ ከአስተሳሰብ ባሪነት መቼና በማን ነፃ እንደሚን ወጣ የእኔ ጥያቄ ብቻ ሳይሆን "ለምን ትናገራለህ?" ብለው ለሚከሱኝም ጭምር ነው።

ዓለም አቀፍ የወጣቶች ቀን እየተከበረ ነውበየዓመቱ ነሐሴ 6 የሚከበረው ዓለም አቀፍ የወጣቶች ቀን የወጣቶችን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ አስተዋጾ አጉልቶ ለማሳየት ያለመ ነው።ዕለቱ ...
12/08/2025

ዓለም አቀፍ የወጣቶች ቀን እየተከበረ ነው

በየዓመቱ ነሐሴ 6 የሚከበረው ዓለም አቀፍ የወጣቶች ቀን የወጣቶችን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ አስተዋጾ አጉልቶ ለማሳየት ያለመ ነው።

ዕለቱ ለመጀመሪያ ጊዜ በይፋ የተከበረውም እ.አ.አ በ2000 ነበር።

እያንዳንዱ ዓለም አቀፍ የወጣቶች ቀን ከዘላቂ ልማት እስከ ዲጂታል እድገት፤ ከማህበራዊ እኩልነት እስከ አየር ንብረት ለውጥ ድረስ የተለያዩ ዓለም አቀፍ ክስተቶች ላይ ትኩረት በመስጠት ይከበራል።

የዘንድሮው ዓለም አቀፍ የወጣቶች ቀን ደግሞ “የወጣቶች ማህበረሰባዊ ተሳትፎ ለዘላቂ የልማት ግቦች” በሚል መሪ ሃሳብ ይከበራል።

ሃሳቡም የወጣቶች መሰረታዊ ተሳትፎ ለዘላቂ የልማት ግቦች መሳካት እና አካታች ማህበረሰቦችን ለመፍጠር አስፈላጊ ነው የሚል መልዕክት አለው ።

ዓለም አቀፉ የወጣቶች ቀን መከበር ወጣቱን በማብቃት ቀጣይነት ካለው እድገት ጋር የማይነጣጠል ትስስር እንዳለው የሚያሳይ ነው።

ወጣቶች በዓለም አቀፍ ደረጃ የለውጥ ፈጣሪ መሃንዲሶች ናቸውና በዛሬው ዕለትም ወጣቶች ከአስተዳደር፣ ከኢኮኖሚያዊ ተሳትፎ እና ባሕላዊ እሴቶችን ከማጎልበት አንፃር ያላቸው ሚና ይታወሳል።

የዘንድሮው የወጣቶች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ25ኛ ጊዜ፤ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ22ኛ ጊዜ እየተከበረ ይገኛል።

በሴራን ታደሰ

#ዓለምአቀፍየወጣቶችቀን

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ኢትዮጵያ ወጣቶች ህብረት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share