Yared Hiruy Foundation

Yared Hiruy Foundation መጽሐፉ ምሳሌ 19:17
---
"ለድኾች የሚሰጥ ለእግዚአብሔር እንዳበደረ ይቆጠራል፣ እግዝአብሔርም የመልካም ስራውን ዋጋ ይከፍለዋል"
#መስጠትና አመስጋኝነት እውነተኛ ደስታ ያስገኛል!

ቤጂንግ-የቻይና መሪ በታይዋን ጉዳይ የዩናይትድ ስቴትስ እንግዳቸዉን አሳሰቡዩናይትድ ስቴትስና ቻይና በታይዋን ጉዳይ ላይ ካልተግባቡ የሁለቱ ሐገራት ልዩነት ወደ ግጭት እንደሚንር የቻይና መሪ ...
14/05/2026

ቤጂንግ-የቻይና መሪ በታይዋን ጉዳይ የዩናይትድ ስቴትስ እንግዳቸዉን አሳሰቡ

ዩናይትድ ስቴትስና ቻይና በታይዋን ጉዳይ ላይ ካልተግባቡ የሁለቱ ሐገራት ልዩነት ወደ ግጭት እንደሚንር የቻይና መሪ አስጠነቀቁ።የቻይና ኮሚንስት ፓርቲ ዋና ፀሐፊና የሐገሪቱ ፕሬዝደንት ሺ ጂፒንግ ሐገራቸዉን በመጎብኘት ላይ ለሚገኙት ለዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ እንደነገሩት የታይዋን ጉዳይ ለቻይና «ጥያቄ ሊቀርብበት የማይገባ» መሠረታዊ ጉዳይ ነዉ።ቻይና እ.ግ.አ ከ1949 ጀምሮ ከዋና ግዛትዋ የተገነጠለችዉን ታይዋንን አሁንም ድረስ የግማደ ግዛትዋ አካል አድርጋ ትቆጥራታለች።ዩናይትድ ስቴትስና ተባባሪዎችዋ ባንፃሩ ለታይዋን የነፃ ሐገርነት ዕዉቅና ባይሰጡም ለታይፔ አስተዳደር ዘመናይ ጦር መሳሪያ ማስታጠቅን ጨምሮ ሁለንተናዊ ድጋፍ ያደርጋሉ።ፕሬዝደንት ትራምፕ ከትናንት ጀምሮ በቻይና የሚያደርጉት ጉብኝት ሁለቱ ኃያል፣ የዓለም ሐብታም ሐገራት በታይዋን፣ በኢራን ጦርነትና በንግድ ልዉዉጥ ላይ ያላቸዉን ልዩነት ለማጥበብ ይረዳል የሚል ግምት አሳድሮ ነበር።የዜና ምንጮች እንደዘገቡት ግን ትራምፕና ሺ ዛሬ ለሁለት ሰዓታት ባደረጉት ዉይይት በሶስቱም ጉዳዮች ላይ የተጠበቀዉን ያክል አልተግባቡም።የአሜሪካዉ ዜና አገልግሎት AP የቻይና ዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር በX ገፁ ያሰራጨዉን መረጃ ጠቅሶ እንደዘገበዉ ሺ ለአሜሪካዉ እንግዳቸዉ « ሁለቱ ሐገራት በታይዋን ጉዳይ ከተስማሙ አጠቃላይ ግንኙነታቸዉ ይሰምራል፣ ይሕ ካልሆነ ግን ሁለቱ ሐገራት መቃቃራቸዉ ምናልባትም መጋጨታቸዉ አይቀርም።» ብለዋል።ሁለቱ መሪዎች በዝግ ከመነጋገራቸዉ በፊት ግን አንዱ ሌላዉን ሲያደንቁና ሲያወድሱ ነበር።ለፕሬዝደንት ትራምፕ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋልም።

14/05/2026

የሆነ ጊዜኮ ለድመት ሁላ ወተት ተከራይተን ነበር 🙃
🐈🐯🐈

"ጌታቸው፡ 'ሴዶ ቃሉን ጠባቂና እውነተኛ ኪንግ መሆኑን አሳይቷል'""እንግዲህ ጌታቸው እንደገለጸው፣ ሴዶ ብዙዎቻችሁ እንደምታስቡት ሰው አለመሆኑን ዛሬ በተግባር አሳይቷል። ብዙዎች የተለያዩ ም...
14/05/2026

"ጌታቸው፡ 'ሴዶ ቃሉን ጠባቂና እውነተኛ ኪንግ መሆኑን አሳይቷል'"

"እንግዲህ ጌታቸው እንደገለጸው፣ ሴዶ ብዙዎቻችሁ እንደምታስቡት ሰው አለመሆኑን ዛሬ በተግባር አሳይቷል። ብዙዎች የተለያዩ ምክንያቶችን በመደርደር ከፋይቱ ሲርቁ፣ ሌሎች ደግሞ በማህበራዊ ሚዲያ የሚባሉ ነገሮችን በመፍራት እኛኑ እየወቀሱ ወደኋላ ብለዋል።

ሴዶ ግን 'እኔ ፈሪ አይደለሁም፤ እኔ ማርሻል አርቲስት ነኝ፣ እኔ ንጉሥ ነኝ' እንዳለው ሁሉ ቃሉን አክብሮ ቀርቧል። 'የአምስት ወይም የአስር ሚሊዮን ብር ጉዳይ አያሳስበኝም፤ የእናንተ ገንዘብ ቢቀርም እንኳ በነጻ ፋይት ለማድረግ ዝግጁ ነኝ' በሚል ቁርጠኝነት ፋይቱን ለማድረግ ወስኗል።

ይህ የውል ስምምነት እንዲፈጸም እና ሴዶ ፋይቱን እንዲያደርግ የስፖርቱ አፍቃሪዎችና የአዲስ አበባ ኢንቴግሬትድ ማርሻል አርት ኃላፊዎች በመምጣት አዋውለውን ፋይቱ የሚደረግ ይሆናል። የፋይቱ ቀንም በቅርቡ ለሁላችሁም ይፋ እንደ ሚደሩ ጌታቸው ገልጿል።"

በክልሉ የፖለቲካ አመራር ላይ አዲስ ለውጥ በታየበት በዚህ ወቅት፣ ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ለሳዑዲ አረቢያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ልዑል ፋይሰል ቢን ፋርሃን አል ሳኡድ ይፋዊ ደብዳቤ መፃፋ...
14/05/2026

በክልሉ የፖለቲካ አመራር ላይ አዲስ ለውጥ በታየበት በዚህ ወቅት፣ ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ለሳዑዲ አረቢያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ልዑል ፋይሰል ቢን ፋርሃን አል ሳኡድ ይፋዊ ደብዳቤ መፃፋቸው ተሰምቷል።

በደብዳቤውም በሀገሪቱ የሞት ፍርድ የተፈረደባቸው በመቶዎች የሚቆጠሩ የትግራይ ተወላጆች ምሕረት እንዲደረግላቸው ተማፅነዋል።

ዶክተር ደብረፅዮን በደብዳቤያቸው እንዳረጋገጡት፣ እነዚህ ስደተኞች ወንጀለኞች ሳይሆኑ በትግራይ በተፈጠረው አውዳሚ ጦርነት፣ እንዲሁም ባስከተለው ሰብአዊ ቀውስ ምክንያት ህይወታቸውን ለማዳን ወደ ሳዑዲ ዓረብያ የተሰደዱ ናቸው። የሳዑዲ መንግስት ለነዚህ ዜጎች ምህረት በማድረግ ከሌሎች አስከፊ እርምጃዎች እንዲጠብቃቸው የተጠየቀ ሲሆን፣ ይህ የምህረት እርምጃ በሁለቱም ህዝቦች መካከል ያለውን ታሪካዊ ግንኙነት የበለጠ እንደሚያጠናክር ተመላክቷል።

ይህ በትግራይ መሪ በኩል የተወሰደው ተነሳሽነት በብዙዎች ዘንድ ትኩረት ያገኘ ቢሆንም፣ የኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት እስካሁን ድረስ እንዲህ ያለውን ይፋዊ ጥያቄና የዲፕሎማሲ ደብዳቤ ለሳዑዲ መንግስት አለመላኩ አነጋጋሪ ሆኗል። ዶክተር ደብረፅዮን የሳዑዲ አረቢያ መንግስት ከሚመለከታቸው ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በመተባበር፣ ስደተኞቹ ወደ ትግራይ በሰላም የሚመለሱበትን ሁኔታ እንዲያመቻች የጠየቁ ሲሆን፣ የሳዑዲ መንግስት የሰውን ህይወት ለማዳን ሲል ፍርዱን ሳይፈጽም ስደተኞች በምሕረት ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ያደርጋል የሚል ጽኑ እምነት እንዳላቸውም ገልጸዋል።

 #ሰበር  #ዜና    ከብዙ ሐሳብ መቀያየር በሗላ እንደሚፋለም በማረጋገጥ ፊርማዉን አኑሯል።
14/05/2026

#ሰበር #ዜና
ከብዙ ሐሳብ መቀያየር በሗላ እንደሚፋለም በማረጋገጥ ፊርማዉን አኑሯል።

13/05/2026

አግዙዋቸው፣ አትርፉዋቸው🙏

13/05/2026

አግዙት

13/05/2026

ተሓረደ ተስፋይ ተኸሸነ ተስፋይ ምንም ዘይጓድሎ ካብ ጣዕሙ ድዩ ካብ ኣመራርፃ ብዕራዩ ዋግኡ 1200ቅርሺ ንኺሎ ኣቀባብላ ዓማዊሉ ዓድዋ ባዓል ዋና ደብርቺ ስጋቤት ዝኾንካ ኣይተ ተስፋይ ሃይለ በየነ ኽበረልና!

አሜሪካ ኢትዮጵያን እና ኤርትራን አስጠነቀቀች!!ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ!!አረብ ኤሚሬት እና ኢትዮጵያ ምሥራቅ አፍሪካን እያተራመሱ ነው!!አሜሪካ ኤርትራ ላይ የጣለችውን ማዕቀብ ልታነሳ ነ...
13/05/2026

አሜሪካ ኢትዮጵያን እና ኤርትራን አስጠነቀቀች!!

ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ!!
አረብ ኤሚሬት እና ኢትዮጵያ ምሥራቅ አፍሪካን እያተራመሱ ነው!!
አሜሪካ ኤርትራ ላይ የጣለችውን ማዕቀብ ልታነሳ ነው!! አሉላ ሰለሞን በምሽት ክለብ!!
በዋጎኽምራ ድርቅ ተከሰተ!!
በሶማሊያ ድርቅ ተከስቷል!!
በትግራዩ ጦርነት መከላከያ ሠራዊት መዋጋት አልቻለም ነበር!!
አማራ የጦር መሳሪያ የታጠቀው ከTDF ማርኮ ነው!!
የሃምዳን ደጋሎ ሠራዊቶች የሚዘገንን ጭፍጨፋ እያደረጉ ነው!!
አረብ ኤሚሬት እና አሜሪካ በሱዳን ጉዳይ ተጣሉ!! የኢትዮጵያ ሠራዊት ወደ ሱዳን ደንበር ተጠጋ!!
በኮሪደር ልማቱ የተፈናቀሉ ዜጎች ከቆሻሻ አንሰናል አሉ!! ቆሻሻ እንኳን ገንዳ ይጣላል!!
➖➖
ምሥራቅ አፍሪካ የሚታወቀው በከፋ ድህነት ፣ በድርቅ ፣ በጦርነት ፣ አሸባሪዎች የሚያምሱት ቀጠና ነው። መሪዎቹ የራሳቸውን ጥቅም ነው የሚያሳድዱት። ሰሞኑን በሶማሊያ ድርቅ ተከስቶ በእርሃብ ህፃናት ሞተዋል። የቤት እንስሶች አልቀዋል።

በኢትዮጵያም በሰሜኑ ክፍል ዋግኽምራ ድርቅ ተከስቶ በሺዎች የሚቆጠሩ የአካባቢው ነዋሪዎች ለመሰደድ ተገደዋል። በኢትዮጵያ በርካታ ታጣቂዎች ተፈልፍለዋል። ደቡብ ሱዳን እየተተራመሰች ነው። ሰሜን ሱዳን በሃምዳን ደጋሎ እና በዓልቡርሃን መካከል የሚደረገው ጦርነት በዘግናኝነቱ ቀጥሏል።

አብይ አህመድ ትላንት ኬኒያ ናይሮቢ ነበሩ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌዲዮን ጢሞቲዎስ ወደ ዋሽንግተን አምርተው ከአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርክ ሩቢዮ ጋር ተነጋግረዋል። አሜሪካ በኤርትራ ላይ የጣለቸውን ማዕቀብ ልታነሳ ነው መባሉን ሮይተርስ የዜና ወኪል የአሜሪካ ባለስልጣናትን ጠቅሶ ዘግቧል። ይሄ ደግሞ የኢትዮጵያ ባለስልጣናትን አናዷል።

በሱዳን ጦርነት የተነሳ ምሥራቅ አፍሪካ ተተራምሷል። አሜሪካ ጥቅሟን ለማስከበር ሁሉንም ኃይሎች እረፉ ለማለት ተገዳለች። መካከለኛው ምሥራቅ ተመሰቃቅሏል። በኢራን በአሜሪካ እና በእስራኤል የነበረው ጦርነት በተኩስ አቁም ጋብ ቢልም....አሜሪካ ጦርነቱን እንደገና ልትጀምረው ነው ሲል አግዚኦስ የአሜሪካ ባለስልጣናትን ጠቅሶ ዘግቧል። ለመካከለኛው ምሥራቅ ቅርብ የሆነው ምሥራቅ አፍሪካ ቀውስ ውስጥ እንዲገባ አሜሪካ አትፈልግም።

የኢትዮጵያ መንግሥት የውስጥ ችግሩን ሳይፈታ ኤርትራን አንበርክኬ አሰብ ወደብን እወስዳለሁ ካለ ሰንበትበት ብሏል። አብይ አህመድ በትግራይ ከባድ ጦርነት አካሂደዋል። ሠራዊታቸው ከባድ ወንጀሎችን ፈፅሟል። የተንቀሳቃሽ ምስሎች እና የሰነድ መረጃዎች በሰብዓዊ መብት ተሞጋቾች እና በስለላ ተቋማት ይገኛል። የትግራዩ ጦርነት በስምምነት ተጠናቀቀ ቢባልም ፣ ጦርነት ጦርነትን ይወልዳልና ሠራዊታቸውን ከትግራይ አንስተው ወደ አማራ ክልል አሰማሩት።

በትግራዩ ጦርነት ጊዜ መከላከያ ሠራዊቱ ከህውሓት ጋር መዋጋት አልቻለም ነበር። አብይ አህመድም:- የህውሓትን ሠራዊትን በመደበኛ ሠራዊት ማሸነፍ ሰለማይቻል ፣ ሁሉም የአማራ ህዝብ ወጥቶ ጠላቱን መዋጋት አለበት ፣ ከህውሓት ሠራዊት ጦር መሳሪያ ከማረከ የራሱ ነው አሉ። ህውሓትም ሲዋጋ የነበረው በህዝብ ማዕበል ነበር። የአማራ ህዝብ ባዶ እጁን ወጥቶ ከህውሓት ሠራዊት ክላሽ ፣ መትረየስ ፣ ዲሽቃ ፣ ላውንቸር ማረከ።

በብልጽግና እና በህውሓት መካከል ደቡብ አፍሪካ ላይ ሲስማሙ። አብይ አማራ የጦር መሳሪያ ታጥቋል ፣ አስፈታዋለሁ ብለው ገቡበት። በሶሥት ሳምንት ይጠናቀቃል የተባለው ጦርነት ዓመታትን እያስቆጠረ ነው። አብይ በአማራ ክልል ጦርነት ሲጠመዱ ህውሓት ሲዘጋጅ ከርሟል። አሁን ላይ ህውሓት አብይን ምን ታመጣለህ ወደ ማለት ተሸጋግሯል።

የትግራይን ወጣት አሜሪካ ቁጭ ብሎ በፕሮፖጋንዳ ያስጨረሰው አሉላ ሰለሞን በምሽት ክለብ ሺሻ ሲያጨስ የሚያሳይ ተንቀሳቃሽ ምስል ተለቋል። አሉላ ሰለሞን በትግራዩ ጦርነት ወቅት ጦርነት ማለት ለትግራይ ህዝብ ባህላዊ ጨዋታ ነው በሚል ንግግሩ ይታወቃል። TMH የተባለ ቴሌቬዥን ጣቢያ አቋቁሞ ነበር።

ለ TMH እና ለትግራይ እናቶች ድጋፍ እናድርግላቸው ብሎ ጎፈንድሚ በመክፈት ከትግራይ ዲያስፖራ 700 ሺህ ዶላር መሰብሰብ ችሏል። ያንን 700 ሺህ ዶላር ቨርጂያ ላይ ቤት ገስቶበታል። እንዲሁም ተደሮበታል። ገንዘብን መውደድ አደጋ አለው። ብልጽግና የበለጠ ሲከፍለው ለብልጽግና አደረ።

ሞጣ ቀራኒዮ እና ወርቁ አይተነው ሺሻ እያጨሱ ነው እያለ ሲሳለቅ የነበረው አሉላ ሰለሞን አሁን እሱ ብሷል። ሲያቦነው ታይቷል። ህውሓት ይልቀቅበት ብልጽግና ብቻ አሉላ ተዋርዷል። ቴዲ አፍሮን ሲሳደብ ነው የሰነበተው። አማራን ፎጣ ለባሽ እያለ ለማሸማቀቅ ሞክሯል። የአማራ ጠላቶች መጨረሻቸው ወርደት መሆኑን አሉላ ማሳያ ነው።

አረብ ኤሚሬት እና አሜሪካ በሱዳን ጦርነት የተነሳ ወዳጅነታቸው ቀንሷል። አረብ ኤሚሬት ሃምዳን ደጋሎን ትደግፋለች። የደጋሎ ሠራዊቶች ህፃናት ፣ አዛውንት ፣ ሴት ሳይሉ በዘግናኝ ሁኔታ ሲገድሉ የሚያሳይ ተንሳቃሽ ምስል መውጣቱን ተከትሎ ዓለም አዝኗል። የደጋሎ ሠራዊቶች በሞባይላቸው እየቀረፁ ነው ሲገድሉ የነበረው። አረብ ኤሚሬት የምትደግፋቸው ታጣቂዎች ዘግናኝ ወንጀሎችን በመፈፀም ይታወቃሉ።

የአብይ አህመድ አለቃ የአረብ ኤሚሬቱ ንጉሥ ቢን-ዛይድ ለአብይ የጦር መሳሪያ እየሰጡ በአማራ እና በትግራይ ዘግናኝ ጭፍጨፋዎችን ፈፅመዋል። ኢትዮጵያን ተጠቅመው ለሃምዳን ደጋሎ ድጋፍ እያደረጉ በሚዘግንን ሁኔታ ሱዳናዊያንን እየጨፈጨፉ ነው። በቤሻንጉል ጉሙዝ ክልል የደጋሎ መልምሎች እየሰለጠኑ ነው። የቆሰሉትም በኢትዮጵያ አየር መንገድ አዲስ አበባ ሒደው ይታከማሉ። አብይ የኢትዮጵያን አየር መንገድን ማዋረዳቸውን ቀጥለዋል።

የአረብ ኤሚሬት ድሮን ከባህርዳር ተነስታ የካርቱምን ኤርፖርት ደብድባለች። ዓልቡርሃን ምላሽ እሰጣለሁ ብለዋል። የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ወደ ሱዳን ደንበር ተጠግቷል። የዓልቡርሃን ሠራዊትም ወደ ኢትዮጵያ ደንበር ተጠግቷል። ዓልቡርሃንን የሚደገፉት ሐገራት ሳውዲ አረቢያ ፣ ኤርትራ ፣ ግብፅ ናቸው። አሁን ደግሞ አሜሪካ እና እስራኤል ዓልቡርሃንን እየደገፉ ነው።

ካርቱም ኤርፖርት ሲመታ ለማውገዝ ግብፅን የቀደመ አልነበረም። ኢትዮጵያ ቀጠናውን እያተራመሰች ነው ስትል ከሳለች። አንዷ በጥባጭ ግብፅ መሆኗን ማን በነገራት? ግብፅ ፣ ኤርትራ ፣ ሳውዲ አረቢያ ወዳጆች ናቸው። ባለፈው የሳውዲው ልዑል ቢን-ሳልማን አሜሪካ ሒደው በኋይትሐውስ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

የሳውዲው ልዑል ለትራምፕ:- ኤርትራ ላይ የተጣለውን ማዕቀብ እንዲነሳ ጠይቀው ሊሆን ይችላል? ሳውዲ ዓልቡርሃንን የምትደግፈው በኤርትራ በኩል ነው። አብይ አህመድ ደግሞ ኤርትራን ለመውጋት እየተገለገሉ ነው። ከኋላ ይህንን የምትሰራው አረብ ኤሚሬት ናት። ሳውዲ አረቢያ እና አረብ ኤሚሬት በመካከለኛው ምሥራቅ እና በምሥራቅ አፍሪካ የበላይ ለመሆን በሚያደርጉት ፍትጊያ ሁለቱ ሐገራት ተቃቅረዋል።

ሳውዲ የምትደግፈውን ፣ አረብ ኤሚሬት ታጠቃለች። አረብ ኤማሬት የምትደግፈውን ሳውዲ አሰቢያ ታጠቃለች። ሁለቱ ሐገራት በምሥራቅ አፍሪካ በሚያደርጉት የበላይነት የንፁኃንን ነፍስ እየቀጠፈ ቀጥሏል። በዚህ የተነሳ ባብኤል መንደብ አደጋ ውስጥ እየገባ ነው። ሆርሙዝ ተዘግቶ መፈናፈኛ ታጥቷል። ምሥራቅ አፍሪካ ቀውስ ውስጥ ከገባ ደግሞ ባብኤል መንደብ የአሸባሪ መነኻሪያ ሊሆን ነው። አሜሪካ ይሄ ስጋት ገብቷታል። ስለዚህ ቀጠናውን ለማስተካከል ኢትዮጵያንና ኤርትራን አርፋችሁ ተቀመጡ፣ ቀጠናውን አትበጥብጡ ስትል ሁለቱን ሐገራት በማስጠንቀቅ ላይ ናት።

የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን የአፍሪካ ሶሥት ሐገራትን ለመጎብኘት ወደ አፍሪካ ተጉዘዋል። ግብፅን ከጎበኙ በኋላ ወደ ኬኒያ አምርተዋል። ኬኒያ ጉባዔ ትላንት ተካሂዷል። አብይ አህመድም ጉባዔውን ለመታደም ነው ኬኒያ የሔዱት። አብይ አህመድ ትላንት ማታ ኢትዮጵያ ገብተዋል። ለማክሮን አቀባበል ለማድረግ ቀድሞው ወደ ሐገራቸው ገብተዋል። ማክሮን አዲስ አበባ ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል።

አብይ አህመድ ህዝብን መበደላቸውን ቀጥለዋል። ከተማ አሳምራለሁ ብለው የዜጎችን ቤት አፈራርሰው ጎዳና ላይ ጥለዋቸዋል። በኮሪደር ልማቱ የተፈናቀሉ ዜጎች:- ቆሻሻ እንኳን ማረፊያ አለው ፣ ገንዳ ይጣላል ፣ እኛ ሰዎች ግን ቤታችን በመንግሥት ፈርሶብን ከቆሻሻ አንሰናል ሲሉ በምሬት እና በተስፋ መቁረጥ ተናግረዋል። የት እንሒድ ሲሉ ግራ በመጋባት ስሜት ተናግረዋል።

አብይ ይህንን ወንጀል በዜጎች ላይ እየፈፀሙ ዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ ምንም አላለውም። ዲያስፖራው ድምፅ ሊሆን ይገባል። አዲስ አበባ የተብለጨለጨችው ድሃን አፈናቅላ ከቆሻሻ አሳንሳ መሆኑን ዲያስፖራው ለዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ ማሳወቅ አለበት።

በቅርቡ በሽሮ ሜዳ አቶ ተገኝ ባልቻ በፖሊስ አባል  ህይወቱ ማለፉ ይታወሳል። ይህንን ድንገተኛ ክስተት ተከትሎ የጉለሌ ክፍለ ከተማ የተሰማውን ጥልቅ ሃዘን ድርጊቱ ከተፈጸመ ዕለት ጀምሮ የሟች...
13/05/2026

በቅርቡ በሽሮ ሜዳ አቶ ተገኝ ባልቻ በፖሊስ አባል ህይወቱ ማለፉ ይታወሳል። ይህንን ድንገተኛ ክስተት ተከትሎ የጉለሌ ክፍለ ከተማ የተሰማውን ጥልቅ ሃዘን ድርጊቱ ከተፈጸመ ዕለት ጀምሮ የሟች ቤተሰቦችን በማጽናናትና ከጎናቸው በመሆን አብሮ አዝኗል እንደ አስተዳደር ለሟች ቤተሰብ አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ በገባው ቃል መሰረት ለአቶ ተገኝ ባልቻ ቤተሰብ የመኖሪያ ቤትና የመስሪያ ቦታ የሟች ቤተሰብ እና የሀገር ሽማግሌዎች ባሉበት አስረክቧል።

እኩል! ተአምር ነው... አይ ኳስ! አል ናስር 1 — 1 አል ሂላልዛሬ ሮናልዶ ዋንጫውን ከፍ አድርጎ ሊያነሳ ዓለም በጉጉት እየጠበቀችው ነበር። ሆኖም እግር ኳስ መጨረሻዋ እስከማይታወቅ ድረስ...
12/05/2026

እኩል! ተአምር ነው... አይ ኳስ!

አል ናስር 1 — 1 አል ሂላል

ዛሬ ሮናልዶ ዋንጫውን ከፍ አድርጎ ሊያነሳ ዓለም በጉጉት እየጠበቀችው ነበር። ሆኖም እግር ኳስ መጨረሻዋ እስከማይታወቅ ድረስ ድራማነቷን ዳግመኛ አሳይታለች።

በ98ኛው ደቂቃ ላይ — ጨዋታው ሊጠናቀቅ ሰከንዶች ሲቀሩ — የአል ናስር በረኛ ራሱ ላይ ባስቆጠረው ግብ (Own Goal) ጨዋታው 1 እኩል በሆነ አቻ ውጤት ተጠናቋል።

ኳስ ግን ምንድን ናት? የደስታው ዋዜማ በአንድ ቅጽበት ወደ ድንጋጤ የተቀየረበት፣ የአል አወል ፓርክ ደጋፊዎች በዝምታ የተዋጡበት አስገራሚ ምሽት ሆኗል።

⚽️⚽️⚽️

Address

Bole
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Yared Hiruy Foundation posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Organization

Send a message to Yared Hiruy Foundation:

Share