12/04/2026
ባለጠጋና ለጋሽ ወጣቶች በመሎ ኮዛ !!
የለጋሾች ወይም የበጎ አድራጊዎች ባህርይ እንደየግል ተነሳሽነታቸው ቢለያይም፣ አብዛኛውን ጊዜ ርኅራኄ እና ለሌሎች ማሰብ ለጋሾች የሌሎችን ችግር እንደ ራሳቸው አድርገው የመረዳት ችሎታ አላቸው።
ድጋፍ የሚያደርጉት በግዴታ ሳይሆን፣ በሌሎች ሕይወት ላይ ለውጥ ለማምጣት ካላቸው ቅን ፍላጎት በመነጨ ነው።
ማኅበረሰቡን የመርዳትና ያሉትን ሀብቶች ገንዘብ፣ ዕውቀት ወይም ጊዜ ለጋራ ጥቅም የማዋል የሞራል ግዴታ እንዳለባቸው ያምናሉ።
"ካለኝ ላይ ማካፈል አለብኝ" የሚል ጽኑ አቋም አላቸው።
እነዚህ ወጣት ባለጠጋዎች በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጎፋ ዞን መሎ ኮዛ ወረዳ ላሃ ከተማ ነዋሪዎች ይገርማል ብርሀኑ እና ሞኮንን ድንቁ ዛሬ ከ100 መቶ ሺህ ብር በላይ ለአቅመ ደካሞች ለግሰዋል። ይህ የሁለቱ ወጣቶች ባህርይ የሀብታሞች ባህርይ ሳይሆን የባለጠጎች ነው።
ወንድሞቼ ይገርማል እና ሞከ ባለጠግነት ከፈጣሪ የሚሰጥ ስጦታ በመሆኑ እንኳን ደስ አላችሁ እያልኩ መልካም ይሁን እላለው !!
ከናንተ ብዙ እንመራለን።
🇪🇹ወንድማችሁ አለሙ አይሳ