Baysh kolfe ባይሽ ኮልፌ

Baysh kolfe ባይሽ ኮልፌ ለመልካም ስራ ረፍዶ አያውቅም!!!
(1)

 ‼️    ጉሊቱ ጋር💖ምንም ሳንጎዳ በምንለግሰው ደም የታመሙ ህፃናትና እናቶችን ህይወት እንታደግ🙏የባይሽ ቤተሰብ መሆን የምትፈልጉ ደጋጎችም ኑ🙏  #እንጠብቃችኋለን!!ነገ እሁድ ሰኔ7 ጠዋት ...
13/06/2026

‼️ ጉሊቱ ጋር💖

ምንም ሳንጎዳ በምንለግሰው ደም የታመሙ ህፃናትና እናቶችን ህይወት እንታደግ🙏የባይሽ ቤተሰብ መሆን የምትፈልጉ ደጋጎችም ኑ🙏 #እንጠብቃችኋለን!!

ነገ እሁድ ሰኔ7 ጠዋት ከ3:00ሰዓት ጀምሮ ነው🙏 💖
"ለመልካም ስራ ረፍዶ አያውቅም"

0911136553
0921058425

ሮቤል ደምሴ ይባላል!ትላንት ሰኔ2 ልጆቹን ከት/ቤት አምጥቶ 10:30 አካባቢ ከቦሌ አራብሳ ድንገት ወጥቶ ጠፍቷል!ባለቤቱና ልጆቹ ተጨንቀዋል!!  #ሼር በማድረግ አፋልጉን🙏092192324109...
10/06/2026

ሮቤል ደምሴ ይባላል!ትላንት ሰኔ2 ልጆቹን ከት/ቤት አምጥቶ 10:30 አካባቢ ከቦሌ አራብሳ ድንገት ወጥቶ ጠፍቷል!ባለቤቱና ልጆቹ ተጨንቀዋል!! #ሼር በማድረግ አፋልጉን🙏
0921923241
0984754798
"ለመልካም ስራ ረፍዶ አያውቅም"

 ‼️  ኑ የባይሽ ቤተሰብ እየሆናችሁ ደማችሁን ለወገኖቻቹ ስጡ🙏 እሁድ  #ሰኔ7 በደማቅ ሁኔታ 26ተኛ ዙር የደም ልገሳ ፕሮግራም ይኖረናል!ሁላችሁም ተጋብዛችኋል🙏እንዳትቀሩብን🙏"ለመልካም ስራ...
10/06/2026

‼️

ኑ የባይሽ ቤተሰብ እየሆናችሁ ደማችሁን ለወገኖቻቹ ስጡ🙏 እሁድ #ሰኔ7 በደማቅ ሁኔታ 26ተኛ ዙር የደም ልገሳ ፕሮግራም ይኖረናል!ሁላችሁም ተጋብዛችኋል🙏እንዳትቀሩብን🙏
"ለመልካም ስራ ረፍዶ አያውቅም"

0911136553
0912121942
0913156086

 #26ኛ‼️ "እየሳቅን ደማችንን ለወገኖቻችን" እሁድ  #ሰኔ7  በደማቅ ሁኔታ 26ተኛ ዙር የደም ልገሳ ፕሮግራም ይኖረናል!ሁላችሁም ተጋብዛችኋል🙏እንዳትረሱት🙏"ለመልካም ስራ ረፍዶ አያውቅም"...
08/06/2026

#26ኛ‼️

"እየሳቅን ደማችንን ለወገኖቻችን" እሁድ #ሰኔ7 በደማቅ ሁኔታ 26ተኛ ዙር የደም ልገሳ ፕሮግራም ይኖረናል!ሁላችሁም ተጋብዛችኋል🙏እንዳትረሱት🙏
"ለመልካም ስራ ረፍዶ አያውቅም"

0911136553
0912121942
0913156086

 #አፋልጉኝ🤲🤲🤲አባታችን አቶ ጠና ሀይሌ ይባላሉ በቀን 30/09/2018 አዲስ አበባ ኮልፌ ልኳንዳ ኪቢያድ ከሚባል ሰፍር ካለው ቤታቸው ከቀኑ 8:00 ሰአት ላይ እንደወጡ አልተመለሱም ትንሽ ...
08/06/2026

#አፋልጉኝ🤲🤲🤲
አባታችን አቶ ጠና ሀይሌ ይባላሉ በቀን 30/09/2018 አዲስ አበባ ኮልፌ ልኳንዳ ኪቢያድ ከሚባል ሰፍር ካለው ቤታቸው ከቀኑ 8:00 ሰአት ላይ እንደወጡ አልተመለሱም ትንሽ የመርሳት ህመም ስላላቸው ያያቹ ወይ ያገኛቹ እባካችሁን ተባበሩን 🤲🤲🤲
0920026786
0921796231
Baysh kolfe ባይሽ ኮልፌ

 ‼️  #ያሳዝናልይህ ወንድማችን   ይባላል፣ከቤተሰቡ ከጠፋ 2ዓመት አልፎታል!የተጨነቀች እህቱ "እባካችሁን ወንድሜ ጠፍቶ ቀረብኝ ዛሬ ደግሞ ልደቱ ነበር እናት አባቱም እያለቀሱ ነው አግዙኝ"...
07/06/2026

‼️ #ያሳዝናል

ይህ ወንድማችን ይባላል፣ከቤተሰቡ ከጠፋ 2ዓመት አልፎታል!የተጨነቀች እህቱ "እባካችሁን ወንድሜ ጠፍቶ ቀረብኝ ዛሬ ደግሞ ልደቱ ነበር እናት አባቱም እያለቀሱ ነው አግዙኝ"ብላ በፌስቡክ ለጥፈነው እናንተ ደጋጎችን አስቸግረን ነበር፣

ትላንት አንድ ኮማንደር ነኝ የሚል ሰው በተቀመጠው የእህቱ ስልክ ደውሎ" ትክክለኛ እህቱ ነሽ?እስካሁንስ የት ሄዳችሁ ነው?ልጁ እኮ ጭንቅላቱን በጥይት ተመቶ በአፋር ክልል ወታደራዊ ካምፕ ተኝቶ ነው የሚገኘው፣ፎቶውን እልክልሻለሁ፣ብታይው ታውቂዋለሽ ወይ?ብሎ ጠየቃት!አዎ ወንድሜ አደል አለችው!

በፍጥነት Edit ተደርጎ የታመመ ሰው ፎቶ ልኮላት የተጨነቀች እህት ስታየው እውነትም ወንድሟ ሚኒሊክ መስሏት እንኳን በህይወት ኖረልኝ"ምንድነው ማድረግ ያለብኝ?"ብላ ጠየቀችው፣

አንቺ ተረጋጊ መቀበል ከቻልሽ ሹፌር አመቻችና ወደ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል እልክልሻለሁ፣ብሎ የተባባሪውን የሹፌር ስልክ ላከላት!

ምስኪን እህት ፅዮን ሹፌሩ የተባለው ጋር ደውላ አወሩ፣አይዞሸ እኔም ወንድ ልጅ አይደለሁ፣መውደቂያዬን አላውቅም፣ለራሴ ስል ነው መልካም ማደርገው፣አላት፣የነዳጅ 8000ብር ላከችለት፣ወደ አዲስ አበባ እስኪመጣ ኦክስጅኑ መነቀል ስለማይችል ተመላሽ የሚሆን ማስያዣ 23500 ይፈልጋሉ ብሏት በድጋሚ ላከችለት፣አድራሻዋን ጠየቃት ስደርስ እደውላለው አላት፣

ትላንት ቀኑን ሙሉ በጉጉትና በተስፋ ጠበቀችው፣በየመሀሉ ስትደወልለት እዚህ ደርሻለው እያለ ተስፋ ሰጥቷታል፣ ሲመሽ አሁንስ ወንድሜ የት ደረስክ ስትለው መተሀራ ነኝ ተዘጋጂ ብሏታል!

ቶሎ በመድረሱ ገርሟታል፣ቀኑን ሙሉ እያለቀሰች ለአመታት ድምፁ እንኳ የናፈቃት ወንድሟን ለማየት ጓጉታለች፣ "አይኑ ግን ያያል?ብላ ደጋግማ ጠይቃለች!እስክትዳብሰው ጓጉታለች!!

ሰዓታት ሄዱ ቀኑን ሙሉ ስትደውልለት የነበረው ሹፌር ስልኩ ዝግ ሆነ፣ኮማንደር የተባለው ጋርም ስትደውል "ጥሪ አይቀበልም" አላት፣ ደነገጠች ስታሰላስል እንደተጫወቱባት ተረዳች፣ወደ ፖሊስ አመራች፣ "ሸውደውሻል ሌቦች ናቸው" አመልክቺ አሏት!!

በሰው ህይወት የሚጫወቱ አረ መ ኔዎችን ህጉ እንዴት ይሆን የሚቀጣቸው?ከመስረቃቸው የሚሄዱበት የወንጀሉ ርቀት አስቡት እስኪ😭 በውሸት በተቀነባበረ ፎቶ እንዲህ ሆኖ ሲያዩ ሌላ የሚጎዳ እናት አባት ቤተሰብ አለ እኮ፣ እንዴትስ ነው የሚያስችላችሁ? እባካችሁን ሌሎቻትሁ ተጠንቀቁ‼️
እህቱ ፅዮን "ከኔ ተማሩ ከወንጀለኞች ራሳችሁን ጠብቁ🙏 "ብላችኋለች!እናንተም መረጃው ለብዙዎች እንዲደርስ ሌላ ሰው እንዳይሸወድ #ሼር አድርጉ🙏 ለምታውቁት ሁሉ አሳውቁ‼️
"ለመልካም ስራ ረፍዶ አያውቅም"

አባታችን አቶ እንቁሐዋርያት ጌታሁን(ባቡ) ይባላሉ! ከሚኖሩበት ሰሚት ሲኤምሲ ሚያዝያ 30 ከ ጠዋቱ 1:30 እንደ ወጡ አልተመለሱም የ ለበሱት ግራጫ ቀለም ሹራብ ክሬም ሱሪ ነበር። የሚጥል በ...
06/06/2026

አባታችን አቶ እንቁሐዋርያት ጌታሁን(ባቡ) ይባላሉ! ከሚኖሩበት ሰሚት ሲኤምሲ ሚያዝያ 30 ከ ጠዋቱ 1:30 እንደ ወጡ አልተመለሱም የ ለበሱት ግራጫ ቀለም ሹራብ ክሬም ሱሪ ነበር። የሚጥል በሽታም ይታመማሉ ቤተሰቦቻቸዉ ፍለጋ ላይ ናቸዉ እናም ሼር አድርጉልን በዚህ ስ.ቁ አሳዉቁን
0911548586 ,0912266535,0921213474

አፋልጉኝ 🤲🤲🤲አባታችን አቶ እንቁሐዋርያት ጌታሁን(ባቡ) ይባላሉ ከሚኖሩበት ሰሚት ሲኤምሲ ሚያዝያ 30 ከ ጠዋቱ 1:30 እንደ ወጡ አልተመለሱም የ ለበሱት ግራጫ ቀለም ሹራብ ክሬም ሱሪ ነበር...
06/06/2026

አፋልጉኝ 🤲🤲🤲

አባታችን አቶ እንቁሐዋርያት ጌታሁን(ባቡ) ይባላሉ ከሚኖሩበት ሰሚት ሲኤምሲ ሚያዝያ 30 ከ ጠዋቱ 1:30 እንደ ወጡ አልተመለሱም የ ለበሱት ግራጫ ቀለም ሹራብ ክሬም ሱሪ ነበር። የሚጥል በሽታም ይታመማሉ ቤተሰቦቻቸዉ ፍለጋ ላይ ናቸዉ
0911548586
0912266535
0921213474
Baysh kolfe ባይሽ ኮልፌ

"የሕክምና ልብሴ ልጄን ከስቃዩ አልሸፈነልኝም😭" ዶ/ር"ዶ/ር የሮም ጌታቸው እባላለሁ።ከስድስት ዓመት በላይ በህክምና ሙያ ውስጥ ሕሙማንን በማከም፣ የተሰበሩ ቤተሰቦችን በማጽናናት እና ለብዙዎ...
05/06/2026

"የሕክምና ልብሴ ልጄን ከስቃዩ አልሸፈነልኝም😭" ዶ/ር

"ዶ/ር የሮም ጌታቸው እባላለሁ።ከስድስት ዓመት በላይ በህክምና ሙያ ውስጥ ሕሙማንን በማከም፣ የተሰበሩ ቤተሰቦችን በማጽናናት እና ለብዙዎች ተስፋ በመሆን ኖሬያለሁ።በስራዬ ምክንያት ብዙ ወላጆች በልጆቻቸው አልጋ አጠገብ ሲያለቅሱ አይቻለሁ፣ብዙ ሰዎች ሕይወትን ለማትረፍ ሲታገሉ ተመልክቻለሁ። ዛሬ ግን ያ አባት እኔ ሆኛለሁ😭😭

የ3ዓመት ከ6 ወር ህፃን ልጄ በአጥንት ካንሰር ተጠቅቶ ከባድ የህክምና ፈተና ውስጥ ይገኛል። በየቀኑ ህመሙን ሲታገል ማየት፣ የልጄን ስቃይ እያየሁ ምንም ማድረግ አለመቻሌ ልቤን ይሰብረዋል።እንደ ሀኪም የበሽታውን ስም አውቃለሁ።እንደ አባት ግን የልጄን ህመም እሸከማለሁ😭

ልጄ ሕይወቱን ለማትረፍ ወደ ውጭ ሀገር ሄዶ ልዩ የአጥንት ቀዶ ጥገና እና ተከታታይ ህክምና ማድረግ ያስፈልገዋል። ለዚህም ከ3.5 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ተጠይቆብናል።

እኔ ሀኪም መሆኔ፣ ህዝቤን ለበርካታ አመታት በቅንነት ማገልገሌ ይህን ወጪ ለመሸፈን አላስቻለኝም።ሌሎችን የምናክም እጆቻችን፣ የራሳችንን ልጆች ለማዳን ሲያንሱ ማየት እጅግ ያማል!

የሕክምና ልብሴ ልጄን ከስቃዩ አልሸፈነልኝም። የዶክተርነት ማዕረጌም የልጄን ህመም አላስቆመውም።ዛሬ በፊታችሁ የቆምኩት እንደ ዶክተር ሳይሆን፣ልጁን ለማጣት የሚፈራ አባት ሆኜ ነው።

ውድ ወገኖቼ እባካችሁን ልጄ የመኖር እድል እንዲያገኝ፣በድጋሚ ሳቁን እንዳይ በአቅማችሁ የምትችሉትን እርዳታ እንድታደርጉልኝ እጠይቃለሁ።
ለእናንተ ትንሽ የሚመስለው አስተዋፅኦ ለልጄ ግን ሕይወት ሊሆን ይችላል።ሌሎችን ለማከም የቆምኩት እኔ ዛሬ ግን የራሴን ልጅ ለማዳን የወገኖቼን እጅ እጠብቃለሁ😭
ምንም ባታደርጉ እንኳ #ሼር በማድረግና በፀሎት አስቡት🙏
"ለመልካም ስራ ረፍዶ አያውቅም"

#አካውንት ዶ/ር የሮም ጌታቸው
ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ- 1000149557982
አባይ ባንክ - 2091011011819814
አዋሽ : 013201344371300
ቴሌ ብር: 0910119336
: https://www.gofundme.com/f/help-tsegabe-fight-cancer?lang=en_US&ts=1780047340

Address

Kolfe Addis Ababa
Addis Ababa

Telephone

+251912121942

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Baysh kolfe ባይሽ ኮልፌ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share