05/10/2025
✅ ሀቅቼክ የዓለም አቀፉ የእውነታ አጣሪዎች ትስስር International Fact-Checkers Network(IFCN) ዕውቅና ያለው ፈራሚ ሆነ!
በኢንፎርም አፍሪካ ስር የተቋቋመው የሀቅቼክ ሀቅን የሚያጣራ ተቋም የዓለም አቀፉን የሐቅ አጣሪዎች መረብ (IFCN) የስነ ምግባር መርሆዎች የተረጋገጠ ትስስር በይፋ መቀላቀሉን ስናበስር በታላቅ ደስታ ነው። ይህም ሐቅቼክን ከኢትዮጵያ የመጀመሪያውና ብቸኛው ሐቅን የሚያጣራ አገልግሎት ያደርገዋል።
ይህ እውቅና በኢትዮጵያና ከዚያም በላይ የሀሰተኛ መረጃን በመታገልና የመረጃ ምሉዕነትን በማስፋፋት ረገድ ለገለልተኝነት፣ ለግልጸኝነት እና ለተጠያቂነት ያለንን ቁርጠኝነት የሚያረጋግጥ ነው።
ይህ እውን እንዲሆን ላደረጉት ለአጋሮቻችን እንዲሁም ለቀድሞ ባልደረቦቻችን እና የሀቅቼክ የቡድን አባላት በሙሉ ከልብ የመነጨ ምስጋናችንን እናቀርባለን።
Read more: https://ifcncodeofprinciples.poynter.org/profile/haqcheck-inform-africa