አወሊያ ዕርዳታና ልማት ድርጅት

አወሊያ ዕርዳታና ልማት ድርጅት Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from አወሊያ ዕርዳታና ልማት ድርጅት, Non-Governmental Organization (NGO), Addis Ababa.

ARDO (አወሊያ ዕርዳታና ልማት ድርጅት) Official page Link: https://www.facebook.com/ardoeth
በጤና ዘርፍ :
በትምህርት ከኬጂ - ኮሌጅ
ለአቅመ ደካሞች ድጋፍና ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎች የሚሰራ ድርጅት ነው!

18/06/2026

awolia asco kg

18/06/2026

awolia kg

18/06/2026

awolia asko kg

ቀን እሮብ ሰኔ 10/2018የሜዳ ልማት በትርፍ መጋራት የወጣ የጨረታ ማስታወቂያየአወሊያ ዕርዳታና ልማት ድርጅት በዘርፉ ልምድና ዕውቀቱ ያላቸውና ሜዳውን አልምተው እና በጋራ ለመጠቀም የሚፈል...
17/06/2026

ቀን እሮብ ሰኔ 10/2018

የሜዳ ልማት በትርፍ መጋራት የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ

የአወሊያ ዕርዳታና ልማት ድርጅት በዘርፉ ልምድና ዕውቀቱ ያላቸውና ሜዳውን አልምተው እና በጋራ ለመጠቀም የሚፈልጉ አካላትን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለማሰራት ይፈልጋል።

ተፈላጊ መመዘኛዎች:-
1. ህጋዊ ፈቃድና የስራ ልምድ ያለው፤

2. ሜዳውን ለመስራት በቂ በጀትና ባለሙያ ያለው

3. ሜዳውን በስታንዳርድ፤ በዘመናዊ ሁኔታ በተፈለገው ጥራትና ጊዜ መስራት የሚችል፤

4. በጨረታው መወዳድር መመዝገብ የሚፈልግ ድርጅት 1000 ብር (አንድ ሺ ብር) በመክፈል በድርጅቱ የፋይናንስ ዋና ክፍል መመዝገብ ይችላል።

5. የጨረታ ሰነድ ማስገቢያ ቀን ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በተከታታይ 10 የድርጅቱ የስራ ቀናት ውስጥ ይሆናል።

6. ቦታው አዲስ አበባ ጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 05 ከጀነራል ዊንጌት ቴክኒክ እና ሙያ ኮሌጅ አለፍ ብሎ በሚገኘው ልዩ ቦታው አወሊያ በድርጅቱ ዋና መስሪያ ቤት ሲሆን ተጨማሪ ማብራሪያ ካስፈለገ በስልክ ቁጥር
0112708160
0112708158
0900726162 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።

7. ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

አወሊያ ዕርዳታና ልማት ድርጅት

አወሊያ ቴሌግራም
👉 t.me/awoliaschool5

ቀን ሰኞ ሰኔ 8/2018                        ኢናሊላሂ ወኢና ኢሌይሂ ራጅዑን!👉 በአወሊያ ዕርዳታና ልማት ድርጅት በተለያዩ የስራ ክፍሎች በጥበቃ ሠራተኝነት እስከ ዛሬ ድረስ ...
15/06/2026

ቀን ሰኞ ሰኔ 8/2018

ኢናሊላሂ ወኢና ኢሌይሂ ራጅዑን!

👉 በአወሊያ ዕርዳታና ልማት ድርጅት በተለያዩ የስራ ክፍሎች በጥበቃ ሠራተኝነት እስከ ዛሬ ድረስ ሲያገለግል የነበረው ወጣቱ የስራ ባልደረባችን የሆነው ኼይረዲን ዜይኔ የአላህ ቀድር ሆኖ ዛሬ ሰኞ ሰኔ 8/2018 ዓ/ል አመሻሽ ላይ የአላህ ቀድር ሆኖ ወደ አኼራ ሄደዋል።

👉 አላህ ጀነቱል ፍርደውስ ይወፍቀው!
👉 ለቤተሰቦቹም አላህ ሰብሩን ይለግሳቸው!
👉 ለኣላህ ብለን ሁላችንም አውፍ እንበለው!

👉 ጽ/ቤታቸንም በስራ ባልደረባችን ሞት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘኑን እየገለፀ ለቤተሰቦቹም ሆነ ለመላው የጽ/ቤቱ መምህራን እና ሠራተኞች መፅናናትን ይመኛል።

አ/ዕ/ል/ድ

አወሊያ ቴሌግራም
👉 t.me/awoliaschool5

15/06/2026

online exam at awolia Muslim schools

ማስታወቂያለአወሊያ ማህበረሰብ በሙሉ!ቀን ጁምዓ ሰኔ 5/2018የ2018 ዓ.ል የትምህርት ዘመን የሁሉም ት/ት ቤቶች ማጠቃለያ ፕሮግራም ዝርዝር እንደሚከለው ቀርቧልየፈተና ፕሮግራም👉 ከሰኞ ሰኔ...
12/06/2026

ማስታወቂያ
ለአወሊያ ማህበረሰብ በሙሉ!

ቀን ጁምዓ ሰኔ 5/2018

የ2018 ዓ.ል የትምህርት ዘመን የሁሉም ት/ት ቤቶች ማጠቃለያ ፕሮግራም ዝርዝር እንደሚከለው ቀርቧል

የፈተና ፕሮግራም
👉 ከሰኞ ሰኔ 8/2018 እስከ እሮብ ሰኔ 10/2018 የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ይሰጣል።

👉 ከሐሙስ ሰኔ 11/2018 እስከ አርብ ሰኔ 12/2018 የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና (ሚኒስትሪ) ይስጣል።

👉 ከእሮብ ሰኔ 10/2018 እስከ ማክሰኞ ሰኔ 16/2018 ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያሉ የሁሉም ት/ት ቤቶች ተማሪዎች የሁለተኛ ሴሚስቴር ፈተና ይሰጣል።

👉 ከሰኞ ሰኔ 15/2018 እስከ ሐሙስ ሰኔ 18/2018 ከ1ኛ እስከ 7ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎች ፈተና ይሆናል።

👉 የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከሰኔ 24/2018 እስከ ሐምሌ 17/2018 ባሉት ቀናት ውስጥ የሚሰጥ ይሆናል።

የመዝጊያ ፕሮግራም(የወላጆች ቀን)
👉 የአወሊያ ቁ.1 ዋናው ገቢ ኬጂ ተማሪዎች የመዝጊያ ፕሮግራም እሁድ ሰኔ 21/2018 ሲሆን

👉 ከ1ኛ እስከ 11ኛ ክፍል ያሉ የዋናው ግቢ ተማሪዎች ቅዳሜ ሰኔ 27/2018 ይሆናል።

👉 የአወሊያ ፒያሳ 1ኛ እና መካከለኛ ደረጃ ት/ት ቤት እሁድ ሰኔ 28/2018 ሲሆን

👉 በተመሳሳይ የአወሊያ ቁ.2 (ነስር ቅርንጫፍ) ከኬጂ እስከ 11ኛ ክፍል እሁድ ሰኔ 28/2018 የወላጆች ቀን ይሆናል።

ማስታወሻ!
👉 የአመቱ የመጨረሻ ወር እና ውዝፍ የተማሪዎች የት/ት ቤት ወርሃዊ ክፍያ ያለባችሁ እና ያልከፈላችሁ ወላጆች ከፈተና በፊት ባሉት ቀናት ውስጥ ብቻ ክፍያችሁን አጠቃላችሁ እንድትከፍሉ ከወዲሁ ለማስታወስ እንወዳለን።

አወሊያ ሙስሊም ት/ት ቤቶች

አወሊያ ቴሌግራም
👉 t.me/awoliaschool5

የአወሊያ ሙስሊም ት/ቤት የሀገር አቀፍ ፈተናዎች ፈተና ማዕከል እንዲሆን ተመረጠሰኔ 3/2018የአወሊያ ቁጥር 1 ሁለተኛ ደረጃ ሙስሊም ት/ቤት በአገር አቀፍ ደረጃ የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ኦ...
10/06/2026

የአወሊያ ሙስሊም ት/ቤት የሀገር አቀፍ ፈተናዎች ፈተና ማዕከል እንዲሆን ተመረጠ

ሰኔ 3/2018

የአወሊያ ቁጥር 1 ሁለተኛ ደረጃ ሙስሊም ት/ቤት በአገር አቀፍ ደረጃ የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ኦን ላ ይን ፈተና በእራሳቸው ግቢ በማዕከልነት ከሚፈትኑ ትምህርት ቤቶች ሆኖ የተመረጠ ሲሆን ት/ቤቱ ለማዕከልነት ሲመረጥ ሰፊ መስፈርቶችን አሟልቶ ነው፡፡

በአወሊያ እርዳታና ልማት ድርጅት ስር ትምህርት ዘርፍ አመራሮች የተዘጋጀውን መፈተኛ ማዕከል የጎበኙ ሲሆን ባለፈው አመት የተገኘውን ከፍተኛ ውጤት ለማስጠበቅ እንደሚሰራ የትምህርት ዘርፍ ኃላፊው ዑስታዝ መሀመድ ሰኢድ ገልፀዋል፡፡

በተካሄደው ስብሰባም የ2018 የትምህርት ዘመን ማጠቃለያ በደማቅ ሁኔታ እንዲካሄድ አጠቃላይ የዝግጅት ስራዎች እንዲሰሩ የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡

ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተና በኦንላይን(Online) ለሶስተኛ ዙር ተሰጠ!ቀን እሮብ ሰኔ 3/2018👉 የአወሊያ ሙስሊም ቁ.1 ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ል የትምህርት ዘመን የ...
10/06/2026

ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተና በኦንላይን(Online) ለሶስተኛ ዙር ተሰጠ!

ቀን እሮብ ሰኔ 3/2018

👉 የአወሊያ ሙስሊም ቁ.1 ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በ2018 ዓ.ል የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ለሚፈተኑ ተማሪዎች አዲስ በተገዙት ኮምፒውተሮች እና ተማሪዎች ባመጡት ላፕ ቶፕ በመጠቀም የትምህርት ቤቱ ባለሞያዎች ባበለፀጉት አዲስ ድህረ-ገፅ (Website) አማካኝነት የ2ኛ ሴሚስቴር ሙከራ ፈተና ለ3ኛ ዙር ለሁሉም ተማሪዎች በሶስት ፈረቃ በተሳካ ሁኔታ በOnline መስጠት ተችሎዋል።

👉 በዚህም ተማሪዎች በትምህርት ሚኒስቴር አማካኝነት ለሚሰጠው ብሔራዊ ፈተና በትምህርት ቤታቸው ውስጥ በOnline መለማመዳቸው ትልቅ አስተዋፅዖ እና ጥቅም ያለው መሆኑን ተገልጿል።

👉 በቀጣይ ቀናቶች ማጠቃለያ ፈተናዎቹ በOnline መስጠቱ የሚቀጥሉ መሆኑን የሁለተኛ ደረጃ ት/ት ቤት ር/መምህር የሆኑት ዑስታዝ አንዋር አብዱልሃኪም ገልፀዋል።

አወሊያ ቴሌግራም
👉 t.me/awoliaschool5

ማሻአላህ!              አኽላቅ ቶርናመንትቀን እሁድ ግንቦት 30/2018⚽️ ለ18 ዙር በአዲስ አበባ እና አከባቢዋ ባሉት መስጂዶች መካከል የሚካሄደው የአኽላቅ ቶርናመንት እግር ኳስ ...
07/06/2026

ማሻአላህ!
አኽላቅ ቶርናመንት

ቀን እሁድ ግንቦት 30/2018

⚽️ ለ18 ዙር በአዲስ አበባ እና አከባቢዋ ባሉት መስጂዶች መካከል የሚካሄደው የአኽላቅ ቶርናመንት እግር ኳስ ውድድር በ15 መስጂዶች መካከል ለ6 ወር አከባቢ በአወሊያ ሜዳ እና በሌሎችም ሜዳዎች ሲያካሄደው የነበረውን የእግር ኳስ ውድድር በዛሬው እለት እሁድ ግንቦት 30/2018 ፍፃሜውን ያገኘ ሲሆን

⚽️ በፍፃሜው ጨዋታ የተገናኙት የሸህ-ሆጀሌ መስጂድ እና የጃዕፈር ቦሌ መስጂድ ሲሆኑ በተደረገው ብርቱ የሜዳ ላይ ፉክክር ሸህ-ሆጀሌ መስጂድ 2 ለ 0 በሆነ ውጤት ጃዕፈር ቦሌ መስጂድን ማሸነፍ ችሏል።

⚽️ ወጣቱ ሳዲቅ ናስር ከጃዕፈር ቦሌ መስጂድ የውድድሩ ኮከብ ተጫዋች በመሆን የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል።

⚽️ በተጨማሪም ፋህሚ ዜይኑ ከባቡ ረያን መስጂድ 7 ጎል በማግባት ኮከብ ጎል አግቢ በመሆን አጠናቋል።

⚽️ በመዝጊያው ፕሮግራሙ ላይ የአኽላቅ ቶርናመነት አዘጋጅ ኮሜቴ ለአወሊያ ዕርዳታና ልማት ድርጅት ሁልጊዜ ለሚያደርግላቸው ቀና ትብብር እና ድጋፍ የክብር 🏆ዋንጫ🏆 እና የምስጋና ሰርተፊኬት በክብር ከትልቅ ምስጋና ጋር አበርክተዋል።

⚽️ አ.ዕ.ል.ድ ለተደረገለት የዋንጫ ሽልማት እና የእውቅና የምስክር ወረቀት ለአኽላቅ ቶርናመንትን በስራ አስኪያጃችን አማካኝነት ያለውን ምስጋና ያቀርባል።

አወሊያ ት/ት ቤት ቴሌግራም👇👇👇
👉 t.me/awoliaschool5

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when አወሊያ ዕርዳታና ልማት ድርጅት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share