Ethio Gospel Media

Ethio Gospel Media Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Ethio Gospel Media, Community Organization, Addis Ababa.

  🥺ከ40 ዓመታት በላይ፣ ብሩክታዊት እና ጌታያውቃል የወንጌል ዘማሪዎች ብቻ አይደሉም - ለኢትዮጵያ ማህበረሰብ የተስፋ፣ የእምነት እና የመነሳሳት ምንጭ ሆነው ቆይተዋል። በዝማሬ እና በአገል...
02/04/2026

🥺
ከ40 ዓመታት በላይ፣ ብሩክታዊት እና ጌታያውቃል የወንጌል ዘማሪዎች ብቻ አይደሉም -

ለኢትዮጵያ ማህበረሰብ የተስፋ፣ የእምነት እና የመነሳሳት ምንጭ ሆነው ቆይተዋል። በዝማሬ እና በአገልግሎታቸው፣ በኢትዮጵያ እና በ2011 ዩናይትድ ስቴትስን መኖሪያቸው ካደረጉበት ጊዜ ጀምሮ ስፍር ቁጥር የሌላቸውን ህይወት ነክተዋል። በጥልቅ የተወደዱ፣ የተከበሩ እና ሁልጊዜም ለሌሎች ያለ ፈቃደኝነት የሚሰጡ ናቸው።

ዛሬ፣ ከእነሱ ጋር የመቆም ተራችን ነው። ከ2014 ጀምሮ፣ ብሩክታዊት ከባድ የጤና እክል - በአንጎሏ ውስጥ የደም መርጋት በሰውነቷ ግራ በኩል ላይ ተጽዕኖ ያሳደረ፣ ክንዷንና እግሯን የነካ - በድፍረት እየተዋጋች ነው። ይህ ሆኖ ግን፣ ሌሎችን በሚያስደንቅ ጥንካሬ እና እምነት ማገልገሏን፣ መዘመር እና ማበረታታቷን ቀጠለች።

በየካቲት 2026፣ ካቨርኖማን ለማስወገድ በፊላደልፊያ በሚገኘው የጄፈርሰን ሆስፒታል እጅግ ውስብስብ የሆነ የ10 ሰዓት የአንጎል ቀዶ ጥገና ተደረገላት። በእግዚአብሔር ጸጋ፣ ቀዶ ጥገናው ተጠናቀቀ፣ ነገር ግን የማገገሚያ ጉዞዋ ገና እየተጀመረ ነው።

ብሩክታዊት በአሁኑ ጊዜ በማገገሚያ ማዕከል ውስጥ ትገኛለች፣ እዚያም ለሚቀጥሉት 6 እስከ 8 ወራት ትቆያለች። ቀድሞውኑም ከፍተኛ ጥንካሬ እያሳየች ነው - ቀስ ብላ መናገር፣ መብላት እና ድጋፍ በመስጠት መንቀሳቀስ ትችላለች - ነገር ግን አሁንም ረጅም መንገድ ይጠብቃታል።

ማገገሟ ሙሉ ተንቀሳቃሽነት እና ነፃነትን እንድታገኝ ለመርዳት ከፍተኛ የአካል ሕክምና፣ የንግግር ሕክምና እና የሙያ ሕክምና ይጠይቃል።

የስሜታዊ እና የአካል ጉዳት ከፍተኛ ነው፣ ነገር ግን የገንዘብ ሸክሙም እንዲሁ።

የኢንሹራንስ ድጋፍ ቢኖርም፣ የቀዶ ጥገና፣ የማገገሚያ፣ ቀጣይነት ያለው ሕክምና እና የሕክምና እንክብካቤ ወጪ ከፍተኛ የገንዘብ ሸክም ሆኖ ቀጥሏል። ሕክምናው እየቀጠለ ሲሄድ፣ ወጪዎቹ እንደሚጨምሩ ይጠበቃል፣ ይህም በዚህ ወሳኝ የማገገሚያ ጊዜ ውስጥ በእነሱ ላይ እየጨመረ የሚሄድ ጫና ያስከትላል።

በሕይወታቸው በሙሉ፣ ብሩክታዊት እና ጌታያውቃል ያለምንም ማመንታት ለሌሎች ሰዎች አፍስሰዋል። አሁን፣ እኛን ይፈልጋሉ።

ድጋፍዎ በቀጥታ ወደ ብሩክታዊት የሕክምና እንክብካቤ፣ ማገገሚያ እና ማገገሚያ ይሄዳል። ከምንም ነገር በላይ፣ በዚህ አስቸጋሪ ጊዜ የአእምሮ ሰላም ይሰጣቸዋል እና ሙሉ በሙሉ በፈውስ ላይ እንዲያተኩሩ ያስችላቸዋል።

ልክ ብዙዎቻችንን እንደደገፉት ሁሉ፣ ብሩክታዊትን እና ጌታያውቃልን ለመደገፍ እንደ ማህበረሰብ አንድ ላይ እንሰባሰብ።

ትልቅም ይሁን ትንሽ፣ ማንኛውም አስተዋጽኦ በእውነት ለውጥ ያመጣል።

አምልኮ ቲዩብ እጅግ ለምንወዳቸው ቤተሰቦች በቶሎ አገግማ ወደ አገልግሎት እንድትመለስ እየተመኘን። ለጊዜው ሰዎች ኢትዮጵያ ውስጥ ሆነው ድጋፍ ለማድረግ የሚችሉበት መንገድ ቢታሰብበት መልካም ነው እያልን ከሀገር ውጪ ያለን
የጎፈንድሚ ማስፈንጠሪያውን በመጫን ድጋፋችችንን እናድርግ https://gofund.me/57e1c877c

"እኔ ምስክር ነኝ!" በሚል መሪ ቃል የቢሾፍቱ ወንጌላዊያን አብያተክርስቲያናት ህብረት የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን የትንሳኤ በዓል ምክንያት በማድረግ ታላቅ የወንጌል ዘመቻ እና የማስታጠቅ...
02/04/2026

"እኔ ምስክር ነኝ!" በሚል መሪ ቃል የቢሾፍቱ ወንጌላዊያን አብያተክርስቲያናት ህብረት የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን የትንሳኤ በዓል ምክንያት በማድረግ ታላቅ የወንጌል ዘመቻ እና የማስታጠቅ ጉባኤ አዘጋጅቷል።

የጌታን የመስቀል እና የትንሳኤውን ስራ በመመስከር የትንሳኤውን ብርሃን እናብራ!

1. የወንጌል ስርጭት ዘመቻ
• ቀን፡ ከመጋቢት 28 - ሚያዝያ 2
• ቦታ፡ በአራቱ የከተማዋ አዋሳኝ አቅጣጫዎች
2. የፍቅር ስጦታና የአደባባይ ምስክርነት
• ቀን፡ ሚያዝያ 1 ቀን
• ቦታ፡ በቢሾፍቱ ስታድየም
• ክንውኖች፡ የደም ልገሳ፣ የወንጌል ስርጭት እና የምስጋና ዝማሬ
3. "እኔ ምስክር ነኝ" የማስታጠቅ ጉባኤ
• ቀን፡ ከመጋቢት 28 - ሚያዝያ 2
• ሰዓት፡ ከምሽቱ 10:30 - 1:30
• ቦታ፡ በመሃል ከተማ ሙሉ ወንጌል ቤተክርስቲያን
ኑ! እንታጠቅ፣ እንመስክር፣ ነፍሳትን ወደ መንግስቱ እንሰብስብ።

ፓስተር ደረጄ ታፈሰ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርሲቲያናት ሕብረት ፕሬዝደንት ሆኑ።የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርሲቲያናት ሕብረት ዛሬ ባካሄደው ጉባኤ ፓስተር ደረጄ ታፈሰ ፓስተር ...
29/01/2026

ፓስተር ደረጄ ታፈሰ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርሲቲያናት ሕብረት ፕሬዝደንት ሆኑ።

የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርሲቲያናት ሕብረት ዛሬ ባካሄደው ጉባኤ ፓስተር ደረጄ ታፈሰ ፓስተር ፃድቁ አብዶን በመተካት የኢትዮጵያ ወንጌላዊያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት ፕሬዚደንት ሆነው እንዲመሩ እንደመረጣቸው አስታውቋል።

የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት ዛሬ ጥር 20 ቀን 2018 ዓ/ም ባካሄደው 40ኛ ጠቅላላ ጉባኤ የኃላፊነት ዘመናቸውን ባጠናቀቁት ፓስተር ፃድቁ አብዶ ምትክ ነው ፓስተር ደረጄ ታፈሰን ፕሬዚዳንት አድርጎ የመረጣቸው።

ፓስተር ደረጄ ከዚህ ቀደም በኅብረቱ የሚሽን እና ቲዮሎጂ መምሪያ ዳይሬክተር ሆነው ሲሰሩ መቆየታቸው ተነግሯል።

ፓስተር ፃድቁ አብዶ በበኩላቸው ላለፉት አስርት ዓመታት ሕብረቱን በፕሬዝዳንትነት የመሩት ሲሆን በስልጣን ሽግግሩ ላይ ባደረጉት ንግግር መላውን የሕብረቱን አመራሮችና አባላቶችን በማመስገን ለተመራጩ የሕብረቱ ፕሬዚዳንት መልካም የአገልግሎት ዘመን እንዲሆን ተመኝተዋል።

ለኢየሱስ ይገባዋል በሚል መሪ ቃል ዳግም እንደገና ጌታችንና መድሀኒታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን ተሰብስበን ልናመልከው እሁድ ጥር 3 ከ8 ሰአት ጀምሮ በጊዮን ሆቴል ጊቢ ውስጥ ከዘማሪ ዳግማዊ ጥ...
14/12/2025

ለኢየሱስ ይገባዋል በሚል መሪ ቃል ዳግም እንደገና ጌታችንና መድሀኒታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን ተሰብስበን ልናመልከው እሁድ ጥር 3 ከ8 ሰአት ጀምሮ በጊዮን ሆቴል ጊቢ ውስጥ ከዘማሪ ዳግማዊ ጥላሁና (ዳጊ) እና ከሀረር አማኑኤል መዘምራን ጋር ልናመሰግነው ቀጠሮ ይዘናል በዚህ ቀን ሁላችሁንም በአክብሮት ጋብዘናችዋል ተባረኩ ::

“የታረደው በግ ኃይልንና ብርታትን፣ ጥበብንና ክብርን፣ ክብርና ምስጋናን ለመቀበል ይገባዋል!”
— ራእይ 5፥12

  ? በተለያዩ እንቅስቃሴዎች
06/12/2025


?

በተለያዩ እንቅስቃሴዎች

 #ጥቅምት 23 #ወንጌል ያሸንፋል!
30/10/2025

#ጥቅምት 23
#ወንጌል ያሸንፋል!

ረቡዕ ጥቅምት  12 /201811:00ዩጎ ሲቲ ቤተክርስቲያን
21/10/2025

ረቡዕ ጥቅምት 12 /2018

11:00

ዩጎ ሲቲ ቤተክርስቲያን

ጥቅምት 23ወንጌል ያሸንፉልበሚሊንየም አዳራሽ
19/10/2025

ጥቅምት 23
ወንጌል ያሸንፉል
በሚሊንየም አዳራሽ

“በጊዮን ሆቴል ግቢ ውስጥ የተከናወነ ምክንያቴ ብዙ ነው የመዝሙ ድግስ ውብ በሆነ ሁኔታ ተዘጋጅቷ::Coming soon ❗️❗️
18/10/2025

“በጊዮን ሆቴል ግቢ ውስጥ የተከናወነ ምክንያቴ ብዙ ነው የመዝሙ ድግስ ውብ በሆነ ሁኔታ ተዘጋጅቷ::Coming soon ❗️❗️

BIBLE 📖📖📖UP⬆️PHONE 📱  DOWN ⬇️ቻሌንጁን ተቀላቀሉእንደገና ቃሉን ብድግ ምናደርግበት አመት ይሁን።  በነገሮቻችን ሁሉ ላይ ኮቴው እንዲበዛ ቃሉ ላይ እንብዛ።  በየሆቴሉ በየካፊቴ...
29/09/2025

BIBLE 📖📖📖UP⬆️
PHONE 📱 DOWN ⬇️

ቻሌንጁን ተቀላቀሉ

እንደገና ቃሉን ብድግ ምናደርግበት አመት ይሁን። በነገሮቻችን ሁሉ ላይ ኮቴው እንዲበዛ ቃሉ ላይ እንብዛ። በየሆቴሉ በየካፊቴሪያው ባስ ሆነ ሰው ሆነ ታክሲ እየጠበቅን ጠረጴዛዎቻችንን በመፅሀፍ ቅዱሳችን እናጣብባለን። እናወራዋለን እንጫወተዋለን። ሞባይሎቻችን እጃችን ላይ በሚታዩበት ቁመት ልክ በቀረው ዘመናችን ቃሉን ከፍ አድርገን እንይዛለን። ባገኘናት ክፍተት ሁሉ ይህ ቅዱስ ቃል ይገለጣል። ይነበባል አሜን በየመንገዱ እንደቦርሳ አንጠልጥለነው እንውላለን።
የተስማማችሁ ተቀላቀሉ።

Bible 📖📖📖📖📖 UP ⬆️⬆️⬆️⬆️⬆️⬆️⬆️⬆️⬆️

PHONE 📱 📱📱📱📱DOWN ⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️

“ድፍርስ ጀረቶች”በወንድማችን ሰለሞን አበበ ገብረ-መድህን የተጻፈው መጽሐፍ መስከረም 18 ቀን 2018 ዐ.ም በኢትዮጵያ አማኑኤል ኅብረት ቤተ ክርስቲያን ሀልዎት አጥቢያ ከ8:30 ጀምሮ ይመረ...
27/09/2025

“ድፍርስ ጀረቶች”

በወንድማችን ሰለሞን አበበ ገብረ-መድህን የተጻፈው መጽሐፍ መስከረም 18 ቀን 2018 ዐ.ም
በኢትዮጵያ አማኑኤል ኅብረት ቤተ ክርስቲያን ሀልዎት አጥቢያ ከ8:30 ጀምሮ ይመረቃል።

አድራሻ፦ ወሎ ሰፈር ጎርጎሪዮስ አደባባይ ፊውቸር ታለንት ት/ት ቤት አጠገብ

ትንቢተ ኤርምያስ 29:11¹¹ ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም።ሕይወት በየዕለቱ በብዙ ጥያቄዎች የተሞላ...
23/09/2025

ትንቢተ ኤርምያስ 29:11
¹¹ ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም።

ሕይወት በየዕለቱ በብዙ ጥያቄዎች የተሞላች ናት። ነገ ምን ይዞ ይመጣል? ህልሜ እውን ይሆናል? አሁን ያለሁበት አስቸጋሪ ሁኔታ እንዴት ሊለወጥ ይችላል? እነዚህ ጥያቄዎች በልባችን ሲንዣበቡ፣ ሰላማችንን ሊያሳጡን ይችላሉ። በተለይ ደግሞ ነገሮች ከቁጥጥራችን ውጪ ሲሆኑ፣ ተስፋን ማጣት ቀላል ነው።

በዚህ አይነት ስሜት ውስጥ ስንሆን፣ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ያለውን አስደናቂ እውነት ማስታወስ አለብን። በነቢዩ ኤርምያስ በኩል እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፡- "ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም።" (ኤርምያስ 29:11)

ይህ ቃል የተነገረው ለእስራኤላውያን በምርኮ ላይ ሳሉ ነበር። ሁኔታቸው እጅግ አስቸጋሪ ነበር፤ የወደፊት ሕይወታቸው ጭላንጭል የለሽ መስሎ ነበር። ነገር ግን እግዚአብሔር ተስፋን ሰጣቸው። ይህ መልእክት ዛሬ ለእኛም ነው። እግዚአብሔር ስለእኛ ያለው እቅድ ሁሌም መልካም ነው። ይህ ማለት ህይወት ቀላል ነው ማለት አይደለም፣ ነገር ግን በእርሱ እጅ ስላለች መልካም ፍጻሜ አላት ማለት ነው።

ለምን በቃሉ ልንተማመን ይገባል?
* የእግዚአብሔር እቅድ መልካም ነው: እርሱ እኛን ለመጉዳት ሳይሆን ለመልካም ዓላማ አሰበልን። እርሱ ስለወደፊታችን የሚያስብ አፍቃሪ አባት ነው። የምናልፍበት መንገድ ምንም ቢሆን፣ የመጨረሻው መድረሻችን ከእርሱ ጋር ነው።
* እምነት እና መታመን: እግዚአብሔር ያሰበልንን መልካም ዕቅድ ባናየውም፣ እርሱ እንደሚፈጽመው በእምነት ልንታመን ይገባል። እምነት ማለት አሁን የምናየው ነገር ሳይሆን፣ እግዚአብሔር በቃሉ የሰጠንን ተስፋ መያዝ ነው።
* ፍጻሜው በእርሱ እጅ ነው: እኛ አሁን ያለውን ሁኔታ ብቻ ነው የምናየው፤ እርሱ ግን ፍጻሜውን ያያል። ለዚህም ነው በእርሱ ተስፋ ማድረግ የሰላም ምንጭ የሆነው።
ታዲያ ይህንን እውነት እንዴት ነው ወደ ተግባር የምንለውጠው? በየዕለቱ ቃሉን በማስታወስ፣ ጭንቀታችንን በጸሎት ለጌታ በመስጠት እና ትንሽ ትንሽ ነገርን እንኳን በማመስገን።

አስታውሱ፣ የእናንተ መጪው ጊዜ በፈጣሪ እጅ ነው። ተስፋችሁ በእርሱ ላይ ሲሆን፣ መንገዱ ምንም ያህል አስቸጋሪ ቢሆን እንኳን፣ ልባችሁ በሰላም ይሞላል። አሁን ያላችሁበት ሁኔታ የመጨረሻ መድረሻችሁ አይደለም። የእግዚአብሔር ዕቅድ መልካም ነውና፣ በደስታ ወደ ፊት ተጓዙ!

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio Gospel Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share